Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮ መረጃ - NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja_news
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 58.41K
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@biruke_promotion

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 510

2021-03-02 12:19:05
1.2K views09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 12:00:03
#Adwa125 #Menelik_II_Square

125ኛው የአድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ በሚኒሊክ አደባባይ በተለያዩ ትዕይንቶች ታጅቦ እየተከበረ ይገኛል።

በበዓሉ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ፣ ጀግኖች አርበኞች፣ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም የጉዞ አደዋ የዘንድሮ ተሳታፊዎች እና ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡና የከተማዋ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
1.7K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 12:00:03
1.6K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 12:00:03
1.6K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-02 11:51:05
#LaLiga

መልካም የዓድዋ ድል ቀን ለኢትዮጵያዊያን ወዳጆቻችን እንመኛለን የሚል መልክት አስተላልፈዋል ከስፔን ላሊጋ!

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
1.9K views08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-01 21:55:10 መታየት ያለበት መልክት/አብይ አህመድ ለአድዋ በማስመልከት ያስተላለፉት አስገራሚ መግለጫ ይመልከቱ" on YouTube



261 views18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-01 20:25:08 ከ3 ሳምንታት በኃላ እነአቶ ጃዋር መሃመድ በአካል ፍርድ ቤት ቀረቡ

በረሃብ አድማ ላይ እንደሚገኙ የሚነገረው እነ አቶ ጃዋር መሐመድ ዛሬ ረፋድ ላይ ፍርድ ቤት ለነበራቸው ቀጠሮ ሲቀርቡ አካላቸው ደክሞ እና ከስተው መታየታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በእነ አቶ ጃዋር የክስ መዝገብ የተከሰሱ የ24 ሰዎችን የእምነት ክህደት ቃል ለመቀበል ዛሬ ጠዋት ላይ ቀጠሮ ይዞ ነበር። ከእነዚህ መካከል እነ አቶ ጃዋር መሐመድ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ 22 ሰዎች በፍርድ ቤት ተገኝተው ነበር።

ጠበቆች ደንበኞቻቸው እነ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ በቀለ ገርባ፣ ሐምዛ አዳነ እና ደጀኔ ጣፋ የረሃብ አድማ ከጀመሩ 33 ቀናት እንዳለፋቸው ለፍርድ ቤት ተናግረው፤ ደንበኞቻቸው አሁን ባሉበት ሁኔታ የእምነት ክህደት ቃላቸውን መስጠት አይችሉም በማለት ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ዐቃቤ ሕግ ተለዋጭ ቀጠሮ ቢሰጥ እንደማይቃወም ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል። በዚህም መሠረት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የፀረ ሽብር እና ሕገ-መንግሥታዊ ጉዳዮች አንደኛ ችሎት የተከሳሾችን የእምነት ክህደት ቃል ለመቀበል ለመጋቢት 6/2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
956 viewsedited  17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-01 20:22:07 #Adwa125

የአድዋ በዓልን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ይዘጋሉ።

በምኒሊክ አደባባይ የሚካሄድ ፕሮግራም እስከሚጠናቀቅ ፦

- ከደጎል አደባባይ ወደ ምኒሊክ አደበባይ የሚወስደው መንገድ ደጎል አደባባይ
- ከራስ መኮንን ወደ ምኒሊክ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ራስ መኮንን ድልድይ
- ከአፍንጮ በር ወደ ምኒሊክ አደባባይ የሚወስደው መንገድ አፍንጮ በር
- ከአዲሱ ገበያ ወደ ምኒሊክ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሰሜን ሆቴል
- ከመርካቶ በአቡነጴጥሮስ ወደ ምኒሊክ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ራስ መኮንን አደባባይ
-ከቸርችር ጎዳና ወደ ምኒሊክ አደባባይ የሚወስደው መንገድ መሀሙድ ሙዚቃ ቤት ዝግ ይሆናል፡፡

በመስቀል አደባባይ ለሚከናወነው ፕሮግራም ፦

-ከቦሌ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር
-ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ቅዱስ ኡራኤል ቤተ- ክርስቲያን
- ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሄራዊ ቤተ-መንግስት መስቀለኛ
- ከቸርችር ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሐራምቤ መብራት
- ከሚክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ለገሃር መብራት
- በሰንጋተራ ፣ በኮሜርስ ፣ በቴሌ ባር ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ኢትዩጵያ ንግድ ባንክ
- ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር ጋር ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡

ህብረተሰቡ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶች ብቻ እንዲጠቀሙ ተብሏል።

በዓሉ በሚከበርባቸው ቦታዎች ከማለዳው 11፡30 ሠዓት ጀምሮ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት ተሽከርካሪን አቁሞ መሄድ ክልክል ነው።

በሌላ በኩል

መልዕክት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ፦

- 125ኛ የአድዋ በዓልን ለመታደም ወደ ዝግጀቱ ስፍራ የሚመጡ ታዳሚዎች ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ ስለሚኖር ለፀጥታ አካላት ተባባሪ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል።

- በዓሉ በሚከበርበት ወቅት ከበዓሉ ጋር ተፃራሪ የሆኑ መልዕክቶች ፣ ህጋዊ ከሆነው የፌደራል መንግስት እና የክልል መንግስታት ሰንደቅ ዓላማ ውጪ ይዞ መንቀሳቀስ ፍፁም የተከለከለ ነው።

- ህብረተሰቡ ለጸጥታው አጠራጣሪ የሆኑ ማንኛውም ነገሮች ሲያጋጥሙት ወይም የፖሊስ አገልግሎትን ማግኘት ሲፈልግ በ011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ መስመር 991 መጠቀም ይችላል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
1.1K views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-01 18:13:09 መታየት ያለበት መልክት/አብይ አህመድ ለአድዋ በማስመልከት ያስተላለፉት አስገራሚ መግለጫ ይመልከቱ" on YouTube



762 viewsedited  15:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-01 16:44:13 የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ከየካቲት 29 ቀን 2013 ጀምሮ የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና በተሳካ መልኩ እንዲጠናቀቅ ከ4 መቶ በላይ የፖሊስ ሀይል አባላት ስምሪት እንደተሰጣቸዉ ለአሃዱ ሬድዮ ኤፍ ኤም 94.3 አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም ይፈጠሩ የነበሩ ችግሮች እንዳይከሰቱ የዲጅታል ደህንነት እና የአካላዊ ደህንነት መፈተሻዎች መዘጋጀታቸዉ ተገልጿል፡፡

ፈተና በሚካሄድባቸዉ ቀናት አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ተሟልተዋል ያሉ ሲሆን ለፈታኞች እና ለተቆጣጣሪዎች ማብራሪያ የመስጠት እንዲሁም የመፈተኛ ክፍሎችን ማዘጋጀት በስፋት እየተሰራባቸዉ መሆኑን ሀገር አቅፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ለሬድዮ ጣቢያው (አሃዱ FM 94.3) አሳውቋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
888 viewsedited  13:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ