Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Tikvahfamily
Update
Cloudbridge
Traininginstitute
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.20K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2024-04-04 14:47:08
#Update: 70 ሺ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ከሳውዲ አረቢ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ሁኔታዎችን የሚያመቻች ልዑክ ወደ ሳውዲ ሊያቀና ነው

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ 70ሺህ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ሁኔታዎችን የሚያመቻች በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አምባሳደር ብርቱካን አያኖ የተመራ የመንግሥት ልዑክ በቀጣይ ቀናት ወደ ሳዑዲ አረቢያ እንደሚያቀና ገልጿል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ክቡር አቶ ነብዩ ተድላ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ልዑኩ በሳዑዲ በሚኖረው ቆይታ አስፈላጊውን ዝግጅት ካጠናቀቀ በኋላ በፍጥነት ዜጎችን የመመለስ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር ገልጸዋል።

@TikvahethMagazine
20.7K viewsedited  11:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 12:24:15
በቀጣይ ዓመት ብሔራዊ መታወቂያ የሌላቸው ነጋዴዎች የንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት አያገኙም ተባለ

በሚቀጥለው ዓመት የንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት ለማግኘት ብሔራዊ መታወቂያ ያስፈልጋል በማለት በቀጣይ ዓመት ብሔራዊ መታወቂያ የሌላቸው ነጋዴዎች አገልግሎት ማግኘት እንደማይችሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

የንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት ማግኘት የሚፈልጉ ደንበኞች በአካል መገኘት ሳይጠበቅባቸው በኦንላይን አገልግሎት እያገኙ ነው ሲባል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚሰጣቸው አገልግሎቶች ከሌሎች ተቋማት ጋር የሚያገናኘው በመሆኑ ከተቋማቱ ጋር ሲስተም የማናበብ ስራ በፋይዳ መለያ የሚሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።

ስለዚህ የንግዱ ማህበረሰብ ከ2017 በፊት ብሔራዊ መታወቂያ በማውጣት ራሱን ለነገሮች ዝግጁ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የላይሰንሲንግ እና ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጅራታ ነመራ ተናግረዋል።

Credit : EPA

@TikvahethMagazine
22.9K views09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 12:21:05
#Update: የግለሰቦች የግል መረጃ ያለፍቃድና ባልተፈቀደለት አካል ጥቅም ላይ እንዳይውል የሚያደርግ አዋጅ በፓርላማ ፀደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 20ኛ መደበኛ ስብሰባ የግለሰቦች የግል መረጃ ያለፍቃድና ባልተፈቀደለት አካል ጥቅም ላይ እንዳይውል የሚያደርግውን የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ መርምሮ አፅድቋል።

@TikvahethMagazine
19.7K views09:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 12:20:28
የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያ ከ48 ኢንቨስተሮች 1.5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ማሰባሰቡን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ሰነድ ሙዓለ ነዋይ ገበያ በፋይናንስና ከፋይናንስ ዘርፍ ውጪ ባሉ መስኮች የተሰማሩ ከ 48 የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብቶች 1.5 ቢሊዮን ብር ካፒታል ማሰባሰቡን ይፋ አድርጓል።

ገበያው 631 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረ ሲሆን የተሰበሰበው ካፒታል 1.5 ቢሊዮን ብር እንደሆነና ከዕቅዱ በ240 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑ ተጠቁሟል።

@TikvahethMagazine
17.8K viewsedited  09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 12:20:03
በሀገራችን ስላምን ለማፅናት፣ ሁላችንም የራሳችን ድርሻ አለን። ለመሆኑ ሰለ አገራችን ሠላም ምን የሚሉት አለ? ስለ አጋራናችሁ  የሰላም ጥሪ መልዕክትስ የሚሰጡን አስተያየት ካለ @Utopiaadd ላይ ያጋሩን። ለሠላም ለመስራት መቼም ረፍዶ አያውቅም!
15.9K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 12:20:03
ከቅርብ አመታት ወዲህ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለትምህርት አሰጣጥ ዘዴ መፍትሄዎችን ማምጣት ችሏል። ተቋማችንም ከዘመኑ ጋር አብሮ በመጓዝ የተለያዩ ቋንቋዎችን  በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እድገት ተማሪና አስተማሪን በቀላል መንገድ በማስተሳሰር መማርን ቀላልና ተደራሽ አድርጎ መቷል።እርሰዎም ፈጥነው በመመዝገብ ፍላጎትዎን ያሳኩ!
   እንግሊዘኛ
   አረብኛ
   አፋን ኦሮሞ
   አማርኛ  ቋንቋን ባሉበት ሆነው ይማሩ!!

ለበለጠ መረጃ፦ 0933666662ወይም
                        0932878889 ይደውሉ

በአካል መምጣት ከፈለጉ
አ.አ፡ቤተል፡ AJ ሞል አራተኛ ፎቅ ላይ ያገኙናል

  ብራይት የስልጠና ማዕከል
  ለብርሀናማ ህይወት ትክክለኛ ቦታ!!

https://t.me/brighttraining90
18.6K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 23:10:32
#inShort : የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ግንባታዎችን በሚመለከት ያስተላለፈው ውሳኔ

@TikvahethMagazine
26.6K viewsedited  20:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 20:35:20
የትራፊክ አደጋ መረጃዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ለመሰብሰብ የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈረመ

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የመንገድ ደኅንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት የመንገድ ትራፊክ አደጋ መረጃ አያያዝ ሥርዓትን ለመተግበር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ።

በሀገራችን የሚደርሱ የመንገድ ትራፊክ አደጋዎች ዳታ አያያዝን በቴክኖሎጂ ለማገዝ ጥናትና ሶፍትዌር የማበልፀግ ሂደቱ አልቆ በተግባር ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል። ቴክኖሎጂው መረጃዎች በአግባቡ ተሰብስበው ፖሊሲዎች እንዲዘጋጁ እና አደጋን ለመከላከል የሚያስችሉ መፍትሄዎችንም ለማስቀመጥ እድል ይፈጥራል ተብሏል።

@TikvahethMagazine
28.6K views17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 17:14:01
ጁምዓና ከተራን ጨምሮ አራት ቀናት ሥራ ዝግ ሆኖ እንዲከበሩ ጥያቄ ቀረበ

ጁምዓ፣ ከተራና ቃና ዘገሊላ የአደባባይ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች፣ እንዲሁም የካቲት 12 የሰማዕታት መታሰቢያ በዓላት ሥራ ዝግ ሆነው እንዲከበሩ በፓርላማ ጥያቄ መቅረቡን ሪፖርተር አስነብቧል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለጤና፣ የሕዝብ በዓላትንና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ የሕዝብ ውይይት የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች፣ ምሁራንና ሌሎች ተቋማት ተሳትፈዋል።

ተሳታፊዎቹ ምን ጥያቄ አቀረቡ?

- የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን በመወከል የተገኙት ኡስታዝ አህመዲን ጀበል፣ በእስልምና አንድ ሰው 3 ተከታታይ ጁምዓ ካልተገኘ በመናፍቅነት የሚያስፈርጅ ከባድ ጉዳይ በመሆኑ፣ ዓርብ (ጁምዓ) ቀን ሥራ ዝግ እንዲሆን፣ ወይም ደግሞ አሁን በሥራ ላይ ያለውን ከአምስት ሰዓት ተኩል እስከ ሰባት ሰዓት ተኩል በአዋጁ መካተት አለበት ብለዋል።

- ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትሪያሪክ የሕግ መምርያ ኃላፊ መምህር አባ ገብረ ሥላሴ ጌትነት፣ እየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ባህረ ዮርዳኖስ ሄዶ መጠመቁን የሚያሳየው የቃል ኪዳኑን ታቦት በመያዝ ጥር 10 ቀን የሚከበረው ከተራና ከጥምቀት በኋላ ጥር 12 ቀን የሚከበረው ቃና ዘገሊላ ክብረ በዓላት ከሥራ ዝግ መሆን አለባቸው ብለዋል፡፡

- በተጨማሪም የካቲት 12 የሰማዕታት ቀን ታስቦ ከመዋል ይልቅ ከሥራ ዝግ ሆኖ መከበር ይገባዋል ያሉት ደግሞ፣ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር) ናቸው፡፡

የተሰጡ አስተያየቶች ረቂቅ አዋጁን ለማጎልበት እንደሚያግዝ ሲገለፅ፣ አዋጁ ኢትዮጵያውያንን እንዲመስል ዘላቂነት ያለው ውይይት እንደሚደረግም ተጠቁሟል።

@TikvahethMagazine
30.1K views14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 17:13:16
በወልቂጤ ተጣምረውና ተዋህደው የተወለዱ መንትዮች በተሳካ ቀዶ ህክምና እንዲለያዩ ተደረገ

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
የተዋሃዱ ወይም የተጣመሩ መንትዮችን በቀዶ ህክምና በተሳካ ሁኔታ እንዲለያዩ ማድረጉን አስታውቋል።

የቀዶ ህክምናው የተሰራው በሆስፒታሉ የህፃናት ስፔሻሊስት ሃኪም በሆኑት ዶ/ር ሙሉአለም አማረ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ የተዋሃዱ ወይም የተጣመሩ መንትዮች ክስተት እርግጠኛ ያልሆነ ፅንስ መከሰትን የሚጠቁም እንደሆነና ባለሙያው ሞኖዚጎቲክ መንትዮች የሚፈጠሩት ከአንድ ቀደምት ፅንስ ክፍፍል እና መለያየት እንደሆነ አስረድተዋል።

በዚህ መሰረት በተደረገው የቀዶ ህክምና አገልግሎት አንደኛው ህጻን በህይወት የተወለደ ሲሆን ህፃኑ በተወለደ በአምስተኛ ቀኑ ከራሱ ጋር ተጣብቆ የተወለደውንና በህይወት ከሌለው መንትያ ጋር በመለየት በህይወት የተረፈው ህጻን በሰላም ወደ ቤቱ መመለሱን ባለሙያው ገልጸዋል።

ይህን መሰል ክስተት የስርጭት መጠኑ ቀደም ሲል ከ50,000 እስከ 100,000 ከሚወለዱ ሕፃናት መካከል በአንዱ የሚከሰት ሊሆን እንደሚችል ዶ/ር ሙሉአለም አማረ አብራርተዋል።

@TikvahethMagazine
26.6K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ