TIKVAH-MAGAZINE — የቴሌግራም ቻናል

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 192.64K
ተመሳሳይ ቻናሎች ዜና
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያና የመረጃ መለዋወጫ መድረክ ነው። በ 251913134524 ላይ ያግኙን። ለማስታወቂያ @tikvahmagbot ላይ መረጃ ይጠይቁ።

የቻናል ስታትስቲክስ
8.7% የተሳትፎ መጠን
16,750 እይታዎች / ልጥፍ
0 ልጥፎች / ቀን

የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

16 märts 2024
Picture 1 from TIKVAH-MAGAZINE 2024-03-16 21:22:29
በጆርዳን ላሉ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች ዝቅተኛ የወር ደሞዝ የተጣራ 275 የአሜሪካ ዶላር እንዲሆን ተወሰነ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጆርዳን ተቀጥረው ለሚሰሩ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች ዝቅተኛው የወር ደሞዝ የተጣራ 275 ዶላር እንዲሆን መወሰኑን ሰምቻለው በማለት ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ውሳኔው ባለፉት ሁለት ዓመታት የቤት ሰራተኞች ፍላጎት በጨመረባት ሀገር ጆርዳን የሚገኙ ከ20,000 በላይ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች ላይ ተፈጻሚ የሚሆን መሆኑን ዘገባው ጠቅሷል።

ለሰራተኞቹ የደመወዝ ጭማሪ በአመት ይደረጋል የተባለ ሲሆን ለዚህም ከኢትዮጵያና ከጆርዳን መንግስት ተወካዮች የተውጣጣ ጥምር ኮሚቴ ተቋቁሞ ወቅታዊውን ሁኔታ ያገናዘበ የደመወዝ ጭማሪ እንዲደረግ ክትትል የሚደረግ መሆኑ ተገልጿል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዚህ ሳምንት ባደረገው ስብሰባ በኢትዮጵያ መንግስት እና ጆርዳን መንግሥት መካከል የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት ያፀደቀ ሲሆን የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ ከቤት ሰራተኞች ውጪ ያሉ ለሌሎች በጆርዳን ተቀጥረው ለሚሰሩ ኢትዮጵያውያን የወር ደሞዝ ዝርዝሮችን ያላካተተ መሆኑ ተጠቁሟል።

ይህ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የቤት ሰራተኞቹ በቀን 8 የስራ ሰዓት እንዲሰሩ እና በሳምንት 48 ሰአት የእረፍት ጊዜ እንዲሰጣቸው ያስቀመጠ መሆኑም ተጠቁሟል።

በርካታ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ለኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች በራቸውን የከፈቱ ሲሆን መንግስት ወደ ቀጠናው መጓዝ የሚፈልጉ ሰራተኞችን መደበኛ እና ህጋዊ ማድረግ የጀመረ ቢሆንም የሰራተኛ መብት ተከራካሪዎች የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ለቤት ሰራተኞች የሚከፍሉት ክፍያ ያነሰ ነው በማለት የሚተቹ ስለመሆኑም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine
17.0K viewsedited  18:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
3 märts 2023
Picture 1 from TIKVAH-MAGAZINE 2023-03-03 13:44:37
Picture 2 from TIKVAH-MAGAZINE 2023-03-03 13:44:37
Picture 3 from TIKVAH-MAGAZINE 2023-03-03 13:44:37
Picture 4 from TIKVAH-MAGAZINE 2023-03-03 13:44:37
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፲ኛ ዓመት በዓለ ሲመት ዛሬ ተከብሯል።

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትን 10ኛ ዓመት በዓለ ሢመት ዛሬ የካቲት 24 ቀን 2015 ዓ/ም  በመንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከብሯል።

በትላንትናው ዕለትም ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በማስመልከት ዜና መዋዕል ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክና ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የተሰኙ መጽሐፍት ተመርቀዋል።

መጽሐፍቱ የቅዱስነታቸውን የሕይወት ታሪክ፣ ባለፉት ፲ ዓመታት በሀገር ውስጥና በውጪ ሀገራት ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ሥራዎችን፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎችን፣ ቤተ ክርስቲያን ባለፉት ፲ ዓመታት በስኬት ያከናወነቻቸው ዋና ዋና ተግባራት እና የገጠሟትን ተግዳሮቶች ተከትሎ በቅዱስ ፓትርያርኩ የተላለፉ መልዕክታትን አጠቃሎ የያዘ መሆኑ ተገልጿል።

መጻሕፍቱን በውጪው ዓለም የሚገኙ ምዕመናን  በቀላሉ አግኝተው ማንበብ ይችሉ ዘንድም በቤተ ክርስቲያን ድረ ገጽ https://www.eotceth.org  ላይ እንዲጫን መደረጉን የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አሳውቋል።

ፎቶ: ተሚማ

@tikvahethmagazine
16.5K viewsedited  10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ

ተደጋግመው የሚነሱ ጥያቄዎች

ስለ TIKVAH-MAGAZINE በተደጋጋሚ የሚነሱ ጥያቄዎች

TIKVAH-MAGAZINE 192.64K ተመዝጋቢዎች ያሉት የቴሌግራም ቻናል ነው። በዚህ ገጽ ላይ የቻናሉ መግለጫ፣ ግምገማዎች፣ ደረጃ እና ዝርዝር ስታቲስቲክስ ይገኛሉ።
በዚህ ገጽ ላይ "ወደ ቻናል ይሂዱ" የሚለውን ቁልፍ ይጫኑ ወይም @tikvahethmagazine ን በቴሌግራም መተግበሪያ ውስጥ ይፈልጉ። እንዲሁም የቻናሉን የተጠቃሚ ስም ገልብጠው በቴሌግራም መፈለጊያ ውስጥ መለጠፍ ይችላሉ።
አዎ፣ TIKVAH-MAGAZINE ነፃ የቴሌግራም ቻናል ነው። ሁሉንም ልጥፎች ያለምንም ክፍያ መከታተል እና ማንበብ ይችላሉ።
የTIKVAH-MAGAZINE ቻናል በአሁኑ ጊዜ 192.64K ተመዝጋቢዎች አሉት። የተመዝጋቢዎች ቁጥር በመደበኛነት ይዘመናል።
TIKVAH-MAGAZINE ይዘቱን በዋናነት በአማርኛ ቋንቋ ያትማል። መልእክቶቹን ለማንበብ በዚህ ገጽ ላይ ባለው ማገናኛ ቻናሉን በቴሌግራም ይክፈቱ።
አዎ፣ ተመሳሳይ የዜና ቻናሎችን ከታች "ተመሳሳይ ቻናሎች" በሚለው ክፍል ውስጥ ማግኘት ይችላሉ። ተዛማጅ የቴሌግራም ቡድኖችን፣ ቦቶችን እና ተለጣፊዎችንም እናሳያለን።
መልእክቶቹ በቴሌግራም ውስጥ ይነበባሉ፦ በዚህ ገጽ ላይ ባለው ማገናኛ TIKVAH-MAGAZINE ን ይክፈቱ። በዚህ ገጽ ላይ የቻናሉ መግለጫ፣ የተመዝጋቢዎች ብዛት፣ ግምገማዎች እና ስታቲስቲክስ ያገኛሉ።
TIKVAH-MAGAZINE avatar
TIKVAH-MAGAZINE @tikvahethmagazine
በቴሌግራም ይክፈቱ