Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Samitech
Cloudbridge
Traininginstitute
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.23K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 244

2022-05-19 22:19:53 የጉማ ሽልማት ፦

የህይወት ዘመን ተሸላሚ
ፕሮፌሰር ሳሌም መኩሪያ

በምርጥ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ምርጥ ድርሰት
እረኛዬ (ቅድስት ይልማ፣ አዜብ ወርቁ፣ ቤዛ ሀይሉ)

ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ምርጥ ተዋናይ
" በእግር እሳት" ብርሀኑ ድጋፌ

ምርጥ የቴሌቪዥን ተከታይ ድራማ ዳይሬክተር
አብርሐም ገዛኸኝ በ "እግር እሳት "

በምርጥ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ እረኛዬ

በምርጥ ሴት ተዋናይት
ሳያት ደምሴ አሸናፊ " እረኛዬ "

ዘንድሮ በጉማ ሽልማት ለመጀመሪያ ጊዜ መሰጠት የጀመረውን "የሄርሜላ ሽልማት" የመጀመሪያዋ ተሸላሚ ዓለም ፀሐይ በቀለ ።

የአመቱን ምርጥ ኤዲተር
ዳንኤል ግርማ " ምን አለሽ "ፊልም

በምርጥ ረዳት ተዋናይ አሽናፊ
ሽመልስ አበራ

የአመቱ ምርጥ ሴት ተዋናይት
አምለሰት ሙጬ "ምን አለሽ" ፊልም

የአመቱ ምርጥ ተዋናይ
እንግዳሰው ሀብቴ

የአመቱ ምርጥ ፊልም
"ማንያዘዋል"

ኑር አክመል በ "ማንያዘዋል"ፊልም የአመቱ ምርጥ ዳይሬክተር

ምንጭ፦ ያሬድ ሹመቴ

@tikvahethmagazine
31.7K viewsedited  19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 18:09:03
በአዲስ አበባ የሚገኙ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮችን የማጽዳትና የመጠገን ሥራ እየተሰራ ነው ተባለ።

በአዲስ አበባ የጎርፍ አደጋ ሥጋት ያለባቸው ሥፍራዎች የሚገኙ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮችን የማጽዳትና የመጠገን ሥራ እየተሰራ መሆኑን የመዲናዋ የመንገዶች ባለሥልጣን አስታውቋል።

ከመንገድ ግንባታና ጥገና በተጨማሪ ተቋሙ ጽዳትና ጥገና ለሚያስፈልጋቸው ከ400 ኪሎ ሜትር በላይ ‘የፍሳሽ መስመር ጽዳትና ጥገና መደረጉን የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር እያሱ ሰለሞን ገልጸዋል።

መጪው የክረምት ወቅት ከባድ ዝናብ እንደሚኖር የሚቲዎሮሎጅ ትንበያ እንደሚያመለክት ኃላፊው ገልጸው ይህንንም ተከትሎ የአደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን በለያቸው ሥፍራዎች የሚገኙ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮችን የማጽዳትና የመጠገን ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ይሁን እንጂ ኅብረተሰቡ ለጽዳት ተብሎ የፍሳሽ ማስወገጃ ቦይ ክዳኖች በሚከፈቱበት ወቅት ደረቅ ቆሻሻዎችን በማስወገድ መስመሮች እንዲዘጉ በማድረግ ችግሩን ማባባሱን ገልጸዋል። እስካሁን 42 ቦታዎች ላይ ጥገናና ጽዳት እየተደረገ በመሆኑ ኅብረተሰቡ እነዚህን ቦታዎች ህገ-ወጥ ተግባራት ከሚፈጽሙ ሰዎች እንዲከላከል ጠይቀዋል።

@tikvahethmagazine
33.6K viewsedited  15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 17:31:46
የቡናና ሻይ ህንፃ የፍሳሽ ማስወገጃ ስራ ላይ በተሰማሩ ሰራተኞች ላይ አፈር ተደርምሶ ጉዳት ደረሰ

ሜክሲክኮ አካባቢ በሚገኘው የቡናና ሻይ ህንፃ የፍሳሽ ማስወገጃ ለመቀየር እየሰሩ በነበሩ የቀን ሰራተኞች ላይ በተሰማሩ ሰራተኞች ላይ አፈር ተደርምሶ ጉዳት ደርሷል።

በዚህም በአምስት ሰራተኞች ላይ ቀላል ጉዳት ሲደርስ የአፈሩ የተደረመሰበትን አንድ ሰራተኛ የማውጣት ስራ እየተከናወነ እንደሆነ ይገኛል ሲል #ኢብኮ ዘግቧል።

የኮንስትራክሽን ደህንነት አጠባበቅ ችግር ለአደጋው መንስኤ እንደሆነ ሰራተኞቹ የተናገሩ ሲሆን የህንፃውን የፍሳሽ ማስወገጃ ኮንትራት ወሰዶ እያከናወነ የሚገኘው የደበበ ክንፈ ህንፃ ስራ ተቋራጭ ኢንጂነሮች በበኩላቸው አደጋው በአጋጣሚ የደረሰ እንደሆነ ገልፀዋል።

@tikvahethmagazine
29.9K viewsedited  14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 17:31:22
#CrohnsandColitisEthiopia #TikvahEthiopia

በኢትዮጵያ ስለ አንጀት ቁስለት ህመም እንዲሁም ተያያዥ የጤና ጉዳዮች ላይ የሚሰራው በክሮንስ እና ኮላይተስ ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር አንጀት ቁስለትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ መረጃዎችን ለማድረስ ተስማምተዋል።

ክሮንስ እና ኮላይተስ ኢትዮጵያ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በጉዳዩ ላይ የተለያዩ መረጃዎችንና ውይይቶችን በ Tikvah Magazine ቻናል ላይ ይዞላችሁ ይቀርባል። ለሚኖሯችሁ ጥያቄዎች የባለሞያ ምላሾችንም ያደርሳል።

ዘወትር ዕሮብ በክሮንስ እና ኮላይተስ ኢትዮጵያ ተዘጋጅተው የሚቀርቡ መረጃዎችን መከታተልና ጥያቄዎችንና ተሞክሮዎችን ማድረስ እንዲሁም ጠቃሚ መረጃዎችን ከድርጅቱ ድረገጽ ( http://ibdeth.org ) ላይ ማግኘት ይችላሉ።

@tikvahethmagazine @ibdeth
28.2K views14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 17:30:53
#ልባምሕይወት

ልባም ሕይወት የአዕምሮና ራስን የማሳደግ ስልጠና 6ኛ ዙር ኦንላይን ምዝገባ ተጠናቆ ስልጠና ሊጀመር ነው።

ሆኖም ቀሪ ባሉት የተወሰኑ ቦታዎች ሰልጣኞችን መቀበል እንፈልጋለን። ስልጠናው ከግንቦት 23 እስከ ሰኔ 25 ይሰጣል።

ለአምስት ሳምንታት፣ በሳምንት ሦስት ቀናት፣ ምሽት ከ3:00 - 5:00 ሰዓት በሚሰጠው የአዕምሮና ራስን የማሳደግ ስልጠና በመዝገብ የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ።

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ወይም ቴሌግራም ቁጥር +251974046870 ይደውሉ ወይም ስምዎን ቴክስት ያድርጉ




https://t.me/libamhiwot
24.5K views14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 15:53:53
ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ የአለም ዋንጫን እንዲመሩ ከተሾሙ ዳኞች ውስጥ አለመካትቱ ታውቋል።

በኳታር አዘጋጅነት በ 2022 ለሚካሄደው የአለም ዋንጫ ፊፋ 36 ዋና ዳኞችን 69 ረዳት ዳኞችን እና 24 የቫር ዳኞችን ውድድሩን እንዲመሩ መሾሙን አስታውቋል።

ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ ፊፋ የአለም ዋንጫን እንዲመሩ ከሾማቸው ዳኞች ስም መካከል #አለመካትቱ ታውቋል።

ፊፋ ለመጀመሪያ ጊዜ በኳታር አዘጋጅነት በሚካሄደው የአለም ዋንጫን ላይ ሶስት ዋና ሴት ዳኞችን እና ሶስት ረዳት ሴት ዳኞችን ውድድሩን እንዲመሩ መምረጡ ተገልጿል ።

የአለም ዋንጫን ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲመሩ ከተመረጡ ሶስት ሴት ዳኞች መካከል አንዷ ሩዋንዷዊቷ ሳሊማ ሙካንሳንጋ መሆኗ ተዘግቧል።

አፍሪካን ወክለው የአለም ዋንጫን እንዲመሩ የተመረጡ ስድስት ዋና ዳኞች ሳሊማ ሙካንሳንጋ ፣ ጃኒ ሲካዝዌ ፣ ባካሪ ጋሳማ ፣ ቪክቶር ጎሜዝ ፣ ማጉዬቴ ኒዳዬ እና ሙስጣፋ ጎርባል መሆናቸው ተነግሯል።

Via @tikvahethsport

@tikvahethmagazine
25.8K viewsedited  12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 15:47:18
#DireDawa

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ጥቂት ቀናት ከወትሮው የተለየ ከፍተኛ የሆነ የሙቀት መጠን እንየተስተዋለ መሆኑን ጠቁሟል። ይህን አስመልክቶም የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ለነዋሪዎችም የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፏል።

በተለይም አረጋውያን እና የተለያዩ ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው (ከፍተኛ ደም ግፊት፣የስኳር ህመም፣ የልብ ህመም፣ የኩላሊት ህመምና ሌሎችም)፣ እራሳቸውን መንከባከብ የማይችሉ የአይምሮ ህሙማን እና ህፃናት በተለየ መልኩ የጥንቃቄ መልእክቶች ተግባራዊ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል።

በዚህም፦

1. ወቅታዊው ከፍተኛ የሙቀት መጠን እስኪያልፍ መኖሪያ ቤትዎን በተለያዩ መንገዶች ማቀዝቀዝ፣

2. እቤትዎ በሚሆኑበት ግዜና በእንቅልፍ ወቅት የቤትዎን መስኮትና በር ክፍት ማድረግ፣

3. በቤትዎ የአየር መታፈን እና ከፍተኛ ሙቀት በሚኖርበት ወቅት ከቤትዎ ውጪ/በረንዳዎ ላይ መቆየት፣

4. ጥም ባይኖርቦትም በቂ ፈሳሽ/ውሃ/ መውሰድ፣

5. አመጋገብዎን ማስተካከል(ስብና ቅባት የበዛባቸው ምግቦችን መቀነስ)፣

6. ቀለል ይሉ አካላዊ እንቅስቃሴዎችን ጥላማ በሆኑ ቦታዎች ላይ መስራት፣

7. የአልኮል መጠጦችን አለመጠቀም/መቀነስ፣

8. ህፃናትን እና የአዕምሮ ህሙማንን በተዘጉ/አየር በሌላቸው ክፍሎች ለብቻ አለመተው፣

9.የተለያየ ህመም ማለትም እንደ ከፍተኛ ደም ግፊት፣ ስኳርና የልብ ህመም ካለብዎ የህክምና ክትትልዎን በሚገባ ያድርጉ፣ የታዘዘሎትን መድሃኒት በትዕዛዙ መሰረት ይውሰዱ ሲል ከሙቀቱ ጋር ተያይዘው ከሚከሰቱ የጤና ችግሮችና ድንገተኛ ህልፈት ነዋሪዎች ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን እንዲጠብቁ የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ገልጿል።

@tikvahethmagazine
24.2K viewsedited  12:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 13:43:00
በዓመት ከ10 ሺ ቶን በላይ የፕላስቲክ ቆሻሻ መልሶ ጥቅም ላይ የሚያውል ኩባንያ ሊቋቋም ነው።

ኩቢክ ኢትዮጵያ የተሰኘው መቀመጫውን በሀገረ አሜሪካ ያደረገው የፕላስቲክ አምራች የግል ኩባንያ በዓመት ከ10,000 ቶን በላይ የፕላስቲክ ቆሻሻ እንደገና ጥቅም ላይ ማዋል የሚችል ፋብሪካ በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመስራት ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።

ኢንቨስትመንቱ በዓመት 125,000 ሜትሪክ ቶን የካርበን ልቀትን መቀነስ የሚያስችል ሲሆን በኢትዮጵያ ላለውም የግንባታና የሪል ስቴት ገበያ በተመጣጣኝ ዋጋ የግንባታ ቁሳቁሶችን ለማቅረብ ያስችላል ተብሏል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ከ10,000 በላይ ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ የስራ እድሎችን ለዜጎች የሚፈጥር ኩባንያ ነው ተብሎ ይጠበቃል፡፡ (IPDC)

@tikvahethmagazine
25.8K viewsedited  10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 13:21:35
#YegaraPortal

ጀማሪ ንግድ ፈጣሪዎችን እና ኢንቨስተሮችን ለማገናኘት በሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አማካኝነት ለአገልግሎት የበቃው የጋራ ፖርታል በአስር ወራት 346 ጀማሪ ንግዶችን እና 63 ኢንቨስተሮችን አገናኝቷል ተብሏል።

ከጅምር የንግድ ሃሳቦቹ በታዳሽ ኃይል እና በአይ.ሲ.ቲ የቀረቡት ከፍተኛውን ቁጥር ሲይዙ 108 ዓለማቀፍ የንግድ ኃሳቦች፣ 238 የአገር ውስጥ ገበያን መሠረት ያደረጉ፣ 257 በወጣቶች የተጀመሩ ፣ 109 ደግሞ በሴቶች የሚመሩ ንግዶች በ የጋራ ፖርታል ተመዝግበዋል፡፡

https://yegara.org/

@tikvahethmagazine
25.4K viewsedited  10:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-19 11:53:37
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ  የአያት መንድር ነዋሪዎች ያለሙት የሕዝብ መናፈሻ እየፈረሰ ነው

በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክፍል ከተማ  አያት መንድር የዞን 8 ነዋሪዎች ሕጋዊ ካርታ አውጥተው ያለሙት የሕዝብ መናፈሻ ያለ ምንም ማስጠንቀቂና ሕጋዊ ማስረጃ በትራክተር እየታረሰ መሆኑን ፓርኩን ያለሙት የመንደሩ ነዋሪዎች ገልጸዋል ሲል አዲስ ማለዳ ዘግቧል፡፡

እንደነዋሪዎቹ ገለጻ ከሆነ፣ ከ15 ዓመት በላይ ያለሙት የሕዝብ መናፈሻ ወይም ፓርክ ከነዋሪዎች በተዋጣ ገንዘብ በአረንጓዴ ልማት የተሸፈነና የሸክላ ሴራሚክስ የተነጠፈለት ነው፡፡

ይሁን እንጅ ዛሬ ማለዳ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ይዘን ነው የመጣነው ያሉ ፖሊሶች ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ ሰራተኞችና አንድ ትራክተር አሰማርተው ፓርኩን እያፈረሱ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ሕጋዊ ካርታ አውጥተው ከ15 በላይ በመናፈሻነት የተጠቀሙት ፓርክ እንደሚፈርስ ምን አይነት ማስጠንቀቂያም ይሁን መረጃ እንዳልተሰጣቸውም ጭምር ነው የተናገሩት፡፡

የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ይዘን ነው የምናፈርሰው ያሉት የመንግሥት አካላት ማዘዣውን ለፓርኩ ባለቤት ለሆኑት ነዋሪዎች እንዲሳዩ ቢጠየቁም የፍርድ ቤት ማዘዣ ማሳየት አልቻሉም ተብሏል፡፡

ፓርኩን የሚጠቀሙ ከ400 በላይ አባዋራዎች ሲሆኑ፣ ፓርኩን ያለሙት ሕጋዊ ካርታ በማውጣትና ብር በማዋጣት እስከዛሬ ድረስ በጋራ ሲጠቀሙበት ቆይተዋል፡፡ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ከመንግሥት በኩል የተሰጠ አስተያየት በዘገባው አልተካተተም።

@tikvahethmagazine
26.2K viewsedited  08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ