Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮ መረጃ - NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja_news
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 58.46K
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@biruke_promotion

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 517

2021-02-01 15:14:18
ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን እንዲያሳውቅ ተጠየቀ።

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን 'ቁርጥ' ያለ ቀን እንዲያሳውቅ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሳስቧል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ በበኩላቸው "ፈተናው የሚሰጥበትን ቀን ለማሳወቅ ለፈተናው የሚያስፈልጉት 400 ሺህ 'ታብሌቶች' ወደ አገር ውስጥ አልገቡም" ብለዋል።

ለዚህም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር እንደሚሰራና 'ታብሌቶቹ' ወደ አገር ሲገቡ ፈተናው የሚሰጥበት ቀን እንደሚወሰን ተናግረዋል።

የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን ለማቀላጠፍ በ1 ሺህ 500 የፈተና ጣቢያዎች አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል። (ENA)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
10.1K viewsedited  12:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-01 10:40:10
ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ዛሬ ጠዋት በኮልፌ ክ/ከተማ ወረዳ 10 እፎይታ የገበያ ማዕከል በመገኘት በእሣት ቃጠሎ የተጎዱ ነዋሪዎችን አነጋገሩ

በትላንትናው እለት በኮልፌና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች የተከሰተው የእሳት ቃጠሎ መነሻ በማጣራት እርምጃ እንደሚወሠድና በቃጠሎው ለተጎዱ ነዋሪዎች አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ገለፁ።

ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ዛሬ ጠዋት በኮልፌ ክ/ከተማ ወረዳ 10 እፎይታ የገበያ ማዕከል በመገኘት በእሣት ቃጠሎ የተጎዱ ነዋሪዎችን ለማፅናናትና የደረሠውን ጉዳት በአካል ተገኝተው ጎብኝተዋል።

በሁለቱም አካባቢ የተነሣው እሣት ድንገተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በንብረታቸው ላይ ጉዳት የደረሠባቸው ነዋሪዎች መፅናናት እንዳለባቸው ገልፀው የከተማ አስተዳድሩ አስፈላጊው ሁሉ ለማድረግ ከጎናቸው እንደሚቆም ወ/ሮ አዳነች
ገልፀዋል።

በአደጋው የተቃጠሉ የሱቆች እና የቤቶች ብዛት ፣ በጠቅላላው የደረሰውን ጉዳት በፖሊስ እየተጣራ ነው ያሉት ወ/ሮ አዳነች ፤ የእሳት ቃጠሎው መነሻ ለማወቅ በሚደረገው ጥረት እና ለጋራ ሰላማችን ሲባል ምንም አይነት መረጃ ያለው ሰው ለህግ አስከባሪ እና ለፖሊስ መረጃውን በመስጠት እንዲተባበር መጠየቃቸውን የከተማ አስተዳሩ መረጃ ያሳያል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
11.1K viewsedited  07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 22:31:08
#kolife_atena_tera

ኮልፌ አጠና ተራ የእሳት አደጋ ተከስቶ እንደነበርና አሁን ላይ መቀነሱ ተገለፀ!

በኮልፌ አጠና ተራ የተነሳውን የእሳት አደጋ መቆጣጠር እንደተቻለ (እሳቱም እንደጠፋ) የኮልፌ አጠና ተራ አባላት ከቪድዮ ጋር አያይዘው አሳውቀዋል።

በእሳት አደጋው የደረሰውን ጉዳት በሚመለከት በቀጥታ ጉዳዩ በሚመለከታቸው አካላት ይፋ ሲደረግ እናሳውቃለን።

ይህ ቪድዮ ከደቂቃዎች በፊት የነበረውን ሁኔታ የሚያሳይ ነው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
11.9K viewsedited  19:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 19:33:13
#Tigray!

የሴቶች ፣ ህፃናት እና ወጣቶች ሚኒስትር ወይዘሮ ፊልሰን አብዱላሂ ከመከላከያ ሚኒስቴር የሴቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜ/ጀነራል ጥሩዬ አሰፌ ጋር ትላንት ጥር 22 ቀን 2013 ምክክር ማድረጋቸው ተሰምቷል።

በወቅቱ በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ "ፆታዊ ጥቃቶች" ተፈፅሟል በሚል የተነሱ ጉዳዮችን በተመለከተ ውይይት እንዳደረጉ ነው የተገለፀው።

ጉዳዮን ለማጠራት የተቋቋመውን ግብረ ሀይል አስመልክቶ ውይይት የተደረገ ሲሆን ግብረ ሀይሉ የሴቶች፣ ህፃናት እና ወጣቶች ሚኒስቴር ፣ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግን እና መከላከያ ሰራዊትን ያካተተ መሆኑ ነው የተሰማው።

ግብረ ሀይሉም እውነተኛው ነገር ለማወቅ ምርመራ እና የማረጋገጥ ስራ እንደሚያከናውን ወ/ሮ ፊልሰን አብዱላሂ ገልፀዋል።

መረጃው የሴቶች ፣ ህፃናት እና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስቴር ነው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
12.9K views16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 15:38:04 ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል የሰጡት ሙሉ መግለጫ!

በትግራይ ላይ የተከሰተውን ወታደራዊ ግጭት አስመልክቶ “ህዝቡ ራሱን በራሱን የማስተዳደር መብቱን በተግባር ለማረጋገጥ በፅናት ስለታገለ የተቃጣበት ጦርነት” ያሉት ሲሆን አራት መንግሥታትና የክልሎች ልዩ ኃይሎች ተሳትፈውበታል ብለዋል።

አራቱ ብለው የጠሯቸው መንግሥታት እነማን እንደሆነ ባይዘረዝሩም “በዚህም ምክንያት የኃይል አለመመጣጠን አጋጥሟል” በማለት አስረድተዋል።

በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል ያለው ትግል እንደቀጠለና በክልሉ ከነበረው ሰሜን እዝ የተገኘውን ኃይል በመጠቀም እየታገሉ መሆናቸውን አስታውሰው ” በኃይል አለመመጣጠን ምክንያት ጊዜያዊ ወታደራዊ ብልጫ ስላገኙ ይህንን ሚዛን ለመለወጥ የመመከት ትግላችንን አጠናክረን እያስቀጠልን እንገኛለን።” ብለዋል።

ከዚህ ቀደም በአሁኑ ወቅት በትግራይ ውስጥ የሚካሄድ ጦርነት እንደሌለና እየተደረገ ያለው የህወሓት አመራሮችን በማደን በቁጥጥር ስር የማዋል እርምጃ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግሥት ኃላፊዎች መግለፃቸው የሚታወስ ነው።

የፌደራል መንግሥቱ ሠራዊት በኅዳር ወር አጋማሽ ላይ መቀለን ከተቆጣጠረ በኋላ በትግራይ ያካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ መጠናቀቁን መግለጹ ይታወሳል።

የክልሉ ዋና ከተማ መቀለ በፌደራል መንግሥቱ ሰራዊት ቁጥጥር መግባቱን ተከትሎ ከሰዓታት በኋላ የህወሃት ሊቀ መንበር ከሮይተርስ ጋር በመልዕክት ባደረጉት ንግግር ትግሉ እንደሚቀጥልና “ትግሉ የራስን መብት በራስ የመወሰን እንደሆነ” ተናግረው ነበር።

በትግራይ ክልል ከተከሰተው ቀውስ ጋር በተያያዘ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግና የፌደራል ፖሊስ በበርካታ የህወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣታቸው ይፋ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው። ከነዚህም አመራሮች አንዱ የህወሃት ሊቀ መንበር ደብረ ፅዮን ሲሆኑ በአሁኑ ወቅት ያሉበት አይታወቅም።

ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል በጠቀሱት ትግል “ከፍተኛ ዋጋ ጠይቋል” ያሉ ሲሆን። “የህወሃት መስራች አባላት ከሚባሉት ላለፉት 45 ዓመታት ከያዙት ህዝባዊ መስመር ፈቀቅ ሳይሉ የታገሉና የመሩ፣ ያታገሉና ብዙ ድል ያስመዘገቡ አዛውንት ነባር ታጋዮች በዚህ የወረራ ጦርነት፣ በጠላት እጅ ተጎድተውብናል። ከባድ መስዋዕትነት ከፍለዋል። አሁንም እየከፈሉ ይገኛሉ። የነዚህ ጀግኖቻችን መስዋዕትነት የበለጠ ቁጭትና እልህ ያስንቀናል እንጂ ፈፅሞ ከትግላችን የሚያቆመን አይሆንም።” ብለዋል

ዶ/ር ደብረፅዮን መስዋዕት ሆነዋል ያሏቸውን ግለሰቦች በስም ባይጠቅሱም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና አምባሳደር የነበሩት አቶ ስዩም መስፍን፣ በተለያዩ የሥልጣን ቦታ ላይ የነበሩት አቶ አባይ ጸሐዬ፣ የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ አስመላሽ ወልደሥላሴ እንዲሁም ከመከላከያ ሠራዊቱ ከድተዋል የተባሉት ኮሎኔል ኪሮስ ሐጎስ በግጭቱ ወቅት እጅ አልሰጥም በማለታቸው መገደላቸው ተነግሯል።

ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል በክልሉ ላይ ደረሱ ስላሏቸው ጥቃቶችና ዘርፈ ብዙ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በመዘርዘር ተናግረዋል።

“የትግራይ ሴቶች በተናጠልና በደቦ ይደፈራሉ። የትግራይ ሰዎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችና ነጻነቶች በከፋ መገለጫና አኳሃን ይጣሳሉ፣ ይገፈፋሉ። የትግራይ መንደሮችና ዓብያተ እምነቶች፣ የትግራይ ሰራዊት ይኑርበት አይኑርበት ሳይገዳቸው የቦምቦችና የመድፎ ዒላማ ይደረጋሉ። ውድና መተኪያ የሌላቸው ቅርሶችም ይወድማሉ፣ ይዘረፋሉ። በሚልዮን የሚቆጠር ህዝብ እንዳለ ከቀየው ወጥቶና ተፈናቅሎ የመከራ ኑሮ ይኖራል።” ብለዋል።

ደብረ ፅዮን ህዝቡ ላይ እየተፈፀመ ነው ያሉትን ወንጀል በግልፅ እንዲቃወምና እንዲያወግዝ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ጥሪ አቅርበዋል። ከዚህም በተጨማሪ በክልሉ ተፈፀመ ያሉት ወንጀል በገለልተኛ አካል እንዲጣራና ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀው ለዚህ ተጠያቂ ናቸው ብለው የጠሯቸውን የኢትዮጵያና የኤርትራ መሪዎች ወደ አለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ጥሪ አድርገዋል።

ደብረ ፅዮን በትናንትናው መልእክታቸው በአሁኑ ወቅት በርካቶች ወደ ትግሉ ሜዳ እየጎረፉ እንደሆነ ገልፀው ህዝቡ ያለ አንዳች ልዩነት “ጠላት” ብለው የጠሩትን ኃይል እንዲታገሉ ጠይቀዋል።

ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ባስተላለፈት መልእክት፣ በጦር ሜዳው፣ መድረኩም ሆነ፣ ድምፅ በማሰማትና በሌሎች መድረኮች ላይ ትግሉ እንደቀጠለ አስታውሰው “ሌሎቻችሁም በፍጥነት የትግሉን ጎራ ተቀላቀሉ።” በማለት ጥሪ አስተላልፈዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ትግሉ እስከመጨረሻ እንደሚቀጥል ባስተላለፉበት በዚህ መልዕክት “እኛ ከመሬታችን እና ከቀያችን ለቀን የምንሄድበት ሌላ ቦታ የለንምና የተሟላ ድል እስክንቀዳጅ ህዝባዊ ጦርነት ከማፋፋም ወደ ኋላ እንደማንል ወዳጅም ጠላትም ሊያውቀው ይገባል።” በማለት አፅንኦት ሰጥተዋል።

የደብረ ፅዮንን ንግግር በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም።

ምንጭ : ቢቢሲ አማርኛ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
13.9K viewsedited  12:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 14:51:02
ዶ/ር ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል ከሁለት ወራት ዝምታ በኋላ በትናትናው ዕለት በድምፂ ወያነ ትግራይ ፌስቡክ ገፅ በቀጥታ ለህዝቡ መልዕክት አስተላለፉ!

ዶ/ር ደብረፅዮን በትግራይ ላይ የተከሰተውን ወታደራዊ ግጭት አስመልክቶ "ህዝቡ ራሱን በራሱን የማስተዳደር መብቱን በተግባር ለማረጋገጥ በፅናት ስለታገለ የተቃጣበት ጦርነት" ያሉት ሲሆን አራት መንግሥታትና የክልሎች ልዩ ኃይሎች ተሳትፈውበታል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል ያለው ትግል እንደቀጠለና በክልሉ ከነበረው ሰሜን እዝ የተገኘውን ኃይል በመጠቀም እየታገሉ መሆናቸውን አስታውሰው " በኃይል አለመመጣጠን ምክንያት ጊዜያዊ ወታደራዊ ብልጫ ስላገኙ ይህንን ሚዛን ለመለወጥ የመመከት ትግላችንን አጠናክረን እያስቀጠልን እንገኛለን።" ብለዋል።

ደብረፅዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) በጠቀሱት ትግል "ከፍተኛ ዋጋ ጠይቋል" ያሉ ሲሆን። "የህወሃት መስራች አባላት ከሚባሉት ላለፉት 45 ዓመታት ከያዙት ህዝባዊ መስመር ፈቀቅ ሳይሉ የታገሉና የመሩ፣ ያታገሉና ብዙ ድል ያስመዘገቡ አዛውንት ነባር ታጋዮች በዚህ የወረራ ጦርነት፣ በጠላት እጅ ተጎድተውብናል። ከባድ መስዋዕትነት ከፍለዋል። አሁንም እየከፈሉ ይገኛሉ። የነዚህ ጀግኖቻችን መስዋዕትነት የበለጠ ቁጭትና እልህ ያስንቀናል እንጂ ፈፅሞ ከትግላችን የሚያቆመን አይሆንም።" ብለዋል።

"እኛ ከመሬታችን እና ከቀያችን ለቀን የምንሄድበት ሌላ ቦታ የለንምና የተሟላ ድል እስክንቀዳጅ ህዝባዊ ጦርነት ከማፋፋም ወደ ኋላ እንደማንል ወዳጅም ጠላትም ሊያውቀው ይገባል።" በማለት አፅንኦት ሰጥተዋል።

የደብረ ፅዮንን ንግግር በተመለከተ ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም።

(Via BBC Amharic)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
13.3K views11:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 11:09:04
ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የገቢና ወጪ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የገቢዎች ሚኒስቴር ፤ ከጥር 14 እስከ 20 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ 64,025,470.75 ብር ግምተዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ወደ ሀገር ለማስገባት እና ከሀገር ለማስወጣት ሲሞከር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው የገለጸው፡፡

የገቢ ኮንትሮባንድ ግምታዊ ዋጋ 48,382,510.75 ብር ሲሆን 17,642,960 ብር የሚገመት የወጪ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች በተለያዩ የጉምሩክ ኬላዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መካከል መድኃኒት፣ የምግብ
ምርቶች ፣ የጦር መሳሪያዎች፣ የመዋቢያ ዕቃዎች፣ የትምባሆ ውጤቶች ፣ አደንዛዥ ዕፆች እና የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ይገኙበታል፡፡

ዕቃዎቹን በጉምሩክ ሰራተኞች ፣ በፀጥታ አካላት እንዲሁም በህብረተሰቡ ርብርብ መያዝ መቻሉን ብስራት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባገኘነው መረጃ ተመላክቷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
12.8K views08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 10:45:20
የህዳሴው ግድብ ያለበት ሁኔታ ተገመገመ።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ እና በሚፈለገው መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚንስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ እና የኢትዮጰያ ኤሌክትሪክ ቦርድ አባላት በስፍራው በመገኘት መገምገማቸውን የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገልጿል።

በግምገማው መሰረትም የግድቡ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ እየተከናወነ እንደሆነና የግንባታ ሂደቱም በጥሩ ሁኔታ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ሚንስትሩና የቦርድ አባላቱ የግንባታ ስራውን ከሚያከናውኑ ኮንትራተሮች፣ ከባለሙያዎችና አማካሪዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል።

ለግድቡ መጠናቀቅ መላው ኢትዮጵያውያን ከሃገር ውስጥ እና ውጪ እያደረጉት ያለው ድጋፍ ከምን ግዜው በላይ ተጠናክሮ ቀጥሏል ሲል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አሳውቋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
11.9K views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-31 09:50:05
ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር በሚያዋስናት ፈጋግ ድንበር ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ኬላ ሥራ ጀመረ!

የኢሚግሬሽን ፣ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር በሚያዋስናት የጋምቤላ ክልል ፈጋግ ድንበር የመጀመሪያው ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ኬላ ትናንት በማስመረቅ ሥራ ጀመረ።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክታር አቶ ሙጂብ ጀማል በምረቃ ስነ- ስርዓቱ ወቅት እንዳሉት የመቆጣጠሪያ ኬላው የሁለቱ ሀገራትን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማሳደግ የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል።

በተለይም በአካባቢው ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርንና አሁን ላይ የሀገራት ስጋት የሆነውን የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ጭምር ጠቀሜታው የላቀ መሆኑን ተናግረዋል።

አሁን ላይ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ የህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ከፍተኛ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ኤጀንሲው ከ2012ዓ.ም. ጀምሮ በሀገሪቱ ጠረፋማ አካባቢዎች ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ኬላዎችን በማቋቋም ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርንና ፍልሰትን ለመቆጣጠር በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
12.2K views06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-30 18:32:03
በትራፊክ አደጋ የ24 ሰዎች ህይወት አለፈ።

በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን "ሰዴ ሙጃ ወረዳ" በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ24 ሰዎች ህይወት ማለፉን የደቡብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ዋና ክፍል ገለፀ።

መነሻውን ከባሕር ዳር ያደረገው የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ሰዴ ሙጃ ወረዳ ሲደርስ 200 ሜትር ከሚረዝም ገደል በመግባቱ ነው የ24 ሰዎች ህይወት ያለፈው።

በአደጋው ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች በደብረ ታቦር እና በፈለገሕይወት ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።

የአደጋው መንስዔ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ አብመድ ዘግቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
13.9K views15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ