2022-02-25 19:54:00
የሚባረከው ጦርነት ... የሀበሾችና የራሺያዊያን ወግ ..
ራሺያ ዩክሬይንን ነው የወረረችበት ዋነኛው ምክንያት .. ኔቶ ከሶቬት ህብረት የተገነጠሉ ሀገራትን አባል ማድረግ አይችልም የሚለው ውል አልተከበረም በተደጋጋሚም ተጥሷል ብላ ነው።
ባለፉት አመታት የተፈጠረው የክሬሚያ ቀውስ ሆነ ሌሎች ቀጠናዊ ቀውሶችንም አረሳንም። ከጀርባ ያሉት የዘመናት የፖለቲካ መቃቃሮች እንደተጠበቁ ሆነው።
ራሻያዊያን ትናንት ማታ የሞስኮ አደባባይን ሞልተው ጦርነቱና ወረራው ይቁም ሲሉ ድምፃቸውን አሰምተዋል። በሀበሾች አጠራር .. ጦርነት ያልደገፉ ሰዎች እንደሚጠሩት .."ጁንታ" .. ሆነዋል።
አስቡት ይህ የእርስ በርስ ጦርነት አይደለም። የሁለት ሀገራት ጦርነት ነው .. መነሻውም ከበላይነት ጥቅምን ከማስከበር ፣ ደህንነትን ከማረጋገጥ አንፃር ልናየው እንችላለን።
ይህ ግን በሀገራቸው ለማይደራደሩት ራሺያዊያን ምክንያት አልሆነም። እጅግ አፋኝና ርህራሄ አልባ የሆነውን የፑቲን አስተዳደርን አደባባይ ወጥተው ጦርነቱን አቁም ሲሉ ጠይቀዋል። ሰው ስትሆን ከጥቅምህ ከፍላጎትህ ከምኞትህ በላይ .. ለሰውና ለሰብዓዊነት ትቆማለህ .. ታስባለህ።
አይደለም ሀገርህ ጎረቤትህ እንዲረበሽ እንዲወረር አትፈልግም። ጦርነትን አደባባይ ወጥተህ መቃወም ባትችል እንኳን ጦርነትን ግን ደግፈህ አደባባይ አትወጣም። ራሺያዊያን ግን አደባባይ ወጥተው ጦርነትን አንፈልግም ብለዋል።
ከሁለት አመት በፊት ትግራይ ላይ ጦርነት ሲከፈት ... ዘመቻውን አለመደገፍ ብቻ .."በጅምላ ጁንታ" .. ተብሎ ያሰድብ ነበር። አረ ጦርነቱ በውይይት ይፈታ ካልክ .."ስንት ተከፍሎሃል ጁንታው"? .. ብለው ይጠይቁ ነበር።
ጦርነት በፍቅር በልባዊነት የተደገፈባት ሀገር .. እሱንም የእርስ በርስ ጦርነት እንደ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን በምድር ላይ ያለ ሀገር የለምም .. ተፈልጎም አይገኝም።
ሌላውን ተውት የሀይማኖት አባቶች ፣ ምሁራን ፣እናቶች ፣አባቶች፣ ህፃናት እራሱ አልቀሩም .. አደባባይ ሲወጡ። ዳግማዊ አድዋ ተብሎ ከውጭ ወረራ ጋር ጦርነቱን አያይዘው ንፁሃን እንዲያልቁ የእራሳቸውን አስተዋጽኦ አድርገዋል።
የትግራይን ህዝብ ለመጨፍጨፍ ለገባው ለወራሪው የኤርትራ ጦር የሰገዱ ያጨበጨቡ ደግሞ ሚሊዮኖች ናቸው።
ይህ አረመኔያዊነት ነው ... ጉዳዩ የፖለቲካ እንደሆነ እየታወቀ ሌላ ነገር ተደርጎ እንዲቀርብ እንዲታሰብ የተደረገበት መንገድ ማንም ሊረሳው የማይችልና የትግራይ ህዝብን ከፍተኛ መስዕዋትነት ያስከፈለ ነው።
የኢትዮጵያ ታሪክ በእንደዚህ አይነት የጠቆሩ ታሪኮች የጨቀየ ነው። ባንዳነት አኩሪና የሚያስመሰግን ገድል ነው። ገዳይነት የሚያስኮፍስ አለፍ ሲልም .."አሳ በለው" .. ተብሎ በዘፈን የሚገለፅ አኩሪ ጀብድ ነው። ጦርነት ቂም በቀል የክብር ጉዳይ ተደረጎ ይወሰዳል።
ይህ አስተሳሰብ በዚህ ዘመን ሁሉንም አደባባይ ላይ ያሰባሰበና አንድ ያደረገ መሆኑን ስታውቅ .. በኢትዮጵያም በህዝቦቿም ተስፋ ትቆርጣለህ። ተጋሩዎች ከጦርነቱ በላይ በጦርነቱ ምክንያት የደረሰባቸውና እየደረሰባቸው ያለው በደሎች ነፃ ትግራይን እንዲመሰርቱና እንዲያስቡ መንገድ ከፍቷል።
Finfinne Times
1.7K views16:54