Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Tikvahfamily
Cloudbridge
Traininginstitute
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.20K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2024-03-30 12:53:29
በወሊሶ ከአንድ ወጣት ሆድ ውስጥ 3 ትልልቅ ሚስማሮችን ጨምሮ መርፌ፣ ሽቦና 9 መፋቂያዎች በቀዶ ህክምና ተወገዱ

በወሊሶ አጠቃላይ ሆስፒታል ከ28 አመት ታካሚ ሆድ ውስጥ 1ብረት፣ 3 ቀጫጭን ሽቦዎች ፣ 3 ትላልቅ ሚስማሮች፣ 1 የልብስ መርፌ እና 9 መፋቂያዎችን በቀዶ ህክምና መውጣቱን የመርቲ ወረዳ ኮሚኒኬሽን አስታውቋል።

የተለያዩ ብረቶች በቀዶ ጥገና ከሆዱ የወጡለት ግለሰብ የአእምሮ ህመምተኛ መሆኑ ሲነገር የተወለደው በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን አማያ ወረዳ ነው። ታካሚው ህክምና ከተደረገለት በኋላ በአሁኑ ጊዜ በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል ተብሏል።

@TikvahethMagazine
18.7K views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-30 12:53:03
#DStv

ቀላል እና ፈጣን መላ ለዲኤስቲቪ ደንበኞች በሙሉ!

ወደ ዲኤስቲቪ የጥሪ ማዕከል ሳይደውሉ በማንኛውም ሰዓት በሞባይልዎ *9299# በመደወል እና My DStv App ስምዎንና የስማርት ካርድ ቁጥርዎን አስገብተው የዲኤስቲቪ ክፍያ መጠንዎንና ቀኑን በቀላሉ ለማወቅ ፓኬጅ ለመቀየር ብሎም በቴሌብር ፣ በሲቢኢ ብር እና በአዋሽ ብር መክፈል ይችላሉ።

የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ!

https://bit.ly/2WDuBLk

የፕሌይ ስቶር ሊንክ ይጫኑ!

https://bit.ly/3qJ95Us 

የአፕ ስቶር ሊንክ ይጫኑ!

https://bit.ly/45hIwEU

በተጨማሪም ስለ አገልግሎታችን ጥራት በሚደርስዎት የፅሁፍ መልዕክት ላይ ሊንኩን በመጫን መጠይቁን እንዲሞሉ በትህትና እንጠይቃለን።

ይሞክሩትና የማይጠገብ የመዝናኛ አማራጭ ያለማቋረጥ ያጣጥሙ ፤ የእርስዎንም አስተያየት ያጋሩ!

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET'
21.2K views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-29 17:43:37
ለውጭ ገበያ የሚቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል እስከ ደቡብ አፍሪካ የማድረስ ዕቅድ መኖሩ ተገለጸ።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገራት እያቀረበች ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል የበለጠ ለማስፋፋት እየሰራች መሆኑን ከኢዜአ በነበራቸው ቆይታ ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ ለሱዳን፣ ለጅቡቲና ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበች መሆኑን ገልጸው፥ ለውጭ ገበያ የሚቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል እስከ ደቡብ አፍሪካ የማድረስ ዕቅድ መያዙን ተናግረዋል።

በቅርቡም #ለታንዛኒያ ኃይል ለማቅረብ መግባባት ላይ መደረሱን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ደቡብ ሱዳን፣  ኡጋንዳና ሩዋንዳ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመውሰድ ፍላጎት ማሳየታቸውንም አንስተዋል።

ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ከሀገራቱ ጋር ንግግር መጀመሯን ነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የገለጹት።

@TikvahethMagazine
27.6K viewsedited  14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-29 17:43:16
የስብሰባ ማስታወቂያ

አዲስ አበባ የሚገኘው የመድኃኔዓለም ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር አጠቃላይ ስብሰባ መጋቢት 22ቀን 2016 ዓ/ም  ከጧቱ 3  እስከ 7 ሰዓት በትምህርት ቤቱ አዳራሽ ይካሄዳል።

በመሆኑም በትምህርት ቤቱ የተማራችሁ ተማሪዎች በሙሉ በስብሰባው ተገኝታችሁ እንድትሳተፉ ጥሪአችንን እናቀርባለን።      
    
[ አስተባባሪ  ኮሚቴው። ]
25.4K views14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-29 16:39:23
በአፍሪካ ለነዳጅ እና ጋዝ ፕሮጀክቶች ብድር የሚያቀርበው የአፍሪካ ኢነርጂ ባንክ በዚህ አመት ስራ ይጀምራል ተባለ

አፍሪካ የነዳጅ እና ጋዝ ፕሮጀክቶችን በገንዘብ የመደገፍ  ስራ ይሰራል የተባለው የአፍሪካ ኢነርጂ ባንክ በዚህ አመት በ5 ቢሊዮን ዶላር መነሻ ካፒታል በ2024 ስራ ሊጀምር መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።

ባንኩ የተቋቋመው በአፍሬክሲም ባንክ እና በአፍሪካ ፔትሮሊየም አምራቾች ድርጅት (ኤፒፒኦ) ሲሆን ዋናዎቹ ባንኮች በአየር ንብረት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ የነዳጅ ፕሮጀክቶችን በመተው ኢንቨስትመንቶቻቸውን ወደ ሌላ ቦታ እንዲቀይሩ ከአካባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች ከፍተኛ ጫና እያጋጠማቸው በመሆኑ ዘርፉ የፋይናንስ እጥረት ችግር ውስጥ ገብቷል ተብሏል።

ይህ ባንክ በአፍሪካ ኢነርጂ ዘርፍ ያለውን ይህንን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ ሚና ይኖረዋል ሲባል ካፒታሉን ለማሰባሰብ እያንዳንዱ የአፍሪካ አባል ሀገር ቢያንስ 83 ሚሊዮን ዶላር መለገስ እንደሚጠበቅበትና ቀሪው ገንዘብ ከመካከለኛው ምስራቅ አማራጭ የፋይናንስ ምንጮች ይሰበሰባል ተብሏል።

@TikvahethMagazine
25.0K views13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-29 15:26:29
አካል ጉዳተኞችን የተመለከተ አዋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊወጣ መሆኑ ተሰማ

አካል ጉዳተኞች መብታቸው እንዲጠበቅ ለመብታቸው መጠበቅም ምላሽ የሚሰጥ ተፈጻሚነቱን የሚከታተል ባለቤት ያለው አዋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊወጣ መሆኑን ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል።

ኢትዮጵያ ለአካል ጉዳተኞችን መብት ምላሽ የሚሰጥ ጥቅል አዋጅ የላትም የተባለ ሲሆን ያን ለማድረግ የአካል ጉዳተኞች ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ወደ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መላኩ ተገልጿል።

ይህ የአካል ጉዳተኞች አዋጅ ፥ ያሉትን ህጎች ተከታትሎ የሚያስፈፅም፣ ካልተፈፀሙም ተጠያቂ የሚሆን ተቋም እንዲኖር ለማስቻል ፣ የህግ ክፍቶችም እንዲስተካከሉ ያደርጋል ተብሏል። አዋጁ ወደ ፍትህ ሚኒስቴር ተልኮ አስፈላጊ አስተያየት ከተሰጡበት በኋላ ወደ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መላኩ ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine
25.8K views12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-29 15:25:40
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቀጣዮቹ አስር ቀናት አጀንዳ የማሰባሰብ ሥራ ይጀምራል ተባለ

በቀጣዮቹ አስር ቀናት ውስጥ በተመረጡ ክልሎች አጀንዳ የማሰባሰብ ሥራ እንደሚጀምር የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መግለፁን ኢፕድ ዘግቧል።

አሁን ላይ ኮሚሽኑ በ10 ክልሎች የተሳታፊዎች ልየታ አጠናቅቋል። የአጀንዳ ማሰባሰቡ ሥራ በአዲስ አበባ፣ በጋምቤላ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በሲዳማ፣ በሐረር እንዲሁም በድሬዳዋ እንደሚጀመር ተጠቁሟል።

@TikvahethMagazine
24.9K viewsedited  12:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-28 20:04:21
ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ባስጀመረው የንባብ ዘመቻ በበርካታ ሰዎች የተጠቆሙት መጻሕፍት የትኞቹ ናቸው ?

ኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬድዮ ከየካቲት 17 እስከ ግንቦት 27 /2016 ዓ.ም ለ100 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የንባብ ዘመቻ ማስጀመሩ ይታወሳል። እስካሁን የመጻሕፍት ምርጫቸውን በማሳወቅ ጥቆማ የሰጡ ሰዎች ሰላሳን ተሻግረዋል።

የመጻሕፍት ጥቆማቸውን ይፋ ባደረጉት የጀመሪያዎቹ 30 ሰዎች ዘንድ የትኞቹ መጻሕፍት በተደጋጋሚ ተመረጡ ?

1) የሀዲስ አለማየሁ "ፍቅር እስከ መቃብር" በ 9 ሰዎች የንባብ ጥቆማ ዝርዝር ውስጥ ተካትቷል።

2) የሎሬት ፀጋዬ ገብረ መድህን " እሳት ወይ አበባ "  በ5 ሰዎች የንባብ የንባብ ዝርዝር ውስጥ መግባት ችሏል።

3) የሀዲስ አለማየሁ " ትዝታ " በ 3 ሰዎች፤

4) የቀዳማዊ አፄ ሀይለስላሴ " ሕይወቴ እና የኢትዮጵያ እርምጃ " በ 3 ሰዎች፤

5) የበዓሉ ግርማ " ኦሮማይ " በተመሳሳይ በ3 ሰዎች የንባብ ምርጫ ውስጥ መካተት ችሏዋል።

የሚከተሉት 6 መጻሕፍት ደግሞ እያንዳንዳቸው በ 2 ሰዎች የንባብ ጥቆማ ዝርዝር ውስጥ መካተት ችለዋል።

1)  የፊዮዶር ዶስቶቭስኪ " ወንጀል እና ቅጣት "

2) የእጓለ ገ/ዮሐንስ " የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ"

3) የተመስገን ገብሬ " ሕይወቴ "

4)  የፋሲካ ሲደልል " የሻምላው ትውልድ "

5) የመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ " የሐያኛው ክፍለ ዘመን መባቻ "

6) የዳኛቸው ወርቁ " አደፍርስ "

@TikvahethMagazine
14.0K viewsedited  17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-28 15:44:35
በሰሜን ኢትዮጵያ ያሉ አሳሳቢ የጤና ችግሮችን ለመፍታት የሚውል 1.8 ሚሊዮን ዶላር እንደምትሰጥ ጃፓን አሳወቀች

በሰሜን ኢትዮጵያ የጤናና ስነ ምግብ አገልግሎትን ማጠናከርን ጨምሮ አሳሳቢ የጤና ችግሮችን ለመቅረፍ ይረዳል ያለውን 1.8 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ለኢትዮጵያ እንደሚሰጥ የጃፓን መንግስት አሳውቋል።

በዚህም የገንዘብ ድጋፉ የጃፓን ኤምባሲ እና የአለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮ በጋራ በመሆን በኢትዮጵያ በትግራይ፣ አፋር እና አማራ ክልሎች የኮሌራ፣ የኩፍኝ እና የወባ ወረርሽኞችን ለመቆጣጠር ለሚሰሩት ስራ እንዲሁም የተመረጡ የጤና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም እንደሚውል ተነግሯል።

@TikvahethMagazine
20.3K viewsedited  12:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-28 12:07:15
ዜጎች የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ በኦንላይን ተመዝግበው ባሉበት እንዲመጣላቸው የሚያስችል አገልግሎት ተጀመረ

ብሔራዊ መታወቂያ ካርድን በኦንላይን ተመዝግቦ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በኩል ካርዱን ካሉበት ሆነው በማዘዝ ባሉበት የማድረስ ሥራ መጀመሩን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ማስታወቁን ኢፕድ ዘግቧል።

የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ የሕትመት ሥራ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ሲከናወን የቆየ ሲሆን የብሔራዊ መታወቂያ ካርዱን ማግኘት የሚፈልጉ ዜጎችም አገልግሎቱን ለማግኘት በአካል መገኘት ይኖርባቸው ነበር። አሁን ግን ዜጎች አገልግሎቱን በቀላሉ ማግኘት እንዲችሉ የኦንላይን ምዝገባ የተጀመረ ሲሆን የክፍያ ሥርዓቱም በቴሌ ብር እና በባንክ መክፈል እንደሚቻል ተጠቁሟል።

የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ማግኘት የሚፈልጉ ዜጎች card-order.fayda.et ድረ ገጽ ላይ በኦንላይን መመዝገብ እንደሚችሉ ሲገለፅ ፥ በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት በኩል ካርዱን ባሉበት ቦታ እንዲመጣላቸው ማዘዝ ይችላሉ ተብሏል። ዜጎች ምዝገባ ከማድረጋቸው በፊት የፋይዳ ቁጥራቸውን የሚገልጽ የጽሑፍ መልዕክት በስልካቸው ስለመላኩ ማረጋገጥ እንደሚኖርባቸውም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine
25.2K viewsedited  09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ