Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Poweroutage
Ethiopiancoffee
Update
Ministryofrevenues
Firealert
Jimma
Wolkite
Silte
Arerti
Addisababa
All tags
የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Poweroutage
Ethiopiancoffee
Update
Ministryofrevenues
Firealert
Jimma
Wolkite
Silte
Arerti
Addisababa
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 207.43K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-04-28 13:26:18
በአንድ ከተማ የሚገኙ 300 ቤቶችና የንግድ ተቋማት በእሳት ወደሙ።

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በአለፋ ወረዳ፤ ሮብ ገበያ ከተማ ሚያዚያ 16/2015 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡00 አካባቢ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ300 በላይ የመኖሪያ ቤቶችና የንግድ ደርጅቶች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መውደማቸው ተገልጿል።

የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት ኮማንደር በጋሻው ሽባበው ቃጠሎውን በቀላሉ ለመቆጣጠር ያልተቻለው በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ አውሎ ነፋስ እንደነበርና ቤቶች ተጠጋግተው በመሰራታቸው እንደሆነ ነው የገለጹት።

እንደ ኃላፊው ገለፃ በቃጠሎው የደረሰውን የንብረት ጉዳት ምን ያህል እንደሆነ ተጣርቶ በቀጣይ ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ገልፀው ወቅቱ በአከባቢው ነፋስ የሚበዛበት በመሆኑ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ነው ያሳሰቡት።

የወረዳው አደጋ መከላከልና መልሶ ማቋቋም ክትትል ባለሙያ አቶ አንባየ ይግዘው በቃጠሎው ጉዳት የደረሰባቸውን አርሶ አደሮችን መልሶ ለማቋቋም ግብዓት በነፃ ማቅረብና ብድር ሊመቻችላቸው እንደሚችል ተናግረዋል ሲል ወረዳው አስታውቋል፡፡

በእሳት ቃጠሎው ጉዳት የደረሰባቸው የህብረሰብ ክፍሎችም እለታዊ የምግብ ፍጆታና ቁሳቁሶች እርዳታ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል።

መረጃው የወረዳው ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።

@tikvahethmagazine
25.9K viewsedited  10:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 13:08:16
ለልጃቸው ሰርግ የገዟት ላም ሲሳይ ይዛ መጣች!

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ይልማና ዴንሳ ወረዳ ደዋሮ ቀበሌ ልዩ ስሟ «አካሌ ባድማ» በተባለች መንደር ልጃቸውን ለመዳር በ18 ሺህ ብር  የገዟት ላም 40ሺህ ብር የሚጠጋ ዋጋ ያለው ማዕድን ለባለ ሰርጎቹ አበርክታለች።

በበህር ዳር ከተማ የጋፋት ወርቅ ቤት ባለቤት አለልኝ ማተቤ ማዕድኑ በተለምዶ ወርቅ ይባል እንጂ ወርቅ አይደለም፣ ዋጋው ግን ከወርቅ ማዕድን በእጅጉ ከፍ ያለ እንደሆነና በዋናነትም ጃፓነችና ቻይናዎች እንደሚገዙት ለዶይቼ ቨሌ ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምናና ግብርና ኮሌጅ ፕሮፌሰር ገዛኸኝ ማሞ በበኩላቸው በአንዳንድ የቆላማ አካባቢዎች በሚገኙ እንስሳት አልፎ አልፎ የሐሞት ጠጠር ይፈጠራል፤ ሆኖም ይህ ነገር በተለምዶ ወርቅ ይባል እንጂ ወርቅ አለመሆኑን ያስረዳሉ።

ፕሮፌሰሩ፥ እንደዚህ ዓይነቱ የሀሞት ጠጠር  ወደ ቻይናና ጃፓን አገር እንደሚሸጥ እንደሚያውቁ ጠቁመው ለምን አገልግሎት እንደሚውል ግን በትክክል እንደማያውቁ ነው የተናገሩት።

የወርቅ ባለሙያው አቶ አለልኝ ማተቤ ራሳቸው ከዚህ በፊት ከእንስሳት የተገኘውን ይህን የአሞት ጠጠር እስከ 80ሺህ ብር ገዝተው እስከ 100ሺህ ብር ሸጠው እንደሚያውቁ አመልክተዋል ሲል ዘገባው ያመለክታል፡፡

@tikvahethmagazine
23.5K viewsedited  10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 13:05:39
ሊንክ ኦል ቴክኖሎጂ አ.ማ ከማክስ ብሪጅ ትምህርት እና ልማት አ.ማ ጋር በመተባበር የግራፊክስ ዲዛይን እና የሶሻል ሚድያ አስተዳደር የ2 ወር ልዩ ስልጠና አዘጋጅቶላችኋል።
ባሉን ውስን ቦታዎች ከታች በተቀመጠው ፎርም ፈጥነው ይመዝገቡ።
==========

ለምዝገባ፡
https://forms.gle/x13WTGgEF3cqxGu27

ለበለጠ መረጃ
ስልክ ቁጥር፡ +251 932105657
/+251 116157401
አድራሻ፡ ቦሌ ፍሬንድ ሺፕ ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 406
21.8K views10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 13:05:22
ጉዞ ወደ ሐዋሳ፤ በኦውን ኢትዮጵያ ቱር የተዘጋጀ

ሚያዚያ 28-29 -2015

• የጀልባ ሽርሽርና የአሳ ገበያ ጉብኝት በሐዋሳ ሀይቅ
• የእግር ጉዞ (Hiking) በታቦር ተራራ
• አብያታ: ሻላ ብሔራዊ ፓርክ ጉብኝት

ዋጋ ለ1 ሰው፡ ብር 5,500: ምንም አይነት ተጨማሪ ክፍያ አይኖርም

ክፍያው የሚያካትታቸው፡ ትራንስፖርት እና የ2 ቀን ቁርስ፣ የታሸገ ውሃ እና ምሣ፤ የ1 ቀን እራት እና መኝታ ክፍያ፤ አካባቢ አስጎብኚ ክፍያ፤ ለታቦር ተራራ ወደ ፓርክ መግቢያ እና የጀልባ ሽርሽር ክፍያ

ዋጋው የአልኮልና የፎቶ ክፍያዎችን አያካትትም።

ለጥንዶች የዋጋ ቅናሽ አለን።
የደንበኞቻችን ፍላጎት በተሻለ እናሟላለን!

ለመመዝገብ፡ https://forms.gle/Riz9zCbL3PYgWoDeA
23.8K views10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 22:40:10
በማጂ ወረዳ በዛሬው ዕለት በደረሰ የመብረቅ አደጋ የ1 ሰው ህይወት አለፈ።

በደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ክልል፤ ምዕራብ ኦሞ ዞን ማጂ ወረዳ ችግት ቀበሌ በዛሬው ዕለት ከቀኑ 7:00 አካባቢ በደረሰ የመብረቅ አደጋ የአንድ ሰው ህይወት አልፏል።

በአደጋውም፥ ከብቶችን በመጠበቅ ላይ የነበሩ በ60ዎቹ ዕድሜ ክልል የሚገኙ አዛውንት ህይወት ያለፈ ሲሆን በወቅቱ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ በመዝነብ ላይ እንደነበር ነው የተገለጸው።

አዛውንቱ በእርሻ ማሳቸው አቅራቢያ በሚገኝ ጎጆ ውስጥ ተጠልልው ባሉበት ወቅት በደረሰ የመብረቅ አደጋ ህይወታቸው ሊያልፍ መቻሉን ወረዳው አስታውቋል።

በተመሳሳይ በወረዳው መጋቢት 9 ቀን ከርሲ ቀበሌ አባት እና ልጅ ከብት እየጠበቁ፤ ዛፍ ስር ተጠልለው ባሉበት ወቅት ከአባቱ ጋር የነበረው የ16 ዓመት ታዳጊ በደረሰ የመብረቅ አደጋ ወዲያው ህይወቱ ማለፉን ወረዳው ገልጾ ነበር።

@tikvahethmagazine
29.9K viewsedited  19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 18:41:41
በሉሜ ወረዳ ልዩ ስሙ ጎዴ ዮሐንስ በተባለ አካባቢ የደረሰው አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ!

ከአረርቲ ከተማ ተነስተው ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበሩ ተጓዦች በሉሜ ወረዳ ልዩ ስሙ ጎዴ ዮሐንስ በተባለ አካባቢ በደረሰ የመኪና አደጋ የ11 ተሳፋሪዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል።

አደጋው አይሩፍ የኮድ ቁጥር ኦሮ 27600 የሆነ መኪና ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ ሴራሚክ ጭኖ ከቆመ መኪና ጋር በመጋጨቱ የተከሰተ መሆኑን የአረርቲ ከተማ ከንቲባ አቶ ጌታቸው ለማ በሰጡት የሀዘን መግለጫ ገልጸዋል።

የሉሜ ወረዳ ኮሚኒኬሽን በበኩሉ አደጋው ጠዋት 11:30 ላይ መከሰቱን ጠቅሶ ወደ አዳማ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከቆመ IVCO TRAKAR-ET 48435 ጋር በመጋጨቱ መከሰቱን ገልጿል።

በአደጋውም የ10 ሰዎች ህይወት ማለፉንና 2ቱ ሴቶች መሆናቸውን ጠቅሷል። በተጨማሪም በሁለት ሰዎች ላይ ከፍተኛ የአካል ጉዳት እንዲሁም በአንድ ሰው ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን ነው የገለጸው።

የሉሜ ወረዳ የትራፊክ ደህንነት አስተባባሪ ኢንስፔክተር ተክልየ ታምሩ የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር እንደሆነ ገልጸዋል።

@tikvahethmagazine
15.1K viewsedited  15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 17:16:26
ህጻናትን መሬት ላይ ሸፋፍኖ፣ አስተኝቶ መለመን ... የልመና ስልት ይሆን?

በመዲናዋ ብዙ አይነት የልመና አይነቶችን እንመለከታለን። አንዳንዶቹ ልመናዎች ግን ህጻናትን ጭምር በመጠቀም የሚደረጉ በመሆናቸው ልብን ሰብሮ ምጽዋት ከመስጠት ባለፈ ጥያቄ ይጭራል።

በተለይ መገናኛ አካባቢ ህፃናትን አስተኝቶ መለመን መለመዱን ጥቆማውን ያደረሱን ቤተሰቦቻችን የገለጹ ሲሆን ጨቅላ ህፃን አስፓልት ላይ አስተኝቶ መለመን ለጤናም ሆነ ለሞራል የሚከብድ ነገር እንደሆነ ነው የጠቀሱት።

በዚህ ጉዳይ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ሴቶችና ህጻናትጉዳዮች ቢሮን አነጋግሯል፦

ጉዳዩ እንደ ቢሮ በሚገባ ይታወቃል፤ ለኛም በጣም አሳሳቢ እና አስጨናቂ ጉዳይ ሲሉ በቢሮው የህጻናት መብት ደህንነት ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ አንዷለም ታፈሰ  ይገልጻሉ። ሆኖም ቢሮው ክልከላ የማድረግ ወይንም የህግ አግባብን ለመተግበር ግን ስልጣን እንደሌለው ነው ያነሱት።

ዳይሬክተሩ አክለውም "እየከፋ እየመጣ ያለው ልመናን በወንጀል ደረጃ አስቀምጦ ወይንም አላግባብ የሆነ የልመና ሂደቶችን ክልከላ ያስቀመጠበት ህግ ስለሌለን እነዚህን እናቶች ወጥታቸሁ አትለምኑም ማለት አንችልም" ሲሉ ተናግረዋል።

ለመሆኑ ህጻናቱን ለልመና ብለው የሚሰርቁት ለዚሁ ይሆን ?

እንደ ቢሮው መረጃ ልጅ ጠፋ ሚባሉ ነገሮችን በተደጋጋሚ እንደሚሰማና አንዱ ልጅ የሚጠፋበትም ምክንያትም ለገቢ ማስገኛ ዘዴ እነደሆነ ይጠቁማል፡፡

ለምሳሌ በ2014/15 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት 58 አካባቢ የሚሆኑ ልጅ የመጥፋት ኬዞች የተመዘገቡ ሲሆን ከዚህም ውስጥ በሁለት መንገድ ሕጻናቱን በመስረቅ ለገቢ ማስገኛ እንደተጠቀሟቸው ተገልጿል።

የመጀመሪያው ልጅን አግቶ ገንዘብ መደራደር አይነት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አሁን እንደምናየው በተለያየ መንገድ ልጆቹን በመውሰድ ለልመና እንደሚጠቀሟቸው እንሰማለን፡፡

ቢሮው ችግሩን ለመቅረፍ የህግ ማዕቀፍ እያዘጋጀው ነው ብሏል።

የህጻናት መብት ደህንነት ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ አንዷለም ታፈሰ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር በኩል ይህንን ድረጊት በህግ ሊከለክል የሚችል (ሊያስቆም የሚችል) አዋጅ እንዲወጣ እየተደረገ መሆኑንና ረቂቁ ማለቁን ጠቁመዋል።

ይህ አዋጅ ተተግብሮ ወደ ሥራ ከተገባ ትልቅ እፎይታ ይፈጥራል ብለው እንደሚያስቡ የገለጹት ዳይሬክተሩ አዋጅ ተግባራዊ እስከሚደረግ ድረስ ቢሮው መመሪያ ማዘጋጀቱን አንስተዋል።

ለመሆኑ መመሪያው ላይ ምን ተካቷል?

መመሪያው ህጻናትን የያዙ እናቶች ልጆቻቸውን የቀን ማቆያ ውስጥ ማዋል እንዲችሉ፤ ምቹ በሆነ ቦታ ላይ ህጻናቱን አድርገው የተለያዩ ገቢ ሚያስገኙ ስራዎቹን ሰርተው በመመለስ ህጻናቱን መልሰው ሊወስዱ የሚችሉበት አሰራር የሚዘረጋ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

መመሪያው ህጻናቱ ማቆያ ውስጥ ሲቆዩ ምን ምን አገልግሎቶችን ያገኛሉ? ምን አይነት ነገሮች ሊሟሉላቸው ይገባል? ምን አይነት ህጻናቶች ናቸው እዚህ ውስጥ ሚገቡት? የሚሉትን የሚመልስ ሲሆን አሁን ላይ ተጠናቆ የፍትህ ቢሮ የህግ አስተያየት ሰጥቶበት ለፋናንስ ቢሮ መላኩን አክለው ገልጸዋል።

ይህ ጎዳና ላይ ለሚለመንባቸው ህጻናት ብቻ ሳይሆን ልጆቻቸው አካል ጉደተኛ ሆነው ወተው መስራት ለማይችሉ፤ ልጆቻቸውን ብቻ ይዘው ቤት ውስጥ ለሚቀመጡ ወላጆች፤ በማረሚያ ቤት ውስጥ ልጆቻቸው ላሉ (በረጅም ጊዜ በማቆየት) ሁሉን ሊያቅፍ በሚችል መልኩ መመሪያው መዘጋጀቱን አብራርተዋል።

ዳይሬክተሩ ልጆቻቸው በማቆያ ከሆኑ ወላጆቻቸው ገቢ ማግኘት የሚችሉበትን መንገድ ጭምር ጎን ለጎን እያሰቡ መመሪያው መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።

የእርሶስ ትዝብት ምንድን ነው?

@tikvahethmagazine
17.1K viewsedited  14:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 17:16:13
ለመጪው የኢትዮጵያ ስቶክ ማርኬት ራስዎን አዘጋጅተዋል?

ስልጠናው የሚጀምርበት ቀን፡- ሚያዚያ 21
ስልጠናው የሚሰጥበት ጊዜ፡- ሶስት ቅዳሜዎች ለግማሽ ቀናት እና ሶስት እሁዶች ለግማሽ ቀናት

ስልጠናው የሚሰጥበት ቦታ፡- ብሉ ስካይ ሆቴል

ዋጋው፡- 6000 ብር

ለበለጠ መረጃ 0911460767/ 0984791562
14.4K views14:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 17:15:58
ብቁ ዜጋ የህጻናት ሃይኪንግ 

ሱባ መናገሻ ደን  - Suba Menagesha Forest

ልጅዎን ዘና ማድረግ ይፈልጋሉ? አከባቢያቸውንና ሀገራቸውን እንዲያውቁስ ይፈልጋሉ? እንግዲያውስ ልጆችዎን በ @bikuZega መስራች ወላጆች በተዘጋጀው ወደ ሱባ መናገሻ ጫካ የእግር ጉዞ ተስሳታፊ ያድርጉት!

የተለያዩ  ዛፎችን እና ወፎችን በመመልከት፣ በሚያምር የደን አከባቢ ውስጥ በመመገብ እና የተለያዩ ጨዋታዎችን በመጫወት ይደሰቱ። ለልጆች አስደሳች እና ትምህርታዊ ተሞክሮ እንደሚሆን እርግጠኞች ነን።

ቅዳሜ, ሚያዚያ 21, 2015

ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ  አሁኑኑ ይመዝገቡ!

የጥቅሉ ዋጋ ለአንድ ሰው
: 1100 ብር ብቻ

በወላጆች የተዘጋጀ እና በጎ ፈቃደኞች ቢኖሩም ወላጆች ልጆቻቸውን ይዘው ቢመጡ እና  አብረዋቸው ጊዜ ቢያሳልፉ ይበረታታል።

ለመመዝገብ እና ለተጨማሪ መረጃ ይደውሉልን
0913547017
0930069223

Message us on Telegram
@bitsitelias
14.1K views14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 16:02:20
በአዳማ ሀሰተኛ ደረሰኝ በማተም እና በማሰራጨት ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በገቢዎች ሚኒስቴር የአዳማ ገቢዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በከተማዋ ሀሰተኛ ደረሰኝ በማተም በማሰራጨት በህገ-ወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ገልጿል።

ግለሰቦቹ በከተማዋ ህጋዊ ፈቃድ አውጥተው በተሰማሩ ድርጅቶችና እና ሆቴሎች የንግድ ስም በመጠቀም ግብይት ባልተፈፀመበት ግብይት እንደተፈፀመ አስመስለው ሀሰተኛ ደረሰኝ በማተም እና በመሸጥ ላይ የተሰማሩ መሆናቸውን የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ደርቤ ገልጸዋል፡፡

በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ለሁለት ወራት ያክል በተደረገ ክትትል በተለያዩ 35 በሚሆኑ ህጋዊ ድርጅቶች ስም የታተመ ሀሰተኛ ደረሰኝ የተያዘ ሲሆን ዋነኛ የድርጊቱ ተጠርጣሪዎችን እጅ ከፈንጅ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል ተብሏል፡፡

ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ሲውሉ ከሀሰተኛ የወጪ እና የገቢ ደረሰኝ ህትመት እና ስርጭት ባለፈ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች፣ የነዋሪነት መታወቂያና ሌሎች ሀሰተኛ ሰነዶችንም ጭምር ሲያዘጋጁ ነበርም ተብሏል።

@tikvahethmagazine
16.4K viewsedited  13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ