Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Samitech
Cloudbridge
Traininginstitute
Silver
Platinum
Golden
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.23K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 243

2022-05-21 10:52:24
#እንድታውቁት

ዛሬ በ13/09/2014 ዓ.ም ለጎንደር ከተማ ከእንጨት ወደ ኮንክሬት ፖል ለመቀየር በሚሰራው ስራ ጎንደር መጋቢ መስመር ከ2:30-900 ሰዓት የሚቋረጥ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጎንደር ዲስትሪክት ገልጿል።

በዚህም የሚቋረጥባቸው አካባቢዎችም፦

- አዘዞ ት/ቤት አካባቢ፣
- አባሳሙኤ ኮንዶሚኔም አካባቢ፣
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በከፊል፣ ጂቲዜድ አካባቢ፣
- ቀበሌ 16 በከፊል፣
- ቀበሌ 14፣15፣1፣2 መሉ በሙሉ እና 3 በከፊል መሆኑ ነው የተገለጸው።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
23.0K viewsedited  07:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 10:45:35
የአዲስ አበባ ሕንፃዎች ቀለም ግራጫ እንዲሆን ተወስኗል በሚል የወጣውን መረጃ አስተዳደሩ አስተባበለ።

በከተማው ለሚገኙ ሕንፃዎች ቀለማቸው ወጥ የሆነ ስታንዳርድ ለማዘጋጀት ላለፈው አንድ ወር ጥናት ተደርጎ አብዛኞቹ ሕንፃዎች ቀለማቸው ግራጫ ቀለም ያላቸው መሆኑን መረጋገጡንና የአዲስ አበባ ከተማ ሕንፃዎች ቀለም ግራጫ እንዲሆን መወሰኑ የከተማዋ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ቢሮ ኃላፊ መናገራቸው ተዘግቦ ነበር።

ሆኖም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ዮናስ ዘውዴ ይህንን ጉዳይ አስተባብለዋል። እስካሁን ድረስ የከተማዋ ህንጻዎች ቀለም ምን አይነት ይሁን የሚለው ጉዳይ ለውይይት ቀረበ እንጂ የከተማ አስተዳደሩ በጉዳዩ ላይ ምንም አይነት ውሳኔ እንዳላሳለፈ ለኢፒድ ገልጸዋል፡፡

ከተማዋ ላይ አንድ አይነት ቀለም ብቻ ለቀለም ቅብ ሥራ ያስፈልጋል የሚል እሳቤ መያዝ እንደሌለበት የተናገሩት ኃላፊ፤ ለአስፈላጊው ህንጻና አካባቢ የሚመጥን ዝብርቅርቅ ያልሆነና ለዓይን የሚማርኩ ቀለማትን የያዘ ስታንዳርድ እንደሚኖረን ይጠበቃል ሲሉ ተናግረዋል።

ውሳኔው የከተማው ነዋሪ ምክርና ስምምነት ያስፈልገዋል፤ በሂደቱ ላይም በርካታ ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉና ተወያይቶ መግባባት ላይ መድረስን እንደሚጠይቅ ኃላፊው ጠቁመዋል።

ኃላፊው ጉዳዩን ''በማህበራዊ ትስስር ገጾች የሚናፈሰው መረጃ ከዕውነት የራቀ ነው'' በሚል የገለጹ ቢሆንም የዚህ መረጃ ምንጭ ግን ሪፖርተር ጋዜጣ በረቡዕ ዕትሙ የከተማዋ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ቢሮ ኃላፊ አቶ ስጦታው አካለን ጠቅሶ ያወጣው ነው።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
21.4K viewsedited  07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 10:45:04
የት ለመማር ወሰኑ?

በ Software Engineering እና በ Information Technology and Systems በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርቶን ለመማር ወደ #ቢትስኮሌጅ ቢመጡ አብዝተው ያተርፋሉ።

በ4 ዓመት ውስጥ በዲግሪ ብቻ ሳይሆን ብቁ ሰራተኛ ሆነው ጭምር ይመረቃሉ።

ጥራታቸውን የጠበቁና የመማር ማስተማር ሂደቱን የሚያግዙ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው መምህራን፣ በዘመናዊ መልክ የተደራጁ መማሪያ ክፍሎች፣ ቤተመፃህፍት፣ የኮምፒዩተር ላብራቶሪዎች እና እጅግ ዘመናዊ የአይቲ መሠረተ ልማት #በቢትስኮሌጅ የተሟሉ ናቸው።

ለማመልከት እና ለበለጠ መረጃ፦

ድረ ገጽ www.bitscollege.edu.et

0982 363636 / 0978028655

#BITSCollege
20.8K views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-21 10:45:04
ኢትኤል ዲዛይን ❖ Ethel Design

ለመኖርያ ቤት ለቢሮ ለንግድ ቦታዎ ውብ እና ማራኪ የሆኑ ዲዛይኖችን በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ካለው የፊኒሺንግ ስራ ጋር ሰርተን እናስረክቦታለን። ይደውሉልን።

የምንሰጣቸው አገልግሎት
የዲዛይን እና የፊኒሺንግ ስራ
የእንጨት ፓርቲሽኖችን መስራት
አጠቃላይ የእንጨት ስራ
ብራንዲንግ

Contact us @etheldesign1
0939902740
0919361804

Telegram: t.me/etheldesign
22.2K views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 23:32:49 #የዛሬ (ግንቦት 12/2014)

በሲዳማ ክልል እና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ዳግም የፀጥታ ችግር እና ግጭት አገርሽቶ የሰዎች ህይወት ማለፉን የአከባቢው የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ከበንሳ ጠቁመዋል። ከሁለቱም ክልል የሚመለከተው አካል እንዲሁም የፌደራል መንግስት የህዝቡን ደህንነት እንዲያስጠብቅና ግጭቱን እንዲቆም መፍትሄ እንዲፈለግም አሳስበዋል።

በ2021 በኢትዮጵያ ግጭት እና ሁከት ከ5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል። ይህ ቁጥር ከቀደመው ዓመት በ3 እጥፍ ይበልጣል። በIDMC ሪፖርት መሠረት በትግራይ ክልል 1.8 ሚሊዮን፣ በአማራ ክልል 1.7 ሚሊዮን፣ በኦሮሚያ ክልል 643 ሺ ተፈናቃዮች ተመዝግበዋል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሀራ በርሀ በታች በሚገኙ አገራት የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ14 ሚሊዮን በላይ ደርሷል።

የብርጋዴር ጀኔራል ተፈራ ማሞ " ህገ መንገስቱን በኃይል በመናድ ወንጀል " በሚል ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ሂደቱን የተመለከተው የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት የፌደራል ፖሊስ ከጠየቀው የ14 ቀን ውስጥ 10 ቀን በመፍቀድ ለግንቦት 22 ቀን 2014 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በህንድ አዘጋጅነት ለሚካሄደው የአለም ከ 17 አመት በታች የሴቶች የአለም ዋንጫ ለማለፍ በአፍሪካ ዞን እየተደረገ በሚገኘው የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ የሴቶች ከ 17 አመት ብሄራዊ ቡድን በናይጄሪያ አቻው 1 : 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል። ቡድኑ ግንቦት 27 በናይጄሪያ በሚካሄደው የመልስ ጨዋታ ላይ ውጤቱን መቀልበሰ ከቻለ በህንድ አዘጋጅነት በሚካሄደው የአለም ዋንጫ ላይ ተሳታፊ መሆናቸውን የሚያረጋግጡ ይሆናል።

ትላንት ሀሙስ አመሻሽ ላይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ስር ከሚገኘው የአሶሳ ማረሚያ ቤት 17 ተጠርጣሪዎች ማምለጣቸውን የዞኑ ማረሚያ ቤት መምሪያ አሳውቋል። ከማረሚያ ቤቱ ያመለጡት ግለሰቦች " በወቅታዊ ሁኔታ እና በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ምክንያት " ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ናቸው ተብሏል። ከዚሁ ማረሚያ ቤት ከሶስት ወር በፊት የቀድሞው የቤኒሻንጉል ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ መሪ አቶ አብዱልዋሀብ መሀዲ በተመሳሳይ ሁኔታ ማምለጡ ይታወሳል።

'ሴንሆን የማር ምርቶች' እና 'ሮም የገበታ ጨው ' የጤና ብቃት ማረጋገጫ ባለማግኘታቸው ከገበያ እየተሰበሰቡ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን አሳውቋል።

በኢትዮጵያ ውስጥ በኮሜዲ ዘርፍ ከታዩ እጅግ ተወዳጅ እና ምርጥ ኮሜዲያኖች እንዱ እንደሆነ የሚነገርለት ኮሜዲያን ወንድወሰን ብርሃኑ ( #ዶክሌ ) በ57 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየቱ ተሰምቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ እና ግብፅ ጋር ለሚያደርጋቸው የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታዎች ዝግጅት ለሀያ ስምንት ተጫዋቾች ጥሪ ተደርጓል፡፡ ዋልያዎቹ ግንቦት 25 እና 29 ከማላዊ እና ግብፅ ብሔራዊ ቡድኖች ጋር የ 2023 የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ የጨዋታቸውን በቢንጉ ስታዲየም የሚያከናውኑ ይሆናል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2014 ዓ.ም የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የአካዳሚክ ካላንደር ማሻሻያ ያደረገ ሲሆን የ8ኛ ክፍል ከተማ ዐቀፍ ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 29/2014 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል ብሏል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
6.2K viewsedited  20:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 23:03:53
#Benishangulgumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል ዞን በማንዱራ፣ ዳንጉር እና ፓዊ ወረዳዎች የ76 ንጹሃን ዜጎችን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲጠፋ ያደረጉ ተከሳሾች እንደየወንጀል ተሳትፏቸው ከእድሜ ልክ ጀምሮ በጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነ፡፡

ተከሳሾቹ በተጠቀሱት አካባቢዎች የእርስ እርስ ጦርነት እንዲነሳና ብሔር-ተኮር ግጭት እንዲቀሰቀስ በማድረግ የ76 ንጹሃን ዜጎች ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲጠፋና ከፍተኛ ንብረት እንዲወድም ማድረጋቸው ተነግሯል።

ተከሳሾች ዜጎችን ወይም በአገር ነዋሪ የሆኑትን በማሰታጠቅ፣ በወረዳዎቹ በ2011 ዓ.ም ከታህሳስ እሰከ ሰኔ ወር አጋማሽ ድረስ ብሔር ተኮር ግጭትን ቀስቅሰዋል፡፡

በ20 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት እንዲደርስ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከቤት ንብረታቸዉ እንዲፈናቀሉ በማድረግ እና ግምቱ ከፍተኛ የሆነ ንብረት እንዲዘረፍ እና እንዲወድም በማድረግ የወንጀል ድርጊት ዉስጥ በመሳተፋቸው በፈጸሙት ወንጀል በዓቃቤ ህግ ተከሰዋል፡፡

የፌዴራል ዓቃቤ ህግ የተከሳሾችን ጥፋተኝነት የሚያረጋግጡ ማስረጃዎቹን አቅረቦ ለፍርድ ቤቱ ያሰማ ሲሆን÷ ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ከነበሩ 29 ተከሳሾች መካከል 3ቱ የቀረበባቸውን ክስ እና ወንጀል መከላከል በመቻላቸው በነጻ ተሰናብተዋል፡፡

ግንቦት 12 ቀን 2014 ዓ.ም. በዋለዉ ችሎት 4 ተከሳሾች ላይ የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት፤ 1 ተከሳሽ በ 25 ዓመት፤ 1 ተከሳሽ በ 23 ዓመት ጽኑ እስራት፤ 17 ተከሳሾች በ 22 ዓመት፤ 2 ተከሳሾች በ 20 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡና 1 ተከሳሽ ዕድሜዉ ለአካለ መጠን ያልደረሰ በመሆኑ በልዩ ሁኔታ በ 8 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ፈርዷል። እንዲሁም ሁሉም ተከሳሾች ከሲቪል መብቶቻቸዉ ለ 5 ዓመት መታገዳቸውን ፍትሕ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

@tikvahethmagazine
8.2K viewsedited  20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 15:22:55
የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ አስረከበ።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ በመሸንቲ ሳይት ተደራጅተው ለቆዩ 196 ማኅበራት የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ አስረክቧል።

በመሸንቲ ሳይት 3 ሺህ 806 አባላትን ያቀፉ 185 ማኅበራት፣ 261 አባላትን ያቀፉ 11 የአርሶ አደር ልጆች ማኅበራት በድምሩ 196 ማኅበራት፣ 4 ሺህ 67 አባላት የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ ተረክበዋል።

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ሀላፊ ኃይለእየሱስ ፀጋዬ አዲስ ከተማን የመመስረት ተግባር እየተሠራ በመሆኑ ውኃ፣ መብራት፣ መንገድና ሌሎች የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። መንግሥት ለሚያከናውናቸው ሥራዎች ሁሉ ማኅበራትም የበኩላቸውን ድጋፍ እዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ለማኅበራት ቦታ መስጠት ብቻ ሳይሆን ከተማ አሥተዳደሩ አስፈላጊውን ማሽነሪና ሌሎች ድጋፎችን እንደሚያደርግ ኀላፊው ቃል ገብተዋል። በተለይ ለግንባታ አስቸጋሪ አካባቢ የገጠማቸው ማኅበራት ከተማ አሥተዳደሩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

በተመሳሳይ ሁኔታ በዘንዘልማ ሳይት ተደራጅተው የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታን ለሚጠባበቁ ማኅበራት በበጀት ዓመቱ ምላሽ ለመስጠት እየሠራ መሆኑን ሀላፊው ተናግረዋል።

ለመኖሪያ ቤት መሥሪያ ግንባታ ቦታቸውን የሚለቁ አርሶ አደሮች ልጆቻቸው በማኅበር በመደራጀት ቦታ እንዲሰጣቸው መደረጉን አቶ ኃይለእየሱስ ተናግረዋል ሲል የዘገበው አሚኮ ነው።

@tikvahethmagazine
24.0K views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 15:20:41
5 ሺህ ሄክታር ስፋት ያለው የአባያ ሃይቅ ክፍል በእምቦጭ ተወሯል ተባለ

የደቡብ ክልል የአከባቢና ደን ባለስልጣን የብዘሃ ህይወት ልማትና ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ኃላፊ አቶ መላኩ ባፋ ፥ እምቦጭ አረም የአባያ ሀይቅን በስፋት እያጠቃ መሆኑን ገልፀው፥ አረሙን ለማጥፋት የሚያስችሉ ስራዎችና ሙከራዎች በሰው ጉልበትና በመሳሰሉት ለመግታት ጥረት ቢደረግም ሊሳካ አልቻለም ብለዋል፡፡

በዚህም በሀይቁ ላይ ያለውን ብዘሃ ሕይወት በማይጎዳ መልኩ አረሙን የማጥፋት ዘመቻ ለማካሄድ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።

አረሙ በፍጥነት ካልተወገደ ከሀይቁ በሚገኝ ገቢ የሚተዳደሩትን በርካታ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ገቢ በማሳጣት ሊጎዳ እንደሚችል ተገልጿል።

የእንቦጩ መስፋፋት ከኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ተባብሮ ለመስራት እንዲያስችል ከስምጥ ሸላቆ ተፋሰስ ባለስልጣን ጋር በጥምረት ለመስራት ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ሃይቁ በውስጡ ከ54 በላይ ብዘሃ ሕይወትን የያዘው የአባያ ሀይቅ በዓመት ከ4 ሺህ ቶን በላይ ዓሳ የማምረት አቅም ያለውና ዓዞን ጨምሮ በነጭ ሣር ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ያሉ የዱር እንስሳትም የህልውናቸው መሰረት መሆኑ ከደ.ሬ.ቴ.ድ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡

@tikvahethmagazine
19.4K viewsedited  12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 15:20:31
የት ለመማር ወሰኑ?

በ Software Engineering እና በ Information Technology and Systems በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርቶን ለመማር ወደ #ቢትስኮሌጅ ቢመጡ አብዝተው ያተርፋሉ።

በ4 ዓመት ውስጥ በዲግሪ ብቻ ሳይሆን ብቁ ሰራተኛ ሆነው ጭምር ይመረቃሉ።

ጥራታቸውን የጠበቁና የመማር ማስተማር ሂደቱን የሚያግዙ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው መምህራን፣ በዘመናዊ መልክ የተደራጁ መማሪያ ክፍሎች፣ ቤተመፃህፍት፣ የኮምፒዩተር ላብራቶሪዎች እና እጅግ ዘመናዊ የአይቲ መሠረተ ልማት #በቢትስኮሌጅ የተሟሉ ናቸው።

ለማመልከት እና ለበለጠ መረጃ፦

ድረ ገጽ www.bitscollege.edu.et

0982 363636 / 0978028655

#BITSCollege
18.4K views12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-20 15:20:22
ኢትኤል ዲዛይን ❖ Ethel Design

ለመኖርያ ቤት ለቢሮ ለንግድ ቦታዎ ውብ እና ማራኪ የሆኑ ዲዛይኖችን በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ካለው የፊኒሺንግ ስራ ጋር ሰርተን እናስረክቦታለን። ይደውሉልን።

የምንሰጣቸው አገልግሎት
የዲዛይን እና የፊኒሺንግ ስራ
የእንጨት ፓርቲሽኖችን መስራት
አጠቃላይ የእንጨት ስራ
ብራንዲንግ

Contact us @etheldesign1
0939902740
0919361804

Telegram: t.me/etheldesign
19.6K views12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ