-የም/ቤት አባላትን ጨምሮ ማንነትን መሰረት ያደረገ እስር ተፈጽሟል። አቶ ክርስቲያን ታደለ 1 አመት ለሚሞላ ጊዜ ታስረዋል። አቶ ታዬ ደንድዓ ፣ ዩሃንስ ቧያለዉ እና ዶ/ር ካሳ ተሻገር ለዉጡ ስህተት ፈጽሟል በማለታቸዉ በመሞገታቸዉ ብቻ ለወራት ታስረዉ ይገኛሉ። ሀብታሙ በላይነህ የተሰኘ የፌደሬሽን ም/ቤት እና የአማራ ክልል ም/ቤት አባል ሲሆን ላለፉት አራት ወራት የት እንደገባ አይታወቅም። ለመንግስት ሃላፊዎች አቤት ብንልም ምላሽ አላገኘንም። ምላሽ ይስጡን?
- በአማራ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቢጠናቀቅም በኮማንድ ፖስት እየተዳደረ ነዉ።የጅምላ እስር እየተፈጸመ ነዉ።
-መንግስት በህዝቡ ዘንድ እምነት አልገነባም ይህም የሰብዓዊ መብት ጥሰትን ተከትሎ ነዉ። ባለፉት 10 ወራት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ሰበብ በማድረግ የመንግስት ሀይሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና የጅምላ ግድያን ፈጽመዋል። በመርዓዊ ፣ በደብረ ኤሊያስ ፣ ጅጋ ፣ ፍኖተሰላም ፣ ሰሜን ሸዋ ፣ ጎንደርና ወሎ የጅምላ ግድያዎች ተፈጽመዋል። ጾታዊ ጥቃት ፣ ድብደባ ፣ ዘረፋ እና ንብረት ማዉደምም ተፈጽሟል። እምነት ለመገንባት መንግስት ምን እቅድ አለዉ?
#ዳጉ_ጆርናል