Get Mystery Box with random crypto!

HabeshaNet.

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiocoronainfo — HabeshaNet. H
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiocoronainfo — HabeshaNet.
የሰርጥ አድራሻ: @ethiocoronainfo
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 1.69K
የሰርጥ መግለጫ

We will provide Coronavirus updates about Ethiopia and the globe!
ይደግፉን | ያስተዋውቁን!
For any questions contact us http://t.me/EthioCoronavirusInfobot
https://www.youtube.com/c/TheNewEthiopiaTube?sub_confirmation=1

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2021-04-15 22:09:35
1.8K views19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-15 13:38:42
የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር የሕዳሴ ውዝግብን ለመፍታት ለአስቸኳይ ስብሰባ ጥሪ አደረጉ የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ውዝግብን ለመፍታት አስቸኳይ ስብሰባ እንዲደረግ ለግብጽና ለኢትዮጵያ መሪዎች ጥሪ አደረጉ።

ለዓመታት ሲካሄድ የነበረው የሕዳሴ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር በኮንጎዋ መዲና ኪንሻሳ ውጤታማ አለመሆኑን ተከትሎ ይህ ውይይት የመጨረሻ ሙከራ ሊሆን ይችላል ተብሏል።

በኪንሻሳ ላይ ሱዳን እና ግብጽ የሕዳሴ ግድብ ድርድር ታዛቢዎችን ሚና ለመቀየርና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሕብረት በአደራዳሪነት እንዲገቡ ሃሳብ ቢያቀርቡም ኢትዮጵያ አልተቀበለችውም።

ኢትዮጵያ ድርድሩ በአፍሪካ ሕብረት ጥላ ስር እንዲሆን ትፈልጋለች።

ይህንን የኢትዮጵያ ሃሳብም ሰሞኑን ሩሲያ እንደምትደግፈው የተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ሩሲያ የሕዳሴ ግድብ ውዝግብ በአፍሪካ ሕብረት ጥላ ስር እንዲፈታ ፍላጎት አላት በማለት የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ተናግረዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህንን ንግግር ያደረጉት በካይሮዋ መዲና ከግብጹ አቻቸው ሳሜ ሽኩሪ ጋር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሆነ ተዘግቧል።
1.6K views10:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-15 09:48:21
የ20 አመቱን ጥቁር አሜሪካዊ የተኮሰችበት ፖሊስ በግድያ ወንጀል ተከሰሰች በሚኒሶታ አንድ ጥቁር አሽከርካሪን በጥይት የገደለችው ነጭ የቀድሞ የፖሊስ መኮንን በሁለተኛ ደረጃ የመግደል ወንጀል ክስ እንደተመሠረተባት አቃቤ ህግ ገለጸ፡፡

ኪም ፖተር በቁጥጥር ስር የዋለች ቢሆንም በኋላ ግን በ 100,000 ዶላር ዋስ ተለቃለች፡፡

ፖተር በስህተት ማደንዘዣ መስሏት ሽጉጧን በመምዘዝ ዳውንት ራይት ላይ መተኮሷን ፖሊስ ገለጿል፡፡

የራይት ቤተሰብ ጠበቃ ቤን ክራምፕ በበኩላቸው ግድያው "ሆን ተብሎ እና ህገ-ወጥ የኃይል እርምጃ በመጠቀም የተፈጸመ ነው" ብለዋል፡፡

ክስተቱን ተከትሎ ኪም ፖተርም እና የአከባቢው የፖሊስ አዛዥ ቲም ጋኖን ሥራቸውን ለቀዋል፡፡
1.1K views06:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-15 09:29:54
ግማሽ ያህል የምርጫ ጣቢያዎች አልተከፈቱም፣ በአፋርና በሶማሌ ምዝገባ አልተጀመረም ሊካሄድ ሰባት ሳምንት ብቻ በቀረው ስድስተኛው አገራዊና ክልላዊ ምርጫ ላይ የመራጮች ምዝገባ ይካሄድባቸዋል ከተባሉት የምርጫ ጣቢያዎች ወደ ግማሽ የሚጠጉት አለመከፈታቸውን የምርጫ ቦርድ ገለጸ።

የመራጮች ምዝገባ ከተጀመረ ከሦስት ሳምንት በላይ ሲሆነው በተለያዩ ክልሎች ውስጥ ተከፍተው ድምጽ ሰጪዎችን ይመዘግባሉ ተብለው ከታቀዱት 50 ሺህ ያህል የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ በአሁኑ ጊዜ ምዝገባ እያካሄዱ ያሉት 25 ሺህ 151ዱ ሲሆኑ ከ24 ሺህ በላይ የሚሆኑት ግን ሥራ አልጀመሩም።
949 views06:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-14 11:38:08 HabeshaNet. pinned a photo
08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-14 10:45:44 በአማራ ክልል የተፈናቃዮች ቁጥር እያሻቀበ መምጣቱ ተነገረ፡፡

የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮምሽን እንዳለው፣ ከተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በተለይም ከኦሮሚያ እና ከቤኒሻንጉል ክልል ተፈናቅለው ወደ ክልሉ የሚመጡ ተፈናቃዮች ቁጥር በየጊዜው በእጅጉ እየጨመረ ነው፡፡

የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮምሽን ኮምሽነር አቶ ዘላለም ልጅአለም ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቁት፣ በ አሁኑ ሰዓት በክልሉ 4 መቶ 95 ሺህ የሚሆኑ ተፈናቃዮች ይገኛሉ፡፡

እነዚህ ተፈናቃዮች በአብዛኛው ኦሮሚያና ቤኒሻንጉልን ጨምሮ ከትግራይ እና ከደቡብ ክልል በተለያዩ ምክንያቶች የተፈናቀሉ መሆናቸውን ነግረውናል፡፡

አብዛኛው ተፈናቃይ ማህረሰቡ ውስጥ አብሮ ይገኛል ያሉን ኮምሽነር ዘላለም፣ በተጨማሪም ቻግኒ፤ሰሜን ወሎ፤ ደቡብ ወሎ እና ጎንደር በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች ተጠልለው እንደሚገኙም ነግረውናል፡፡

እነዚህን ተፈናቃዮች የሚደግፍ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም፣ በማንነታቸው ምክንያት ከቀያቸው ቤት ንብረታቸውን ጥለው የመጡ ዜጎች ወደ ቀደመ ቀያቸው መመለስ እንዳለባቸው ክልሉ እንደሚያምን ነው የነገሩን፡፡

በተለይም ወደ ቀደመ ቀያቸው እንዲመለሱ የማድረጉ ስራ መንግስትና በተለይም የመጡበት ክልል ከፍተኛ ሃላፊነት ሊወስድና መልክ ማሲያዝ እንዳለበትም አስታውቀዋል፡፡

በየዉልሰዉ ገዝሙ
ሚያዝያ 06 ቀን 2013 ዓ.ም
905 views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-14 10:44:53 92 ኢትዮጵያውያን ከየመን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡

በዛሬዉ እለት 92 ኢትዮጵያውያን ከየመን ወደ አገራቸው መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡

በየመን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ለመመለስ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ከኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀን የተውጣጣ የልዑካን ቡድን ወደ ኤደን በመሄድ የሊሴ ፓሴ የመስጠት ስራ አከናውኗል።

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት መረጃ እንዳመለከተዉ ኢትዮጵያዊያኑ ወደ ሀገራቸዉ እንዲመለሱ የተደረገዉ ከዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) ጋር በመተባበር ነዉ፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጄኔራል ተወካይ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ተገኝተው ለተመላሾቹ አቀባበል እንዳደረጉላቸዉም ተገልጿል።


ኢትዮ ኤፍ ኤም
904 views07:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-14 10:29:17
ሱዳን ከያዘቻቸው ግዛቶች ወታደሮቿን እንድታስወጣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጫና እንዲያደርግ ኢትዮጵያ ጥሪ አቅርባለች። @ETHIOID
890 views07:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-18 18:14:21 የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዛሬ ሴናተር ክሪስ ኩንስን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚልኩ ፎሬን ፖሊሲ መጽሄት ዘግቧል፡፡ መልዕክተኛው የተላኩት ስለ ትግራዩ ግጭት ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ እና ከአፍሪካ ኅብረት ሃላፊዎች ጋር ለመነጋገር እና ፕሬዝዳንቱ ስለ ትግራዩ ግጭት የገባቸውን ስጋት ለማስረዳት እና መፍትሄ እንዲፈለግ ለመገፋፋት እንደሆነ ኩንስ ለመጽሄቱ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር የገባችበትን የድንበር ውዝግብ እንድትፈታም የመገፋፋት ተልዕኮ አላቸው ተብሏል፡፡ ኩንስ በአሜሪካ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ አባል እና የውጭ ዕርዳታን የሚቆጣጠረው ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው፡፡

[Wazema]


@ethiocoronainfo
1.4K viewsedited  15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-08-27 17:12:20 የትምህርት ዕድል (ስኮላርሽፕ) ዕድሎችን ይፈልጋሉ?|Are you looking for a scholarship opportunity?

ይደግፉን SHARE በማድረግ ያስተዋውቁን!

አገር አቀፍ እና አለም አቀፍ የስራ እና የትምህርት እድሎች ፣ ሙሉ ወጪያቸው የተሸፈኑ ኮንፍረንሶች ፣ ልምድ ልዉዉጦች ፤ ስልጠናዎች፣ እንዲሁም የስራ ፈጠራ ውድድር እድሎች ፤ ሁሉም በአንድ የሚገኝበት ቦታ ለወጣቶች።

We are #ethio-scholarships
Join us #ethio-scholarships

T.me/schol76

ይደግፉን SHARE በማድረግ ያስተዋውቁን!
3.7K views14:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ