Get Mystery Box with random crypto!

GURAGE KINGDOM

የቴሌግራም ቻናል አርማ selam_zegurage — GURAGE KINGDOM G
የቴሌግራም ቻናል አርማ selam_zegurage — GURAGE KINGDOM
የሰርጥ አድራሻ: @selam_zegurage
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.40K
የሰርጥ መግለጫ

ስለ ሀገራችን ወቅታዊ መረጃ ይወራበታል።
@Kuratinfo21_bot

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 20:37:54
ያለፉት 30 አመታት መንግስት ለጉራጌ ህዝብ
የሚበጅተው ባጀት ከወረዳና ከዞን ተቀጣሪ ሰራተኞች (ካድሬዎች) ደሞዝና አበል ያለፈ ለህዝቡ ጠብ የሚል ነገር ሰርቶ አያውቅም!!
1.1K viewsKurat, 17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 19:13:36
ጉራጌ ሳይማር ኢኮኖሚክስ የገባው ነው። ጉራጌ ገንዘብ መስራት ብቻ ሳይሆን አያያዙንም ያውቅበታል። ጉራጌ ስራ የሚጀምረው ገንዘብ ማስገቢያ ቀዳዳ እንጂ ማውጫ ከሌለው የእንጨት ሳጥን (ባንክ ) ጋር መሆኑን ላየ ጉራጌ ለባንክ ቁጠባን እንደ አስተማረ እንጂ ባንክ ለጉራጌ ቁጠባን እንዳላሰረተማረ ትረዳለህ ።
1.2K viewsKurat, 16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 19:26:59
……ከእንግዲህ የጉራጌ ህዝብ በገዛ ልጆች የሚፈፀምበትን ደባ በማያዳግም መልኩ ማስቆም አለበት። የኛ ጠላቶች እነሱ እንጂ ሌላ አይደለም ። ከመጣ ከሄደው ጋር እየተለጠፉ የጀርባ ቅማል የሆኑብንን ማውረድ ብቻ ሳይሆን ከኛ አርቀን መጣል አለብን። ቢኖሩ አይጠቅሙንን፣ ቢጠፉም አይጎዱንም ። ከተሸከምናቸው ግን ከቻሉ ያጠፉናል ካልሆነም በጅቦች ያስበሉናል።
ስለዚህ ..... ወይ እናጥፋቸው ወይ ያጥፉን!!
1.9K viewsKurat, 16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 19:10:54
☞እውቅና ሳይሰጠው ይኖር ዘንድ የሚወድ የለም፡፡ በጥረታች ዝናችን በዓለሙ ሁሉ ቢናኝም ፤ እጣፈንታችን ግን ያሳስበናል፡፡
እኛ የወደቅንበት ልጆቻችን እንዲደግሙት አንፈቅድም
1.5K viewsKurat, 16:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 17:47:17
በጉራጌ ወጣቶች እስርና ማስፈራራቱ እየበረታ ቢመጣም ቆርጦ የተነሳውን ወጣት ግን ማስቆም አልተቻለም ፣ አይቻልምም!!
እርግጠኛ ሆኜ መናገር የምችለውም ጥያቄውን ሳያስመልስ የሚንበረከክ አንድም የጉራጌ ወጣት እንደማይኖር ነው!
ምክንያቱም ጥያቄያችን የህልውና ነውና ነው! ፔሬድ!!
1.8K viewsKurat, 14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 17:19:28
......#እንዴትስ_ያስችላል? .........
ሶዶ ክስታኔን ገፍቼ ፣ መስቃንን አጥቼ፣
ያለ ዶቢ መኖር ፣ 7ቤቱን ትቼ
ከሆነም ይሆናል ~ ካልሆነም አይሁን
በፍቅር ተዋልዶ ~ በፍቅር የኖረን
በማይጠቅም ሀሳብ ~ መጠላላት ለምን?

ለተጨማሪ ቴሌግራም ቻናላችንን
https://t.me/selam_zegurage ይቀላቀሉ
1.6K viewsKurat, 14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 17:01:40
ጦርነቱን ማን እንደሚጀምረው ባናውቅም ማን ዋጋ እንደሚከፍል እናውቃለን "

በአማራና በትግራይ ህዝቦች መካከል የተፈጠረው ቁርሾ ስልጣን ፈላጊዎች የፈጠሩት እንጂ በህዝቦቹ መካከል ለግጭት የሚዳርግ ምንም ምክንያት እንደሌለ ግልፅ ነው ።
በሁለቱም መካከል የሚሞተው ፣ የሚሰደደው፣ የሚሰቃየው ሚስኪኑ ወገናችን መሆኑ በእውነት ያሳዝናል።
በስልጣን ጥመኞች ምክንያት ታሪካችን በእልቂትና በደም የተጨማለቀ መሆኑ የሚያሳዝን እንጂ የሚያኮራ አይደለም ።

የሚገርመው ምስኪኑን ማግደውና አማግደው ስልጣን ከያዙ ቦኋላ እንኳን ለወገናቸው ከማዘን ይልቅ አፈሙዛቸውን ወደራሱ መልሰው ምስኪኑን ህዝብ እያሰቃዩ እነሱ ጮማ እየቆረጡና ውስኪ እየተራጩ ከመኖር የዘለለ የማይጠቅሙ ከንቱዎች መሆናቸውን ሲታሰብ ያማል።

አማራና ትግራይ የጋራ የሆነ ብዙ ታሪክ ያላቸው መሆኑና የኢትዮጵያ መሰረት መሆናቸውን ካየን በሁለቱ መካከል የሚካሄደው ጦርነት አግባብነቱ በፍፁም አይታየኝም።
ኢትዮጵያን ያለ አማራና ትግራይ ለማየት መሞከር የማይቻል መሆኑ እሙን ነው። ምክንያቱም የኢትዮጵያ መሰረትና ታሪካችን ናቸውና።

ሁለቱም ብዙ የጋራ ታሪክና ማንነት ያላቸው ህዝቦች ከመሆናቸው ባለፈ #የሴም ነገድ አካል መሆናቸው ደግሞ በደምም የተሳሰሩ አንድ ህዝቦች ናቸው ማለት ይቻላል።
በእነዚህ አንድ ታሪክና አንድ ነገድ ባላቸው ህዝቦች መካከል የሚደረግን ጦርነት አለመቃወም ይቻላል ብዬ አላስብም!

በመካከላቸው ችግሮች አይኖሩም ብሎ መናገር ባይቻልም የችግሮቹ ፈጣሪ የስልጣን ጥመኞች እንደሆኑ መረዳትና በሰላማዊ መንገድ ህዝቦቹ መፍታት እንደሚችሉ ማወቅ ይገባል።
ጦርነት መቼም መፍትሄ ሆኖ አያውቅም።
በዝሆኖች ፀብ ደግሞ ተጎጂው ሳሮቹ ናቸውና
ለሳሮቹ እናስብ።

ለተጨማሪ ቴሌግራም ቻናላችንን
https://t.me/selam_zegurage ይቀላቀሉ
1.2K viewsKurat, 14:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 23:16:19
#Nomore ብለን በመነሳት #ንጋታችንን እናብስር!!
ያለፉት 30 አመታት ለጉራጌ ህዝብ የጨለማ አመታቶች ናቸው።
በልማት የተበደልንበት
በኢኮኖሚ የተመታንበት
ከስልጣን የተገፋንበት
ነፃነታችንን የተነፈግንበት
ንብረታችንን የወደመበት
መኖር ተከልክለን የተፈናቀልበት
ህልውናችን አደጋ ውስጥ የወደቀበት
ለጥያቄያችን መልስ ያጣንበት ነው!
አዎ ያለፉትን 30 አመታት ቆም ብለን ካሰብናቸው ለጉራጌው ከጨለማም ጨለማ አመታቶች እንደነበሩ ጨለማ ውስጥ ሆነህም ይታዩሃል።
ይሁንና አሁንም ጨለማ ውስጥ እንዳለንም ማወቀ አለብን።
☆ሳይነጋልን በጨለማ ውስጥ እየዳከርን መኖር ግን የለብንም ። አዎ ለጉራጌው መንጋት አለበት።
በጨለማ ውስጥ የጨለመ ኑሮን መኖር በቃ ማለት ግድ ይለናል።
ለዚህ ደግሞ ግዜው አሁን ነው። ይሄንን ግዜ በአግባቡ ተጠቅመን ንጋትን ካላወጅን እድሜ ልካችንን በጨለማው ውስጥ መኖር እጣ ፋንታችን ሆኖ እንደሚቀር ማወቅ ይገባናል።
☆እኛ በጨለማ ውስጥ መኖራችን ሳያንስ ፣ ለመጪው ትውልድ ጨለማን ልናወርስ ስለማይገባ ሁላችንም #Nomore ብለን በመነሳት ንጋታችንን እናብስር!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ለተጨማሪ መረጃዎች ቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ
☞ https://t.me/selam_zegurage
Share
2.1K viewsKurat, 20:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 20:42:48
#ዋ!!!
የዞን ምክር ቤት ውሳኔ ይከበር
የህዝብ ድምፅ በስልጣን ጥመኞች አይሸጥም/አይለወጥም!!
ይሄንን ለመቀልበስ መንደር ለመንደር የምትዞሩ ስልጣን አምላኪዎች ከድርጊታችሁ ተቆጠቡ።
ያከበራችሁን ህዝብ ማክበር ካልቻላችሁ መልሶ ሲያዋርዳችሁ ስልጣናችሁ አይታደጋችሁምና እረፉ!
ክብር በህዝብ እንጂ በስልጣን አይገኝም!
ህዝቡን ያላከበረ አመራር አይከበርም፣ እኛም አናከብርም!!
1.9K viewsKurat, 17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 17:46:23
1.5K viewsKurat, 14:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ