Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Choleraupdate
Silver
Platinum
Golden
Naturaldisaster
Alert
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.58K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 249

2022-05-18 15:11:58 #Update : በኢድ- አልፈጥር በዓል ላይ የጭስ ቦንብ በማፈንዳት ወንጀል የተጠረጠረው የፖሊስ አባል ፍርድ ቤት ቀረበ። የፌደራል ፖሊስ አድማ ብተና ዘርፍ አባል የሆነው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ ከትናንት በስቲያ ሰኞ በአዲስ አበባ በተከበረው የኢድ- አልፈጥር በዓል ላይ በመስቀል አደባባይ የሰማዓታት መታሰቢያ ሙዚየም አካባቢ ከፈነዳው የአድማ በታጭ የጭስ ቦንብ ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ስር ውሎ በፌደራል…
18.8K viewsedited  12:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 13:06:49
በሚቀጥሉት ሦስት ወራት 150 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ከውጭ እንዲገባ ተወስኗል።

መንግስት በሰጠው አቅጣጫና የሀገሪቱ ብሄራዊ ማክሮ ኢኮኖሚ ቡድን በወሰነው መሰረት የኑሮ ውድነትን ለማሻሻልና ገበያውን ለማረጋጋ በሚቀጥሉት ሶስት ወራት 150 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ከውጭ እንዲገባ መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

በአሁኑ ጊዜም 12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ እየገባ ነው። ከዚህ ውስጥ 4 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሊትር ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ ለህብረተሰቡ እየተከፋፋለ ሲሆን 7 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሊትር ዘይት ደግሞ በሚቀጥሉት ሶስት ሳምንታት ውስጥ ተጠቃሎ እንደሚገባ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ አስረድተዋል፡፡

ድፍድፍ ዘይት ከውጭ አስመጥተው በሀገር ውስጥ ለሚያመርቱ ሶስት ፋብሪካዎችም ምርቶቻቸውን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ የውጭ ምንዛሬ የተመቻቻላቸው ሲሆን የምግብ ዘይት እጥረትን ለዘላቂነት ለመፍታትም ለሌሎች አቅራቢዎችም ዘይት ከውጭ አስመጥተው ለመንግስት እንዲሸጡ ፈቃድ የተሰጣቸው መሆኑንም ተገልጿል፡፡

መንግስት ባለፉት ሁለትና ሶስት አመታት የምግብ ዘይት ከቀረጥ ነጻ እንዲገባ በማድረጉ 23 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ያጣ ሲሆን ለነዳጅ የ100 ቢሊዮን ብር ድጎማ ማድረጉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

@tikvahethmagazine
21.6K viewsedited  10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 12:58:40
የአዲስ አበባ ከተማ ሕንፃዎች ቀለም ግራጫ እንዲሆን ተወሰነ።

በከተማው ለሚገኙ ሕንፃዎች ቀለማቸው ወጥ የሆነ ስታንዳርድ ለማዘጋጀት ላለፈው አንድ ወር ጥናት ሲደረግ ቆይቶ አብዛኞቹ ሕንፃዎች ቀለማቸው ግራጫ ቀለም ያላቸው መሆኑን የከተማዋ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ቢሮ ኃላፊ አቶ ስጦታው አካለ (ኢንጂነር) ለሪፖርተር ተናግረዋል።

ቂርቆስ ክፍለ ከተማን ለማሳያነት የጠቀሱት ኃላፊው፣ በቂርቆስ ከ100 ሕንፃዎች ውስጥ ከ30 እስከ 40 በመቶ የሚሆኑት ሕንፃዎች ቀለም ግራጫ ነው ብለዋል፡፡ ከእዚህ ውጪ ያሉት ቀለሞች አነስተኛ ቁጥር ያላቸውና የተለያዩ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡

‹‹መሬት ላይ የሌለ አዲስ ቀለም ብናስቀምጥ የተሠሩት ሁሉም ሕንፃዎች እንደ ገና [ቀለም] ሊቀይሩ ነው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ዋነኛው የትኛው ቀለም ነው የሚለውን ወስደን ቀሪዎቹ ሕንፃዎችና ወደፊትም የሚሠሩት በተመሳሳይ ግራጫ እንዲሆኑ ወስነናል፤›› ሲሉ ለከተማዋ ሕንፃዎች ግራጫ የተመረጠበትን ምክንያት አስረድተዋል፡፡

ግራጫ ቀለም ሲወሰን ሁሉም ሕንፃዎች ሙሉ ለሙሉ ተመሳሳይ ቀለም ይኖራቸዋል ማለት እንዳልሆነ የሚናገሩት ኃላፊው፣ እስከ 30 የሚደርሱ በኮድ የሚለያዩ የግራጫ ቀለም ዓይነቶች እንዳሉና የሕንፃ ባለቤቶች ከእነዚህ ውስጥ መምረጥ እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡ በዚህም መሠረት ከግራጫ ቀለም ዓይነቶች ውስጥ የማይካተት ቀለም የተቀቡ ሕንፃዎች በሙሉ፣ ቀለማቸውን በግራጫ ቀለም አማራጮች እንደሚቀይሩ አስረድተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ለከተማዋ ሕንፃዎች የቀለም ስታንዳርድ ተግባራዊ የማድረግን ሐሳብ ከሳምንታት በፊት በተደረገው የከተማ አስተዳደሩ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ላይ አንስተው ነበር፡፡

Read more https://telegra.ph/ሪፖርተር-05-18

@tikvahethmagazine
19.6K viewsedited  09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 12:56:40
ባልታወቀ ምክንያት የተቋረጠው ከአርባምንጭ -ሻሸመኔ የትራንስፖርት አገልግሎት ከሰኔ 1 ጀምሮ ይቀጥላል ተባለ።

ባልታወቀ ምክንያት ተቋርጦ እንደነበር የተገለጸው ከአርባምንጭ -ሻሸመኔ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ለማስጀመር የምዕራብ አርሲ እና የጋሞ ዞኖች ከስምምነት መድረሳቸው ተነግሯል።

ቴክኒካል በሆኑ ጉዳዮች ከባለድርሻ አካላት ጋር በሰፊው በመወያየት ከሰኔ 1/2014 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎቱ ይጀምራል ሲሉ የምዕራብ አርሲ ዞን ትራንስፖርት ኤጀንሲ ተወካይ እና የትራንስፖርት አገልግሎት አቅርቦት ማረጋገጫ ሥራ ሂደት ባለቤት አቶ ትቤሶ ሎሎ ተናግረዋል።

የጋሞ ዞን ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት መምሪያ ምክትል ኃላፊና የትራንስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሣይ ካሎሴ ከአርባምንጭ ወደ ሻሸመኔ የሚደረግ ከፍተኛ ፍላጎትና ፍሰት ያለው አካባቢ መሆኑን አስታውሰው የዞኑ መንግስት እንዲጀመር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ገልጸዋል።

@tikvahethmagazine
18.1K viewsedited  09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 12:56:27
p.s5
p s4
ps3
laptop
0911061990/ 0947152583

ይዘዙን ያሉበት ድረስ እናመጣለን

Merkato near to yergahaile
join @gamerszone1
17.4K views09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 12:56:27
የአንፖል ካሜራ lamp camera

በከፍተኛ ጥራት የሚቀርፅ Full HD ካሜራ የተገጠመለት የአንፖል ከስልኮ ጋ በ app በማገናኘት ማንኛውንም አይነት ክትትል የሚያደርጉበት የአንፖል መሰኪያ ላይ በመግጠም ብቻ ማንኛውንም እንቅስቃሴ የሚቃኙበት ለሱቅ፣ ለቤት፣ የልጆችዎን እንቅስቃሴ ያለሃሳብ የሚቃኙበት እንዲሁም አካባቢዎን ከስርቆት የሚከላከሉበት የራሱ ሳውንድ ሪከርድ እንዲሁም ሚሞሪ የሚቀበል በመሆኑ ተመራጭ ያደርገዋል።

ዋጋውን ዋጋውን እና ሙሉ መረጃውን ከታች ባስቀመጥነው ሊንክ ገብተው ይመልከቱ

https://t.me/joinchat/Um_xfu9NW05k6L77
https://t.me/joinchat/Um_xfu9NW05k6L77

አድራሻ፦ ልደታ ፌዛክ የገበያ ማእከል 1ኛ ፎቅ ላይ
ስልክ:- 0913979989 0900664655

 Inbox @Tebe_mart09    
21.0K views09:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 20:05:04
በመጀመሪያ ዕጣ ሰባት ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው የልዩ -2 ሎተሪ አጣ ዛሬ ወጥቷል።

የልዩ -2 ሎተሪ ዛሬ በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆኗል።

1ኛ. 7,000,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 0759162

2ኛ. 3,000,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0134613

3ኛ.1,000,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0299997

4ኛ. 400,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1037132

5ኛ. 100,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 0530065

6ኛ. 50,000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 0516747

7ኛ. 30,000 ብር የሚያስገኘው የ7ኛ ዕጣ ቁጥር 1185534

8ኛ. 12 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 01329

9ኛ.12 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 31649

10ኛ. 12 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 400 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 02455

11ኛ. 120 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 120 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 4335

12ኛ. 120 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 0652

13ኛ. 1,200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 768

14ኛ. 12,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 60 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 50

15ኛ. 120,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 40 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 6 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡

@tikvahethmagazine
29.9K viewsedited  17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 17:53:25
በቦረና ከ165ሺህ ኪ.ግ በላይ የሚመዝን አደንዛዥ ዕጽ በቁጥጥር ስር ዋለ

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የሚኦ ወረዳ ፖሊስ ከ165 ሺህ ኪ.ግ በላይ ካናቢስ የተሰኘ አደንዛዥ እጽ በቁጥጥር ስር መዋሉን የወረዳዉ ፖሊስ የወንጀል መከላከል እና ፀጥታ ማስከበር ዲቪዥን ሃላፊ ዋና ሳጅን ሮባ ገልገሎ ተናግረዋል ፡፡

አደንዛዥ ዕፁ በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለው በኬንያ በኩል ለማስወጣት ከ አራት ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ገንዘብ ለገበያ ለማቅረብም አዘዋዋሪዎቹ ስምምነት ላይ ደርሰው እንደነበረም ተገልጿል፡፡

በቁጥጥር ስር የዋለው አንድ መቶ ስልሳ አራት ሺህ በላይ የሚመዝነው ካናቢስ የተባለው አደንዛዥ እጽ በጸጥታ አካላት እንዲቃጠል መደረጉን ብስራት ሬድዮ ዘግቧል፡፡

@tikvahethmagazine
27.6K viewsedited  14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 16:28:16
አንዲት እናት እያዋለደች ባለበት ሰዓት በባሏ በጩቤ ተወግታ የተገደለችው የጤና ባለሞያ

በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በዳዳ ሳታላይት ጤና ጣቢያ አዋላጅ ነርስ የነበረችው ሲ/ር ሲ/ር አማረች ዋዳ በምትሰራበት ቦታ በባሏ በጩቤ ተወግታ ህይወቷ አልፏል።

ድርጊቱ የተፈጸመው ግንቦት 5 ዕለት ከጧቱ 3:00 ሰዓት ላይ አንዲት እናት እያዋለደች እንዳለ ሲሆን ገዳይ በጩቤ 5 ቦታ በመውጋት ህይወቷ እንዲያልፍ ማድረጉን ፖሊስ አስታውቋል።

ከወረዳው ኮሚውኒኬሽን ቢሮ በተገኘው መረጃ መሰረት ሲ/ር አማረች ከገዳይ ባሏ ሁለት ልጆች የወለደች ሲሆን የአንድ ወንድና የአንድ ሴት እናት ነበረች።

ገዳይ በሰዓቱ በህግ ቁጥጥር ውሎ ምርመራ እየተካሄደ ሲሆን መረጃው ተጣርቶ የህግ እርምጃ ሲወሰድ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

@tikvahethmagazine
25.9K viewsedited  13:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 16:07:46
የጎጃም ባህል ማዕከል ግንባታ አፈጻጸም 41 በመቶ መድረሱን የምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር ገለጸ።

በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ማርቆስ ከተማ ላይ በመገንባት የሚገኘው የጎጃም ባህል ማዕከል ግንባታ አፈጻጸም 41 በመቶ መድረሱን የምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር ገልጿል።

የባህል ማዕከሉ ዘመናዊ የመሰብሰቢያ አዳራሽ፣ ሙዚየም፣ ቤተ መፅሀፍትና ሌሎች ቢሮዎችን ያካተተ መሆኑንና ከተማዋን የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ጠቀሜታ እንዳለው የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አያሌው ተናግረዋል።

በአማራ ህንፃ ስራዎች ተቋራጭነት እየተገነባ የሚገኘው ይህ የባህል ማዕከል የግንባታ ጥራቱን በጠበቀና በተገቢው የውል ስምምነት ጊዜ ለማጠናቀቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የድርጅቱ የጎጃም በህል ማዕከል አሰሪ መሀንዲስ አቶ ሰለሞን ቸኮል ተናግረዋል።

መረጃው የክልሉ ኮሚውኒኬሽን ቢሮ ነው።

@tikvahethmagazine
24.0K viewsedited  13:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ