TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Poweroutage
Ethiopiancoffee
Update
Ministryofrevenues
Firealert
Jimma
Wolkite
Silte
Arerti
Addisababa
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 209.53K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-03-27 18:08:40
"የኢትዮጵያ ክላሲካል ሙዚቃዎች እናት"

"የኢትዮጵያ ክላሲካል ሙዚቃዎች እናት" ተብለው የሚጠሩት እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ በ100 ዓመታቸው ማረፋቸውን የሀገር ውስጥ የዜና ተቋማት ዘግበዋል።

እማሆይ ፅጌ ማርያም ከአባታቸው ከከንቲባ ገብሩ ደስታና ከእናታቸው ከወ/ሮ ካሳየ የሌምቱ በአዲስ አበባ ከተማ በ1915 ዓ.ም ታህሳስ 4 ቀን ነው የተወለዱት።

በስድስት ዓመታቸው በኢትዮጵያ መንግስት ፈቃድ ከታላቅ እህታቸው ስንዱ ገብሩ ጋር ለትምህርት ወደ ስዊዘርላንድ የተጓዙ ሲሆን መሠረታዊ ትምህርት፣ ቋንቋ እና ሙዚቃ አጥንተው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

በኢትዮጵያ ዘመናዊ የመንግስት አስተዳደር መዋቅር ሲዘረጋም የመጀመሪያዋ ሴት ፀሐፊ በመሆን ለ2 ዓመት አገልግለዋል።

ለዕረፍት ብለው ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ ባቀኑበት በ25 ዓመታቸው በመመንኮስ ለአስር አመታት እዛው የቆዩ ሲሆን በኋላ ላይም ወደ አባታቸው ሀገር ጎንደር በመሄድ ለአምስት አመታት ቆይተዋል።

ከዛም ከእናታቸው ጋር በመሆን ወደ እየሩሳሌም የሄዱ ሲሆን እናታቸው ከአንድ አመት ቆይታ በኋላ ሲመለሱ እማሆይ ግን በጳጳሱ በአቡነ ዮሴፍ ፅ/ቤት ለአምስት አመታት አገልግለዋል። በዚህ መሀልም መነኩሴ ሁነው እንዴት ፒያኖ ይጫወታሉ በሚል አለመግባባት ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። የንጉሱ አገዛዝ በወታደራዊ አገዛዝ ሲተካ ዳግም ወደ እስራኤል ተመልሰዋል።

ከሰሯቸው በርካታ ስራዎች መካከልም Homeless Wonder (ሆምለስ ወንደር)፣ The son of seam (ዘ ሰን ኦፍ ሲም)፣ The mad man's daughter (ዘ ማድ ማንስ ዶተር) እና Mother's love (ማዘርስ ላቭ) የሚል አርዕስት ያላቸው ሥራዎች በምሳሌነት ይጠቀሳሉ።

እማሆይ ጽጌ ማርያም እንግሊዝኛ፣ ጀርመንኛ፣ ዕብራይስጥኛ፣ አማርኛና ግዕዝን አቀላጥፈው ይናገሩ ነበር። የተለያዩ የሙዚቃ ስራዎቻቸውንም በተለያዩ ኮንሰርቶች ላይ በማቅረብ የሚገኘውንም ገንዘብ ለድሆች መርጃ አውለዋል።

ከእረፍታቸው ጋር ተያይዞ ዝርዝር መረጃ ለጊዜው አልወጣም።

@tikvahethmagazine
19.4K viewsedited  15:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 15:03:31
በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የጨረር ህክምና መስጫ ማሽን አገልግሎት መቆራረጥ ቅሬታን አስነስቷል።

በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆስፒታሉ ከሚሰጡ ህክምናዎች አንዱ በሆነው የካንሰር ህክምና ማዕከል ያለው የጨረር ህክምና መስጫ ማሽን በመቆራረጡ ምክንያት ብዙ ወረፋ ጠብቀው አገልግሎት ለማግኘት የሚመጡ ታካሚዎች እየተንገላቱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በካንሰር ህክምና ያሉ የህክምና ባለሙያዎች ደግሞ በማሽኑ አገልግሎት መቋረጥ ሳቢያ ብዙ ወራትን ወረፋ ጠብቀው አገልግሎቱን ለማግኘት የሚመጡ ታካሚዎችን ህይወት አደጋ ላይ መውደቁንና በባለሙያዎችም ላይ የስነ ልቦና ጫና መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡

የህክምና ማዕከሉ ኃላፊ የካንሰር ህክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር ኤዶም ሰይፈ የማሽኑ አገልግሎት ሲቋረጥ የታካሚዎቹ ህመም ይበልጥ ሊወሳሰብ የሚችልበት አጋጣሚ ስለመኖሩ ገልጸዋል፡፡

ለማሽኑ ጥገና የሚስፈልጉ መለዋወጫዎች በቶሎ አለመገኘታቸውና አለመድረሳቸው ለአገልግሎቱ መቆራረጥ ዋና መንስኤ ነው ያሉት ኃላፊዋ አንድ ማሽን በቂ ባለመሆኑ ህሙማንን መታደግ ይቻል ዘንድ ተጨማሪ ማሽን ሆስፒታሉ እንደሚያስፈልገው መጠቆማቸውን ኢብኮ ዘግቧል።

#ማስታወሻ፡ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የጨረር ህክምና መስጫ ማሽን አገልግሎት መስጠት ያቆመው ባለፈው ሳምንት ሲሆን ከሁለት ቀናት በኋላ አገልግሎት አገልግሎት መስጠት #መጀመሩን ማረጋገጥ ችለናል።

በዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው መረጃ መሰረት በኢትዮጵያ በየአመቱ 70 ሺህ ሰዎች በካንሰር ይያዛሉ።

በሌላ በኩል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቀውንና ጨረር በማመንጨት ካንሰርን የሚገድለውን ‹‹ሌይነር አክስለሬተር›› የተሰኘ ዘመናዊ የካንሰር ህክምና መስጫ ማሽን በ24 ሚሊየን ዶላር ወጪ ለ7 ዩንቨርስቲዎች ያስረከበ ቢሆንም አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት የጅማና የሐሮማያ ዩኒቨርሲቲዎች ናቸው።

@tikvahethmagazine
23.0K viewsedited  12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 12:21:38
በኢትዮጵያ ከሚመረተው ኤሌክትሪክ ኃይል አብዛኛው ጥቅም ላይ እየዋለ አይደለም፤ ምክንያቱ ምን ይሆን?

ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ የማመንጨት አቅሟ ከ5 ሺህ 200 ሜጋ ዋት በላይ የደረሰ ቢሆንም እየተጠቀመች ያለው የኃይል አቅርቦት ግን ከ 1 ሺህ 700 ሜጋ ዋት የዘለለ አይደለም።

የሚመነጨውን ኃይል መሸከም የሚችልና ወደ እያንዳንዱ ደንበኛ የሚያደርስ መሠረተ ልማት አለመዘርጋቱ የምታመነጨውን ኤሌክትሪክ ኃይል እንዳትጠቀም አድርጓታል ነው የተባለው።

ይህን የገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ መላኩ ታዬ ሲሆኑ የችግሩ መንስኤም ኃይል ለማመንጨት የሚሰጠውን ትኩረት ያህል ኃይልን ተደራሽ ለማድረግ የሚሰጠው ትኩረት አነስተኛ በመሆኑ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቂ ኃይል እያመነጨ ቢሆንም የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያዎች ቁጥር ግንባታ አነስተኛ በመሆኑ ተደራሽነቱ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እያሳደረ ይገኛልም ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን ተደራሽ ለማድረግ የፀሐይ የኃይል ምንጭን እንደአማራጭ እየተጠቀመ መሆኑን ገልጸው በዚህም በ12 የገጠር ከተሞች በ8.5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የፀሐይ ኃይል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን አቶ መላኩ አንስተዋል። (EPA)

@tikvahethmagazine
9.2K viewsedited  09:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 10:42:26
"ነጭ ወርቅ" የተባለው እጣን በኩንታል እስከ 23 ሺ ብር ያወጣል!

ምዕራብ ጎንደር ዞን አጠቃላይ ካለው የደን ሽፋን 30 በመቶው በእጣን ዛፍ የተሸፈነ ነው። በእጣንና ሙጫ በማምረት የተሰማሩ ሰዎች ከዚሁ ምርት የሚገኘው ገቢ ከሰሊጥ፣ ጥጥና ማሽላ ምርት ከሚገኘው ገቢ በአስር እጥፍ  ብልጫ እንዳለው ያስረዳሉ።

የኑስ ዲቦ የተባሉ አምራች በ2014 ዓ.ም 1 ኩንታል እስከ 23 ሺህ ብር ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ለአብነት አንስተዋል። በዚህም የአብዛኛው የማኅበሩን አባላት  ሕይወት መለወጡን ነው የገለጹት።

መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፦

- በ2014 በጀት ዓመት በዞኑ 4 ሺህ 80ዐ  ኩንታል የሚጠጋ እጣንና ሙጫ የተመረተ ሲሆን ከ67 ሚሊዮን ብር በላይ  ደግሞ ገቢ ተገኝቷል።

- ዘንድሮ ከ9 ሺህ ኩንታል በላይ የእጣንና ሙጫ ምርት በመሰብሰብ ከ163 ሚሊዮን ብር በላይ  ደግሞ ገቢ ለማግኘት ታቅዷል።

- በዞኑ ያለውን ሃብት በሙሉ አቅም ማምረት ቢቻል በዓመት ከ35 ሺህ በላይ ኩንታል የእጣንና  ሙጫ ምርት ማግኘት የሚቻለሰ ሲሆን ይህም አሁን ባለው ዋጋ እንኳ ለገበያ ቢቀርብ 609 ሚሊዮን ብር ዞኑ ገቢ ማግኘት ይችላል።

ይህ ኃብት ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ችግሮች ምክንያት በሚጠበቀው ልክ ጥቅም ላይ አልዋለም። አሁን ላይ በአከባቢው 22 ማኅበራትና 24 ባለሃብቶች በእጣንና ሙጫ ማምረት ፈቃድ ወስደው ወደ ሥራ ገብተዋል።

የሕገ ወጥ እርሻ መስፋፋት፣ ሰደድ እሳት እና ሌሎች ችግሮችን ለመከላከል የጥበቃ ሥራ ላይ ትኩረት መደረጉ የተገለጸ ሲሆን በተለይም ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዋጋው እየጨመረ በመምጣቱ የአካባቢው ማኅበረሰብ ጥበቃ እየተጠናከረ  መምጣቱ ተነግሯል።

ምንጭ : አሚኮ

@tikvahethmagazine
13.3K viewsedited  07:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 09:53:25
የቡና አቅራቢና ላኪዎች ባለፉት ሳምንታት በመዲናዋ ቡና በጫኑ መኪኖች ላይ የደረሰው ዘረፉ እንዳሳሰባቸው ገለጹ።

በቡና ኢንዱስትሪ ውስጥ ያሉ ላኪዎችና አቅራቢዎች ከተለያዩ አከባቢዎች በጭነት መኪና ተጓጉዘው ወደ ውጭ በሚላኩ ቡናዎች ላይ በአዲስ አበባ አልፎ አልፎ እየተከሰተ ያለው ስርቆት ስጋት ውስጥ እንደከተታቸው ገልጸዋል። ይህ ስጋት ባለፉት ሳምንታት ሶስት ቡና የጫኑ መኪኖች ከተዘረፉ በኋላ የተፈጠረ ነው።

ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ እያንዳንዳቸው በአማካይ 61 ኪሎ ግራም ቡና የያዙ፤ 300 ጆንያ ቡና የጫነ መኪና የቃሊቲ ጉምሩክ ኬላን ካለፈ በኋላ መዘረፉ ተገልጿል። ይህ 11 ሚሊየን ብር ያወጣል ተብሎ የሚገመተው ቡና መነሻው ከሲዳማ ክልል ቤንሳ ወረዳ ነበር።

መኪናው ቡናውን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ በአዲስ አበባ በተዘጋጁ መጋዘኖች ለማራገፍ በመንገድ ላይ ነበር። ከጥቂትም ሳምንታት በፊትም እንዲሁ ሁለት ተጨማሪ የጭነት መኪናዎች የቡና አቅራቢዎች እና የቡና ላኪ መኪኖች ላይ ተመሳሳይ ዝርፊያ ተከስቷል።

የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን ከጥቂት ሳምንታት በፊት፣ በሦስት የጭነት መኪናዎች ላይ የተፈጸመው ዘረፋ ሪፖርት እንደደረሰው አስታውቋል። የተቋሙ ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ኡመር መሥሪያ ቤታቸው የቡና ስርቆት ሪፖርቶች ከላኪዎች እንደደረሰው አረጋግጠው "እነዚህ ክስተቶች ከጀመሩ ጥቂት ሳምንታት አልፈዋል፤ እና መፍትሄ ለማግኘት ከህግ አስከባሪዎች ጋር እየሰራን ነው" ሲሉ ገልጸዋል።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የሲዳማ ቡና አቅራቢዎች ማኅበር ከፍተኛ አመራር አባል እና አቅራቢ ዘረፋ ከተፈጸመባቸው ሁለቱ የማኅበሩ አባላት መሆናቸውን አንስተው በቅርቡ ስለተፈጸመው ዝርፊያ ሲናገሩ፥ "መኪናው ቡናውን ወደ አዲስ አበባ ሲያጓጉዝ ነበር። ከዚያም ሹፌሩና ረዳቱ ቃሊቲ ካለፉ በኋላ ተዘርፈናል ብለው ደወሉ።  እነሱ ወንበዴዎቹን ያውቋቸው እንደሆን ባናውቅም የሚገርመው የጭነት መኪናው ሙሉ ይዘቱ በአዲስ አበባ መዘረፉ ነው።" ሲሉ ነው የገለጹት። አሽከርካሪው እና ረዳቱ አሁን በፖሊስ ቁጥጥር ስር መሆናቸውንም አክለዋል።

ጥቃት ከደረሰባቸው አንዱ በበኩላቸው፥ “የላላ የጸጥታ ጥበቃ ባለበት አካባቢ እንኳን ምንም አይነት ዘረፋ አልደረሰብንም። ህግ የማስከበር ስራ በተጠናከረበት እና የህግ የበላይነት በሚከበርበት አካባቢ እንዴት እንዘረፋለን ብለን እንገምት?" ብለዋል። "ቡናውን ለዓለም አቀፍ ደንበኞቼ ሸጫለሁ፤ አሁን ምን ልልክላቸው ነው?" ሲሉም ይጠይቃሉ።

ዘገባው የሪፖርተር ሲሆን ዘረፋ የተፈጸመባቸው አቅራቢዎችና ላኪዎች ጉዳዩን ያስረዱት ፖሊስ ጉዳዩ ላይ ምርመራ ከመጀመሩ በፊት መሆኑን በዘገባው ጠቁሟል።

@tikvahethmagazine
13.7K viewsedited  06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 09:52:27
#ጥቆማ

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የዓይን ሕክምና ትምሕርት ክፍል Fight Blindness in Ethiopia ከተባለ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር #ነፃ የዓይን ምርመራና የሞራ ቀዶ ጥገና አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

የቀዶ ሕክምና አገልግሎቱም በሞራ ግርዶሽ ምክኒያት ለማየት የተቸገሩ ታካሚዎችን እይታ ለመመልስ ያለመ ነው።

ስለሆነም እስከ መጋቢት 22/2015 ዓ.ም ችግሩ ያለባችሁ ሰዎች ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዓይን ሕክምና ክፍል በመገኘት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ሆስፒታሉ ጥሪ አቅርቧል።

አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ሰዎች #Share በማድረግ እናድርስ

@tikvahethmagazine
12.0K viewsedited  06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 09:52:11
#AmazonFashion

አማዞን ፋሽን ለሙሽራ፣ ለሚዜ፣ ለባንክ ቤት ሰራተኞች እና ለተመራቂ ተማሪዎች ‍የሚሆኑ  ሱፎች፣ ሸሚዞች፣ ጫማዎች፣ ከረባቶች፣ ኮቶች በብዙ አማራጭ እና እጅግ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርበንሎታል።

ለጨረታ እና በብዛት ፈላጊዎች ከ4000 ሺ ብር ጀምሮ ሙሉ ልብሶችን እናስረክባለን። በብዛት ለሚወስዱ የብድር አገልገሎት አንዲሁም በሚፈለገው ሳይዝ እናቀርባለን።

አድራሻ፦ ፒያሳ Down Town ህንፃ ምድር ላይ እና 2ኛ ፎቅ                                                            
0919339250 , 0923468025 
https://t.me/joinchat/AAAAAEc8iQJX1Zjgepjq1w
11.2K views06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-27 09:52:02
ሌዘርቴክ ዲዛይን የቤት፣ የቢሮ፣ የህንፃ ፣ የሪል ስቴት፣ የአፓርትመንት የተለያዩ የሜካኒካል እና የአርክቴክቸር ብረታ ብረት ስራዎችን ያቀርባል።

በዋናነት ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል
Handrail, Gates & Fences
Wall art & Logo/adverts
Partitions & Facades
Custom tables and furniture
AC Installation, Garbage Chutes & more

አድራሻችን : መስቀል ፍላወር ከdreamliner hotel አጠገብ
ቻናሉን ይቀላቀሉ : t.me/lasertechethiopia

ለበለጠ መረጃ
Phone : 0970094777
Contact : @lasertech_design
Website : lasertechplc.com

ፈጠራ, ጥራት እና ፍጥነት የስራችን መሰረት ነው!
12.2K views06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 11:56:01
የምልክት ቋንቋን የሥራ ቋንቋ ማድረግ ለሰብአዊ መብቶች መከበር ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል

በኢትዮጵያ ምን ያህል መስማት የተሳናቸው ሰዎች እንዳሉ ትክክለኛውን ቁጥር ለማወቅ አስቸጋሪ ቢሆንም፤ እስከ 1 ሚሊዮን የሚደርሱ ከመስማት ጋር የተገናኘ ጉዳት ያለባቸው ሰዎች እንደሚኖሩ ይገመታል።

የምልክት ቋንቋዎች የራሳቸው ሰዋሰው፣ መዝገበ ቃላት እና ዘዬ ያላቸው የተሟሉ፣ ቋንቋዎች ሲሆኑ፤ ከውልደት ጀምሮ መስማት ለተሳናቸው ሕጻናት ደግሞ ብቸኛ የመጀመሪያ ቋንቋቸው ነው፡፡

ከኢትዮጵያ የብሔር ብዝኃነት አንጻር ተጨማሪ ቋንቋዎችን በሥራ ቋንቋነት ለማካተት የሚያስችል የቋንቋ ፖሊሲ በቀረጻ ሂደት ላይ መሆኑ ቢታወቅም፤ መስማት ለተሳናቸው ሰዎች የግድ አስፈላጊ የሆነውን የምልክት ቋንቋን የሥራ ቋንቋ ለማድረግ በቂ ትኩረት አላገኘም።

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነትን በአዋጅ ቁጥር 676/2002 አጽድቃ ተቀብላለች። በዚህም የምልክት ቋንቋ ትምህርትን የማመቻቸትና የማበረታታት ግዴታ አለባት።

የምልክት ቋንቋን ይፋዊ የሥራ ቋንቋ ማድረግ መስማት የተሳናቸውን ሰዎች መረጃ የማግኘት መብት ለማረጋገጥ፣ በማኅበረሰብ ውስጥ በሁሉም ዘርፍ የሚኖራቸውን የተሳትፎ መጠንና የአገልግሎት ተደራሽነት ለማሳደግ ብሎም ሰብአዊ መብቶቻቸው ሙሉና ውጤታማ በሆነ ደረጃ እንዲረጋገጡ ለማስቻል አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡

ሙሉ ጹሑፉን ለማንበብ https://ehrc.org/expertview

#HandsSpeakEyesListen
#እጆች_ይናገራሉ_አይኖች_ያዳምጣሉ

@tikvahethmagazine @RWethiopia
19.9K viewsedited  08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-26 11:54:48
#DireDawa: ከሚያሽከረከረው ባጃጅ ላይ የተረሳ 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ

መጋቢት 15 ቀን በምሽቱ ፈረቃ ለሥራ የወጣው አሽከርካሪ ወጣት መኮንን ግርማ  አቶ መሀመድ ዑስማን የተባሉ ተሳፉሪን  ከሳቢያን ወደ ኦርቢት ያደርሳል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ ተደውሎ ይጠየቃል።

አሽከርካሪው እንደተባለው ከተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለት በላስቲክ የተጠቀለለ በርካታ ብር ተቀምጦ ማግኘቱን እና ወዲያው ገንዘቡን ይዞ ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳሬክቶሬት በመምጣት 150ሺህ ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ተናግሯል።

ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ዑስማን ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የምሽት ባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውንና፣ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋና ማቅረባቸውን የድሬዳዋ ፖሊስ አስታውቋል።

ስለ ድሬዳዋ የምሽት ባጃጆች እንቅስቃሴ አዲስ ዘይቤ የድሬዳዋ የሌሊት ሾፌሮች ትላንት እና ዛሬ ከሚለው ጹሑፍ ማንበብ ይቻላል።

@tikvahethmagazine
17.7K viewsedited  08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ