Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-ETHIOPIA

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethiopia — TIKVAH-ETHIOPIA
ርዕሶች ከሰርጥ:
Gbe
Questionandanswer
Globalbankethiopia
Bankinethiopia
Oursharedsuccess
Furtheraheadtogether
Mpesasafaricom
Tikvahfamilyaa
Addisababa
Update
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethiopia
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.34M
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-17 23:14:51
" ቲክቶክ ላይት " ጥያቄ ቀረበበት።

አዲሱ መተግበሪያው ' ቲክቶክ ላይት ' በፈረንሳይ እና ስፔይን አገልግሎት የጀመረው ቲክቶክ በህጻናት እና ተጠቃሚዎች የአዕምሮ ጤንነት ላይ ሊያስከትል ስለሚችለው አደጋ ያለውን ግምገማ በ24 ሰዓት ውስጥ እንዲያቀርብ ዛሬ የአውሮፓ ኮሚሽን ጠየቀ።

ከዋናው ቲክቶክ መተግበሪያ አነስ ብሎ የወጣው የቲክቶክ መተገበሪያ ተጠቃሚዎች #ተከፍሏቸው የቪዲዮ ምስሎችን እንዲመለከቱ በማድረግ በሚያስቆጥሯቸው ነጥቦች የመግዛት አቅምና ዋጋ ያላቸውን የስጦታ ካርዶችን የሚሽልም ነው፡፡

በመተግበሪያው ተሳታፊ ለመሆን ተጠቃሚዎች ቢያንስ እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

ሽልማቱን ለማግኘት በቀን እስከ 1.06 ዶላር የሚደርስ ሽልማት ለማግኘት በየቀኑ አንድ ሰዐት ድረስ ቪዲዮውን መመልከት ይችላሉ፡፡

የአውሮፓ ኮሚሽን የቻይናው ቲክቶክ ባለቤት ባይትዳንስ (ByteDance) መተግበሪያውን ከመልቀቁ በፊት ሊያስከትል ስለሚችለው አደጋ ቁጥጥርና ጥንቃቄ ግምገማ ማድረግ ነበረበት ብሏል።

ጥያቄው የቀረበው ቲክቶክ ያወጣው አዲሱ " Task and Reward Lite " የተባለው መተግበሪያ፣ ለአካለ መጠን ያልደረሱ ሕፃናትን ደህንነት እንዲሁም በተጠቃሚዎች የአእምሮ ጤና ላይ ፣ በተለይ ሱስ አስያዥ ባህሪን ከማነሳሳት ጋር ተያይዞ ሊያመጣ የሚችለውን ተፅእኖ መሰረት በማድረግ ነው ” ሲል የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

መተግበሪያው ሊያስከትለው ስለሚችለው አደጋ ቁጥጥር እንዲሁም ጥንቃቄ ያለውን ግምገማ እንዲያቀርብ ከተሰጠው የ24-ሰዐት የጊዜ ገደብ ባሻገር፣ ቲክቶክ የተጠየቀውን ተጨማሪ መረጃ እ ኤ አ እስከ ሚያዝያ 26 ድረስ መስጠት አለበት ሲል ኮሚሽኑ አሳስቧል።

የቲክቶክ ቃል አቀባይ ፥ " አዲሱን መተግበሪያ በተመለከተ ከኮሚሽኑ ጋር በቀጥታ ተገናኝተናል፣ ለቀረበልን ጥያቄም ተገቢ ምላሽ እንሰጣለን " ማለታቸውን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል።

መረጃውን ቪኦኤ ፤ አዣንስ ፍራንስ ፕሬስን ዋቢ በማድረግ ነው ያስነበበው።

@tikvahethiopia
94.4K views20:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 22:52:14
" ' በኃይል ይዣለሁ ፣ ይዣለሁ ማለቱ ፍጹም ሰላም አያመጣም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት የሆኑት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ፥ " በወረራ " ተይዘዋል ያሏቸውን የትግራይ ክልል ግዛቶችን በሰላም ስምምነቱ መሰረት ነጻ እንዲወጡ እና የአካባቢዎቹ ሰላምና ደህንነት ተረጋግጦ ተፈናቃዮች ወደ ቀድሞ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ኃላፊነት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ ወስደው እንዲሰሩ ከፌዴራል መንግሥት ጋር መግባባት ላይ መድረሱን ተናግረዋል።

ከዚህ ውጭ የክልሉ ጸጥታ ኃይል ምንም አይነት የኃይል እርምጃ ለመውሰድ እንዳልተንቀሳቀሱ ከሰላም ስምምነቱ ጋር የሚጣረስ አንድም ነገር ላለመፈጸም በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ጄነራሉ የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነቱን ለመገምገም በአፍሪካ ህብረት በተመራው የስትራቴጂክ ግምገማ  ወቅት እስካሁን ድረስ ስላልተሰሩ ጉዳዮች ተነስቶ እንደነበር እና እንዲሰራባቸው አቅጣጫ መቀመጡን አስታውሰዋል።

ከስትራቴጂክ ግምገማው በኃላም ለውጦች መታየታቸውን አመልክተዋል።

መሰረታዊ ከሚባሉት የስምምነቱ ክፍሎች እና ካልተፈጸሙት አንዱ ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው መመለስ ነው ያሉት ጄነራሉ " ተፈናቃዮች እንዲመለሱ የትግራይ ግዛት መከበር አለበት ብለዋል።

" በዚህ ላይ ' እንደ ራያና ጸለምቲ ቀላል ነው ፤ ምዕራብ ትግራይ ነው ከባዱ ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሁሉም ቀላል ነው ሁሉም ከባድ ነው ' እየተባለ ምክንያት ይቀርባል። አንዳንዴ ደግሞ ' አከራካሪ ቦታዎች ' እያሉ ይገልጹታል ሆኖም በህገ መንግሥቱ መሰረት ትግራይ ትግራይ ነው አከራካሪ የሚባል ነገር የለም ጥያቄ ካለ እንኳን በህግ አግባብ ነው መተግበር ያለበት " ሲሉ ተናግረዋል።

" ' በኃይል ይዣለሁ ፣ ይዣለሁ ማለቱ ፍጹም ሰላም አያመጣም " ሲሉ አክለዋል።

ጄነራሉ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ችግሮች ዘላቂ ሰላም በሚያመጣ መልኩ እንዲፈቱ እንደሚፈልግ ገልጸው " ለዚህም የመከላከያ ሰራዊት እና ፌዴራል ፖሊስ ኃላፊነት ወስደው እንዲሰሩ እየተደረገ ያለው " ብለዋል።

" በወረራ ተይዟል " ባሉት የትግራይ ክፍል ሁሉም ነገር ያለ አግባብ መቀየሩን አስታውሰው " ሁሉም ፈርሶ ወደነበረበት የትግራይ ቅርጽ እንዲመለስ ፌዴራል መንግሥት በትኩረት እየሰራ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

የትግራይ የጸጥታ ኃይል ስምምነቱን የሚያፈርሱ ተግባራት ላለመፈጸም ከፍተኛ ጥንቃቄ እያደረገ ነው ብለዋል።

" በማህበራዊ  ሚዲያ እና በሌሎችም ፦
- በራያ አላማጣ፣
- በኦፍላና ፣
- በኮረም ላይ ትኩረት አድርገው የሚናፈሱት ወሬዎች ከእውነት የራቁ ናቸው። እነሱ እንደሚሉት በኃይል መያዝ የምንፈልገው አካባቢ የለም። በስምምነቱ መሰረት በፌዴራል መንግሥት ጥረት ነጻ እንዲሆንልን ነው የምንፈልገው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ዘላቂ ሰላም የሚያረጋግጥና ዳግም ደም አፋሳሽ ጦርነትን የማይቀሰቅስ ተግባር እንዲፈጸም ነው የምንፈልገው በእርግጥ ችግሩን በሰላም ለመፍታት በነበረው ሂደት አለመግባባትና ፍጥጫ ነበር ይህ ለራሳቸው ሆነ ለሀገራችን ስለማይጠቅም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና የሰላም ተባባሪ እንዲሆኑ እንጥራለን " ብለዋል።

ዛሬ የአማራ ክልል መንግሥት በሰጠው ይፋዊ መግለጫ፤ " ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ከሷል።

እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ የፌዴራል መንግሥት የሰጠው አስተያየት የለም።

@tikvahethiopia
113.2K viewsedited  19:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 14:39:20
#NewsAlert

ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ አካሂዶ በሁለት ጉዳዮች ውሳኔ አሳልፏል።

ውሳኔ ከተላለፈበት አንዱ ጉዳይ የሽግግር ፍትሕ ረቂቅ ፖሊሲ ነው።

ምክር ቤቱ ፥ " በሀገሪቱ በተለያዩ ዘመናት የተከሰቱ እና የቀጠሉ ተደራራቢ እና ሰፊ የተጎጂና የአጥፊ ወሰን ያላቸው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ የእርስ በእርስ ግጭቶች፣ ያልጠሩ ትርከቶች እና በደሎችን ለመፍታት የተለያዩ ሙከራዎች ተደርገዋል " ብሏል።

" ሆኖም እነዚህ አሰራሮች ፦
- በእውኀት፣
- በዕርቅ፣
- በምህረት እና በፍትሕ ላይ የተዋቀረ እና በግልፅ ፖሊሲ የሚመራ ሁለንተናዊ የሽግግር ፍትሕ ስልትን አካታች፣ ሰብአዊ መብት ተኮር በሆነ እና በተሰናሰለ መንገድ ባለመተግበራቸው የሚፈለገውን ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት አልቻሉም " ሲል ገልጿል።

በመሆኑንም የሽግግር ፍትሕ ሂደቱን በተደራጀ፣ በተቀናጀ እና ውጤታማ በሆነ መልኩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመምራትና ለመተግበር እንዲቻል ረቂቅ ፖሊሲ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቀረቡን አስረድቷል።

ምክር ቤቱም በረቂቅ ፖሊሲው ላይ ከተወያያ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ #በስራ_ላይ_እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

@tikvahethiopia
243.1K views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 10:07:55
#Update

የአማራ ክልል መንግሥት ምን አለ ?

ዛሬ የአማራ ክልል መንግሥት ይፋዊ መግለጫ ሰጠ።

የክልሉ መንግሥት ፥ " ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ከሷል።

" ህወሓት የአማራ ክልል ተማሪዎችን መማሪያ መጽሐፍ እንደ ሰበብ ተጠቅሞ በይፋ ጦርነት ማወጁና መቀስቀሱ ይታወቃል " ሲል አስታውሷል።

የአማራ ክልል መንግሥት ህወሓትን " የመላ ኢትዮጵያ ጠላትና የደኅንነት ስጋት " እንደሆነ ገልጾ " ባለፉት 3 ዙሮች ከተደረገው ደም አፋሳሽ ጦርነት ትምህርት ሊወስድ ይችል ይሆናል በሚል ጭላንጭል ተስፋ የፌዴራል መንግሥት እጅግ እልህ አስጨራሽ ትዕግስት ተላብሶ ውይይቶች እንዲካሄዱ ተደጋጋሚ ጥረት ሲያደረግ ቆይቷል " ብሏል።

" የአማራ ክልል መንግሥትም በተደጋጋሚ ከትግራይ ጊዜያዊ አሥተዳደር ጋር በፌዴራል መንግሥት አማካኝነት ውይይት ለማድረግ በርካታ ሙከራዎች የተደረጉ ቢሆንም ህወሓት ይህን የሰላም አማራጭ ወደ ጎን በመተው የማንነት ጥያቄ ያለባቸውን የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ ኦፍላ፣ ኮረምና ዛታ አካባቢዎች ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ገልጿል።

" ህወሓት ወረራ የፈፀመባቸው ፦
- የራያ አላማጣ፣
- ራያ ባላ፣
- ኦፍላ፣
- ኮረምና ዛታ እንዲሁም የወልቃይት ጠገዴ እና ጠለምት አካባቢዎች የሀገሪቱ ሕገ መንግሥት ከመፅደቁ በፊት በነበሩ አሥተዳደራዊ መዋቅርና አደረጃጀት በኀይል ጠቅልሎ ከመውሰድ ጀምሮ የዘር ማጥፋት ወንጀል እስከመፈፀም ድረስ አሰቃቂ ጥፋት የፈፀመባቸው አካባቢዎች  ናቸው " ብሏል።

" ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ህወሓት በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን አሰቃቂ ጥቃት ተከትሎ ከተቀሰቀሰው ጦርነት በኃላ አካባቢዎቹ በጉልበት ተገፎባቸው የነበረውን ራሳቸውን የማሥተዳደር ነጻነት መቀዳጀት እንደቻሉ " የአማራ ክልል መንግሥት ገልጿል።

በኃላም የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መፈረሙን ፤ ህወሓት ግን ስምምነቱን በማክበር በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የድርሻውን ከመወጣት ይልቅ ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ በመጣስ የተለያዩ ጥፋቶችን ሲፈጽም እንደቆየ አመላክቷል።

" አሁንም እየፈጸመ ይገኛል " ብሏል።

የአማራ ክልል መንግሥት ፥ ህወሓት ደም አፋሳሽ የሆነ ጦርነት ለማድረግ ከመሞከር እንዲታቀብ እና የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲያከብር አሳስቧል።

" በአጭር ጊዜ በወረራ የያዛቸውን አካባቢዎች ለቆ እንዲወጣ " ሲል ጠይቋል።

" ይህ የማይሆን ከሆነ የአማራ ክልል መንግሥት እና ሕዝብ ከሌሎቹ ወንድምና እህት ኢትዮጵያዊያን ጋር በጋራ በመሆን ሀገርን ከማፍረስ መታደግና ሕዝባችንንም ከጥቃት ለመከላከል እንገደዳለን " ሲል አስጠንቅቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
269.1K views07:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 10:06:21
" 400 ሺህ ብር ክፈል ይሉኛል። እኔ ይሄን ያህል ገንዘብ ከየትም ላመጣ አልችልም። ... ልመና ወጥታችለሁ። " - አባት

ኤርትራዊው ስደተኛ ባልታወቁ ሰዎች ተወስዶ ለማስለቀቂያ 400 ሺህ ብር እንደተጠየቀበት ተነገረ።

አባት ገንዘቡን ለማግኘት ልመና ወጥተዋል።

በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ በጭላ ቀበሌ በተቋቋመው የዓለምዋጭ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚኖሩት ኤርትራዊው ስደተኛ አቶ መሀመድ ኡስማን ባለፈው መጋቢት 26 ቀን 2016 ልጃቸው አማን መሀመድ መታገቱን ገልጸዋል።

ልጃቸው በአቅራቢያ ካለው የዳባት ትምህርት ቤት ቀን 10:00 እየተመለሰ እያለ ባልታወቁ ሰዎች መታገቱን አመልክተዋል።

አጋቾቹ በየሁለት ቀን በመደወል የማስለቀቂያ ገንዘብ እየጠየቋቸው እንደሆነ ጠቁመዋል።

አባት አቶ መሀመድ ፥ " እየደወሉ 400 ሺህ ብር ክፈል ብለውኛል። እኔ ይሄን ያህል ገንዘብ ከየትም ላመጣ አልችልም። እስከዚህች እለት ድረስ ይኸው በየአብያተክርስቲያናቱ እና በየመስጂዱ ለልጄ ማስለቀቂያ የሚሆን ገንዘብ ለማሰባሰብ ልመና ላይ ነኝ። ሌሎች ስደተኞችም በልመና ይተባበሩኛል እስካሁን የተገኘ ገንዘብ የለም " ብለዋል።

አጋቾቹ በየደወሉ ቁጥር ልጃቸው እያለቀሰ ድምፁን እንደሚያሰሟቸውም ገልጸዋል።

ልጃቸው በተለምዶ " ባጃጅ " በሚባለው ባለ3 እግር ተሽከርካሪ ታግቶ መወሰዱን ገልጸው የሰሌዳ ቁጥሩን ለፖሊስ ቢያመለክቱም እስካሁን ውጤት የለም።

የኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ፥ " አንድ ልጅ የጠፋ አለ እገታ ሳይሆን አይቀርም የሚል መረጃ ስለመጣ እንደተቋም ከሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የማጣራት ስራ እየሰራን ነው " ብሏል።

የጭላ ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ ምናለ ግንብነህ በበኩላቸው ፥ ከህፃኑ ጋር ሌላ የአስተማሪ ልጅም መወሰዱን ጠቁመዋል።

" እንዴት ሄደ ? ወደየት ሄደ ? የሚለውን ፖሊስ እየሰራበት ነው " ያሉት አስታዳዳሪው " አንድ የታሰረ ልጅ አለ መረጃ ስጥ እየተባለ ነው ያለው " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የቪኦኤ አማርኛ አገልግሎት መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia
234.4K views07:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 10:06:06
#NEVACOMPUTER

በጣም በተመጣጣኝ ዋጋ ዘመናዊ የሆኑ 2023 እና 2024 ቢዝነስ ላኘቶፓች፣ እጅግ ፈጣን የሆኑ የኤዲቲንግ ላፕቶፓች እንዲሁም ለተማሪዎች ቅናሽ የሆኑ ኢሮፕ ስታዳርድ እና ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖች አሉን። ከበቂ መስተንግዶ መረጃ እና ከአንድ አመት ዋስትና ጋር እንጠብቆታለን።

ነቫ ኮምፒዉተር ቴሌግራማችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/nevacomputer

ስልክ፦ 0920153333
አድራሻ - መገናኛ ማራቶን ህንፃ ግራውንድ ፍሎር - NEVA COMPUTER
www.nevacomputer.com
209.4K views07:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 10:06:01
#SafaricomEthiopia

ልዩ ልዩ የኢንተርኔት ጥቅሎችን ከ M-PESA በመግዛት 50% ተጨማሪ ዳታ አግኝተን በነጻ ከሳፋሪኮም ወደ ሳፋሪኮም እንደዋወል!
  
ዳታ እንግዛ! በነጻ እንደዋወል!

የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom
#SafaricomEthiopia
#Furtheraheadtogether
207.7K views07:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 22:15:23
#Update

“ ከታገቱ ሚያዚያ 19/2016 ዓ/ም ሰባት ወራት ይሆናቸዋል። እንደቀላል ነገር በወጡበት ቀሩ ” - የታጋች ባለቤት

ከ6 ወራት በፊት ወደ ባቱ (ዝዋይ) ለስራ ጉዳይ እየተጓዙ በታጣቂዎች ታገቱ ከተባሉ 6 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች መካከል 3ቱ ቢለቀቁም 3ቱ ግን እንዳልተለቀቁ ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም የሚችለውን ሁሉ እንደሞከረ ከ2 ሳምንታት በፊት ገልጾልን ነበር።

በወቅቱ #እንባ እየተናነቃቸው ቃላቸውን የሰጡን የአንዱ ታጋች እህት ፣ “ በስልክ እንኳን ‘አለሁ በሕይወት’ እንዲለን ድምጹን ያሰሙን። 2.8 ሚሊዮን ብር ተከፍሎ 3ቱ ሠራተኞች ግን ከእገታ አልተለቀቁም ” ማለታቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ “ ሠራተኞቹ የአገር ልማት ሥራ ላይ ሲደክሙ ነው ይሄ ችግር የደረሰባቸው። ግለሰቦቹን በማገት የሚመጣ ለውጥ የለም። በሰላም እንዲለቋቸው የሚል ጥሪ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ ” ነበር ያለው።

አሁንስ ምን አዲስ ነገር አለ ?

ከ3ቱ ታጋቾች መካከል የሁለት ልጆቻቸው አባት የታገተባቸው ወ/ሮ ቤተልሄም ገዛኸኝ ፥ ታጋቾቹ አሁንም እንዳልተለቀቁ ገልጸዋል።

ከባለቤታቸው በተጨማሪ አንድ የሁለት ልጃቸው እናት የሞቱባቸው አባትና አንድ ሁለት ቤተሰቦቹን የሚያስተምር ሠራተኞች እንደሚገኙበትና ከታገቱ ከ6 ወራት በላይ ቢያስቆጥሩም ፣ አሁንም ያሉበት እንደማይታወቅ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በንግግራቸው መሀል #የሚያለቅሱት ወይዘሮ ቤተልሄም በሰጡት ቃል ፣ “ በሕይወቱ ስለመኖሩም እየተጠራጠርኩ ነው። ሁለቱ ልጆቹ በትምህርታቸው ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ ደርሶባቸዋል። አንዷ ተመራቂ፣ አንዱ ማትሪክ ተፈታኝ ናቸው። እኔም የስኳርና የደም ግፊት ሕመምተኛ ነኝ ” ብለዋል።

ለመንግሥት ጭምር ባስተላለፉት መልዕክትም፣ “ ሞቷልም፣ አለም ቢባል እኮ አንድ ነገር ነው። እንዲህ አድርጉ የሚሉን ነገር ካለም ቢጠቁሙን መፍትሄ ነው” ብለው፣ “እንደ ቀላል ነገር በሀገራቸው ላይ ታግተው በወጡበት ቅርት ሲሉ ዝም ማለት በጣም ይከብዳልና ሁሉም ርብርብ ያድርጉልን ” ሲሉ ጠይቀዋል።

“ ከታገቱ ሚያዚያ 19 ቀን 2016 ዓ/ም 7 ወራት ይሆናቸዋል። እንደቀላል ነገር በወጡበት ቀሩ። እቃ እንኳን ሲጠፋ ዝም አይባልም እንኳን ሰው። እንደ ሰው ትኩረት ይሰጣቸው ” ሲሉም አክለው አሳስበዋል።

“ እንዲያው በእግዚአብሔር፣ በሁሉም ልጆች ባሏቸው አባቶች፣ እህት፣ ወንድም ባላቸው ሰዎች ሁሉ ስም ሁሉም ሰዎች እንደራሳቸው አይተው የሚችሉትን ነገር ሁሉ ይተባበሩን። ያጣሩ። ከእግዚአብሔር በታች ሰዎችን ነው የምለምነው ” ነው ያሉት።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
268.8K views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 21:56:59
#Rwanda #UK

ዩናይትድ ኪንግደም (UK) ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ ለማዛወር የያዘችው እና ከፍ ያለ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታመነው ዕቅድ የሃገሪቱ ሕግ ሊሆን እንደተቃረበ ቪኦኤ ዘግቧል።

የዕቅዱ ተቃዋሚዎች ደግሞ ስደተኞቹን #በኃይል ከአገር የማስወጣቱን ውጥን ማገድ የሚችል አዲስ የሕግ መቋቋሚያ ለማበጀት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን እገዳ ተጽዕኖ ለማስቀረት እና በላይኛው ምክር የቀረበውን ተቃውሞ ለመቋቋም የታለመው ይህ ሕግ በዚህ ሳምንት በሃገሪቱ ፓርላማ ይድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

‘ የሩዋንዳ ዕቅድ ’ የሚል ቅጽል የተሰጠው ይህ ውጥን ጠቅላይ ሚንስትር ሪሺ ሱናክ ‘ሕገ ወጥ ስደተኞችን ወደዚያች አገር የሚያጓጉዙ ጀልባዎች እንቅስቃሴ’ ለማስቆም ለገቡት ቃል ‘ወሳኝ እርምጃ ነው’ ተብሏል።

የሱናክ ቃል አቀባይ ዴቭ ፓሬስ ምን አሉ ?

" የእንግሊዝ ፓርላማ በያዝነው ሳምንት በሕገ ወጥ አስተላላፊዎች ከፍተኛ እንግልት እና ብዝበዛ የሚፈጽምባቸውን ሰዎች ህይወት የሚታደግ ህግ የማጽደቅ እድል ያገኛል።

አሁን ባለው አካሄድ መቀጠል እንደማንችል ግልፅ ነው። በመሆኑም ይህ ሁኔታ የሚለወጥበት ጊዜው አሁን ነው። " ብለዋል።


በአነስተኛ ጀልባዎች ተጓጉዘው የእንግሊዝ ቻናልን በማቋረጥ ከዚያ የሚደርሱትን ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ ምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሩዋንዳ ለማዛወር እና በቋሚነትም ኑሯቸውን በዚያ እንዲያደርጉ በማቀድ ሁለቱ አገሮች የተፈራረሙት ስምምነት 2 ዓመታት አስቆጥሯል።

በፍርድ ቤት የታገደው ዕቅድ እንግሊዝን በትንሹ 470 ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣት እንደሚችል ቪኦኤ በዘገባው አስፍሯል። #VOA

@tikvahethiopia
242.5K views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 21:54:41
#Ethiopia

የመጋቢት ወር ሀገር አቀፍ የዋጋ ግሽበት 26.2 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አሳወቀ።

በወሩ ከተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ፦

ምግብ ነክ ዕቃዎች (food items) 29 በመቶ ድርሻ ይዘዋል።

ምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች (Non-food Items) 22 በመቶ በመሆን ተመዝግቧል።

በአጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ #በየካቲት_ወር ከነበረበት 28.2 በመቶ ወደ 26.2 በመቶ በመሆን መጠነኛ ቅናሽ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አመላክቷል።

@tikvahethiopia
226.6K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ