Get Mystery Box with random crypto!

መረጃ ቲቪ🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ merejatvethiopia16 — መረጃ ቲቪ🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ merejatvethiopia16 — መረጃ ቲቪ🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @merejatvethiopia16
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.62K
የሰርጥ መግለጫ

ωєℓ¢¢σмє тσ Mereja TV™🇪🇹
✅ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናላችን ነው
➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ፣
➠ የስፓርት እና መዝናኛ ዘገባዎች፣
➠ የአለም ሙሉ መረጃና የታሪክ መዛግብቶች ።
መረጃ ቲቪ -Mereja TV Satellite Eutelsat 8 West B Frequency 11637 / 11636 Symbol Rate 27500 5/6
🎬 "ተመራጭ የዜና ምንጭ"
@meraja_tv

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-03-11 12:18:37
"…በእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ኃይል አለ ለእርሱ ምክርና ማስተዋል አለው። እነሆ፥ ይፈርሳል፥ የፈረሰውም ተመልሶ አይሠራም፤ በሰውም ቢዘጋበት የሚከፍትለት የለም። እነሆ፥ ውኆቹን ይከለክላል፥ እነርሱም ይደርቃሉ፤ እንደ ገና ይሰድዳቸዋል፥ ምድሪቱንም ይገለብጣሉ። ኃይልና ጥበብ በእርሱ ዘንድ ናቸው የሚስተውና የሚያስተው ለእርሱ ናቸው።

"…መካሮችንም እንደ ዘረፋ ይወስዳቸዋል፥ ፈራጆችንም ያሳብዳል። የነገሥታትንም እስራት ይፈታል፥ ወገባቸውንም በመታጠቂያ ያስራቸዋል። ካህናትን እንደ ዘረፋ ይወስዳቸዋል፥ ኃያላንንም ይገለብጣቸዋል። ከታመኑ ሰዎችም ቋንቋን ያርቃል፥ የሽማግሌዎችንም ማስተዋል ይወስድባቸዋል።በአለቆች ላይ ንቀትን ያፈስሳል፥ የብርቱዎችንም መታጠቂያ ያላላል።ጥልቅ ነገር ከጨለማ ይገልጣል፥ የሞትንም ጥላ ወደ ብርሃን ያወጣል።

"…አሕዛብን ከፍ ከፍ ያደርጋል፥ እነርሱንም ያጠፋል፤ አሕዛብንም ያሰፋል፥ እነርሱንም ያፈልሳቸዋል። ከምድር አሕዛብ አለቆች ዘንድ ማስተዋልን ይወስዳል፥ መንገድም በሌለበት በረሃ ያቅበዘብዛቸዋል። ብርሃንም ሳይኖር በጨለማ ይርመሰመሳሉ እንደ ሰካራም ይቅበዘበዛሉ።" ኢዮ 12፥ 13-25


"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?

"… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ
175 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:18:32
"…ኣ… ላችሁ…  አይደል…?

http://tiktok.com/@zemedkun.b

• ባጃጅ አጥቼ ነው። እየመጣሁ ነው ጠብቁኝ…!
114 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:18:32
"…አዛኜን ደክሞኛል… ነገር ግን ምን ቢደክመኝ የእናንተም ውትወታ ታክሎበት በዚያውም የዕለተ አርብ ልማዳችን እንዳይቀር እንደተለመደው በቃ በቲክቶክ መንደሬ ከ10 ደቂቃ በኋላ እንደ ቲክቶክ አንበሳ እያገሳሁ እመጣለሁ እና ጠብቁኝ።

http://tiktok.com/@zemedkun.b

"…ኣ… ላችሁ… አይደል…?
109 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:18:31
አጀንዳዬን አልቀይርም…!

"…በሻሸመኔ ከተማ የከተማው ከንቲባ እና ካቢኔው ባሰማሩት ፅንፈኛ የኦሮሞ የወሃቢይ እስላም ቄሮዎችና ፖሊሶች በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ከርስቲያን ውስጥ በገጀራ፣ በድንጋይ፣ በዱላ ተቀጥቀጠው በሰማእትነት አርፈዋል። የእኛን ካህን ከገደሉ በኋላም በገንዘባቸው የሾሙትን የጨረቃ ጳጳስ አጅበው በየቦታው በሬ አሸክመው "አላህ ወአክበር" እያሉ በመዞር ላይ ናቸው።

"…የካህኑ ባለቤት ከነ ሁለት መንታ ልጆቿ በችግር ላይ እንዳትወድቅ በሃገረ አሜሪካ የሚኖሩ መንፈሳውያን ቤተሰቦች ሁሉን ነገር ሊያሟሉና ተንከባክበው ሊያሳድጉ ቃልገብተዋል። እግዚአብሔር ይምስገን።

"…በሉ ቀሪ የተጎዱ ወንድም እህቶቻችን ቁስል ላይ ዘይት እናፍሰን ደስም እናሰኛቸው። አዎ ከአህዛብ ጭፈጨፋ በተአምር የተረፉትን ቁስለኛ ባለማዕተብ ወገኖቻችንን እናሳክም እንርዳቸውም።

• https://gofund.me/9f5c8ff8

• BE E/O/B/K BESHASHEMENE
   K/TEGOJIWOCH ~
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦          1000525914619

• የምትሰጡ በደስታ ስጡ…!
93 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:18:31
አንዳንድ ሰዎች…!

"…አዎ አንዳንድ ሰዎች በብዙ እርዳታ ጠያቂዎች ተወጠርን እኮ። ለየትኛው እንሁን? አሁንስ ግራገባን ስትሉ እሰማለሁ።

"…የእኔ መልስ ለለመናችሁ ሁሉ ስጡ። የምትሰጡት ከሰጣችሁ መልሳችሁ ስጡ። እኛ ለማኞቹ ለእናንተ ለሰጪዎቹ የልመና ፕሮጀክታችንን ቀርጸን አቅርበናል። ሁሉም ለማኝ የሚለምነው ጎደለኝ ብሎ ነው። የጎደለውን ዓይታችሁ ባቀረበው ፕሮጀክት መሠረት ካላችሁ መስጠት የእናንተ ፈንታ ነው።

"…ስለ ዓይነ ብርሃን የሚል ዓይነ ሥውር፣ እጅ እግር ያጣ የኔቢጤ፣ በሽታ ያደቀቀው ለማኝ ሁላቸውም ለማኝ ናቸው። በዜማ የሚለምን አለ። በባን የሚለምን አለ። ዝም ብሎ ተቀምጦ የሚለምንም አለ። እንደ እኔ መራታም ደግሞ አለ በኪሳችሁ ውስጥ ብር ያስቀመጠ ይመስል ነፍሴ የማትፈልገው 100 ብር ካለህ ወዲህበል የሚል ገገማም አለ። ብቻ ሁሉም ለማኝ ነው።

"…በነገራችን ላይ አጭበርባሪ ከማኝም አለ። ኖራ ተለቅልቆ የቆዳ በሽታ ያዘኝ ብሎ የሚቀፍል ጤነኛ የሆነ አጭበርባሪ ለማኝም አለ። ሳይታወር እውር የሚመስል፣ ሳይሰበር በዊልቸር፣ በክራንች የሚሄድ፣ ልመናን እንጀራው ያደረገም ለማኝ አለ። ሁሉም ለማኝ ቸግሮት ነው ማለት አይቻልም። ደኅና እየኖረው ልመና ሱስ የሆነበትም እንዳለ ነው የምሰማው።

"…ዋናው ነገር ያቀረብነውን የልመና ፕሮጀክት ማየት ነው። የእኔ የልመና ፕሮጀክት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሰብረው እንገባለን ያሉ አህዛቦችን አትገቡም በማለታቸው በመንግሥትና በኦሮሞ ጽንፈኞች ገሚሶቹ ታርደው፣ ገሚሶቹ ተጨፍጭፈው የአልጋ ቁራኛ ለሆኑት የሻሸመኔ ከተማ ባለማዕተብ ክርስቲያኖች ነው።

በማርያም…!
በቅዱስ ሚካአል…!

"…ማርያምን ተጎጂዎቹን አንዳቸውንም አላውቃቸውም። እመቤቴን።
80 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:18:31
84 ሺ ደርሰናል…!

"…817 ደጋግ ኢትዮጵያውያን ያላቸውን ለግሰዋል። 8 ሺ ቀጸላ ጊዮርጊስ 2ሺ ወለተ ሊባኖስ ለአስቸኳይ ፈጥኖ ደራሽ በቀጥታ ስለላኩ 94 ሺ ዶላር በሉት። የምፈልገውን ግማሹን ደርሻለሁ። ሆኖም መወትወቴን አላቋርጥም።

"…በአሜሪካ የሚገኙ፣ በካናዳ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ቢሳተፉ መልካም ነበር። ለሃገር መከላከያ ብለው ለብልጽግና ካድሬ ከሙዳየ ምጽዋት አውጥተው ለገዳዩ መንግሥት ማረጃ የሚሆን ቢለዋ መግዣ የሰጡት የአማሪካና የካናዳ ሊቃነ ጳጳሳቶቻችንም ዝም ጭጭ ብለዋል። ነገ አቁፋዳቸውን ይዘው ለሞርጌጅ መክፈያ ድረሱልን የሚሉ ሁሉ ዛሬ ጭጭ ብለዋል። እኔ ግን ውትወታዬን አላቋርጥም።

"…ሻሸመኔ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለመውደቃችንም፣ ለመነሣታችንም አይነተኛ ማሳያ የሚሆነን ከተማ ነው። በግብር፣ በታክስና በመዋጮ አማርረው፣ በጥይት፣ በገጀራ፣ በክትክታ ዱላ ጨፍጭፈው ሰባብረው ከርስታቸው ለማባረር፣ ለማፈናቀልም ፖሊሲ ቀርፀው የሚጥሩትን ጥረት ያየ ከሻሸመኔዎች ጋር በጽናት ይቆም ነበር።

"…እኔም ይሄን አሳክቼ በተጎጂ ወንድም እህቶቼ ቁስል ላይዘይት አፍስሼ ደስ እስካሰኛቸው ድረስ መወትወቴን አላቆምም። ለዚህ ነው ከአህዛብ ጭፈጨፋ የተረፉትን ቁስለኞች እናሳክም እንርዳቸው የምላችሁ።

• https://gofund.me/9f5c8ff8

• BE E/O/B/K BESHASHEMENE K/TEGOJIWOCH የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000525914619

• የምትሰጡ በደስታ ስጡ…!
63 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:18:31
ተመዝግቦ ይቀመጥ…!

"…በሰውበሰው ተጫኔ (ዘሪሁን ሙላት) እና በዋሲሁን ኦዳ ባንክ አርክቴክትነት፣ በዳንኤል ክስረት አማካሪነት፣ በአረመኔዎቹ አቢይ አሕመድና በሽመልስ አብዲሳ ትእዛዝ፣ በሳዊሮስ፣ ኤውስጣቴዎስና ዜናማርቆስ ቡራኬ፣ በኃይለሚካኤል አዝማችነት፣ በኦሮሞ ጽንፈኛ የወሀቢ እስላሞችና በኦሮሞና በደቡብ ፅንፈኛ የጴንጤ ባለሃብቶች የገንዘብ ድጋፍ፣ በኦሮሚያ ፖሊስና ሚንሻ፣ በሻሸመኔ ከንቲባና ካቢኔ ፊትአውራሪነት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሰው አያየንም፣ ሕግም አይገዛንም፣ ዘመኑ የእኛ ነው ባሉ ኦሮሞ አስዳቢዎች ባለማዕተቦቹ ሲጨፈጨፉ የሚያሳይ ታሪካዊ ቪድዮ ነው።

"…ይሄን ለልጆቻችሁ አሳዩ፣ በቤት በሰፈራችሁ ምከሩ፣ ተነጋገሩበት፣ ብድር የማይመልስ ባለማዕተብ አይወለድ። በቀል የእግዚአብሔር ነው ሕግ ማስከበር፣ ፍትሕ ማስፈን ግን የሁላችን ድርሻ ነው። ይሄን የጠገበ፣ የፏነነ፣ ለከት ያጣ በኦሮሞ ስም አረመኔያዊ ጭፍጨፋ እየፈጸመ ያለን ነውረኛ ኃይል ልኩን የሚያስገባና ለፍትህ የሚያቀርብ ሥርዓትና ኃይል መፍጠር የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ነው። ብትሸሸው የማይለቅህን፣ ፈንገስ እግሩን ብትልስ የማይምርህን አራጅ ገጥመህ መስዋዕትነት ከፍለህ ካልሸኘኸው በጥይት ረሽኖ፣ በገጀራ በዱላ ጨፍጭፎ፣ በድንጋይ ቀጥቅጦ ያጠፋሃል። በጥይት አልሞት ብትለው ቤትህን አፍርሶ፣ መድረሻ አሳጥቶ፣ ከሥራ አፈናቅሎ፣ ጨርቅህን አስጥሎ አሳብዶ፤ በዚያም አልሞት ብትለው በራብ፣ በጠኔ፣ በችጋር ይፈጅሃል። አይምርህም። ፍቅር ለማያውቅ ሸንጋይ ፍቅር ፍቅር እያልክ አትሟዘዝ።

"…ለዚህ ነው ከጭፈጨፋው የተረፉትን ቁስለኞች እናሳክም እንርዳቸው የምላችሁ።

• https://gofund.me/9f5c8ff8

• BE E/O/B/K BESHASHEMENE K/TEGOJIWOCH የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000525914619

• በደስታ ስጡ…!
56 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:18:31
"ርዕሰ አንቀጽ"

"…ከዛሬ መጋቢት 1/2015 ዓም ጀምሮ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ማለዳ ማለዳ ካሉኝ ጓደኞቼ መካከል 5ሺ ጓደኞቼ ስሙን ጽፈው እግዚአብሔር ይመስገን ካላሉኝ በቀር ወደ ሌላ አጀንዳ አልገባም ማለቴ ይታወሳል። የአመስጋኙን ቁጥርም ከ3ሺ በቀጥታ ወደ 5ሺ ከፍ ያደረግኩት 3ሺው ስላላዋጣኝ ነበር። እያየን ቀስ እያልኩ እጨምራለሁ ብዬ እንጂ ከቦታውም ስለማይመጣ 5ሺውም እንደማያዋጣኝ ራሳችሁ ምስክር ናችሁ።

"…ሰሞኑን የአመስጋኙ ቁጥር እየበዛ በመሄዱ እግዚአብሔር የሚለውን ስም ላለማየት ጥቂት የማይባሉ ሰዎች እኔ ሳላባርራቸው በራሳቸው ፈቃድ ፔጄን ለቀው ውልቅ ስላሉ በዛሬው የመጀመሪያ ቀን ግብይቴማ ብዙዎች ደንግጠው ይጠፋሉ ብዬም አስቤ ነበር። የሆነው ግን በተቃራኒው ነው።

• በ3 ሰዓታት ውስጥ 30ሺ ሰዎች አይተውኝ።
• በ3 ሰዓታት ውስጥ 5ሺ ሰዎች አመስግነዋል።
• መስመር ላይ 12,437 ሰዎች የነበሩ ሲሆን ለክብራቸው፣ ለስማቸው፣ ለማእረጋቸው፣ ለሥልጣናቸው፣ ለዝናቸው፣ ለሃብታቸው ሳይጨነቁ በደስታ እግዚአብሔር ይመስገን ብለው በዓለሙ ሁሉ ፊት የእግዚአብሔርን ስም ጠርተው ያመሰገኑት ግን በቁጥር 5,256 ጓደኞቼ ብቻ ናቸው። ይሄ የአመስጋኝ ቁጥር በአሜሪካና ካናዳ እንቅልፍ ላይ ያሉትን አይጨምርም። እነሱም ገና ሲነጋላቸው ስሙን ያመሰግናሉና።

"…ለአንዳንዶች ሲያዩት ሞኝነት፣ ቂልነት ቢመስልም ለእኔና ለአመስጋኝ ጓደኞቼ ግን በዚህ በሰይጣናዊ አጋንንታዊና ዲያብሎስ በነገሠበት ዓለም የእግዚአብሔርን ስም ጮኽ ብሎ ጠርቶ ማመስገን እንደ ቀላል እንደተራም ነገር አንቆጥረውም። መባረክ መመረጥም ነው እንጂ። 5ሺ ሰው ሳይወድ በግዱ እያፋሸከ፣ እየተንጠራራ እየተነጫነጨም ቢሆን ወይም ደስስ እያለው ፈጣሪን እንዲያመሰግን ማስገደድስ ቀላል ይመስላችኋል እንዴ? ቴርሞ ሜትሪዻ በር…

•ድርጅቱ…!
55 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:18:31
“…ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያው ድረስ የእግዚአብሔር ስም ይመስገን።” መዝ 113፥3።”

"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?

"… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ
51 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 12:18:30
"…እንዲህ እያልን እንጸልይ…!!

"…በሚያስፈልግበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናቡን ያዘንብ ዘንድ ስለ ዝናብ እንማልዳለን። የወንዙን ውኃ ሙላልን ብለን እግዚአብሔር እነሱን እስከ ልካቸውና እስከ ወሰናቸው ይመላ ዘንድ ስለወንዝ እንማልዳለን። ለዘር እና ለመከር ሊሆን እግዚአብሔር ለምድር ፍሬዋን ይሰጣት ዘንድ ስለ ምድር ፍሬ እንማልዳለን፤"

• አሜን…!!
49 views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ