Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮ መረጃ - NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja_news
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 58.41K
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@biruke_promotion

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 513

2021-02-26 21:25:06
በትግራይ ክልል ወንጀል የፈጸሙ ቡድኖች ከህግ ተጠያቂነት አያመልጡም!

በመግለጫው “የማይታመኑት የህወሃት ወንጀለኞች ቡድን የተሳሳተ መረጃን በመጠቀም ባለፉት ወራት በትግራይ ክልል ያለውን ውስብስብ የጸጥታ፣ የሰብዓዊና ማህበራዊ ፈተና ለመወጣት ጥረት እያደረገ የሚገኘውን ሉዓላዊውን የኢትዮጵያ መንግስት ተወቃሽ ለማድረግ እየሰሩ ነው” ብሏል።

“የመንግስት ጥረት ክልሉን ለማረጋጋትና የዜጎችን ህይወት ወደነበረበት ለመመለስ መንግስት ከሰብዓዊ ድርጅቶችና ከልማት አጋሮች ጋር ይሰራል” ብሏል።

በክልሉ የሰብዓዊ ድጋፍ የሚያደርጉ አካላት እና መገናኛ ብዙሃን ገብተው እንዲሰሩ መፈቀዱን ያስታወሰው መግለጫው፤ የፌዴራል መንግስት ተቋማት ከድርጅቶቹ ጋር በትብብር ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት አረጋግጧል።

በድርጅቶቹ የሚደረገው የሰብዓዊ ድጋፍ በሰላም ሚኒስቴር አስተባባሪነት የሚከናወን መሆኑን ገልጾ፤ በጋራ ስምምነት መሰረት 129 የሁለትዮሽና የባለ ብዙ ድጋፍ ድርጅቶች 135 ሰራተኞች በክልሉ ተንቀሳቅሰው ድጋፍ እንዲሰጡ ፈቃድ እንደተሰጣቸው ጠቁሟል።

“29 ዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች ስራ ላይ ሲሆኑ የአስቸኳይ ጊዜ ማስተባበሪያ ኮሚቴ እና የኮማንድ ፖስት አባል ሆነው እየሰሩ ይገኛሉ” ያለው መግለጫው፤ ኮማንድ ፖስቱ የሚደረገው ሰብዓዊ ድጋፍ ለሚመለከተው አካል በተዘረጋው መዋቅር በኩል እየደረሰ ስለመሆኑ የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅሷል።

በአሁኑ ወቅት ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ፣ ለአልጀዚራ፣ ለኒውዮርክ ታይምስ፣ ፍራንስ 24፣ ሮይተርስ፣ ቢቢሲና ፋይናንሺያል ታይምስ ፈቃድ የተሰጣቸው መሆኑ ገልጿል።

የሰብዓዊ መብት ጥሰትን በተመለከተ የጾታ ጥቃትን ጨምሮ የተፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን ለመመርመር መንግስት ቁርጠኛ መሆኑን ያመለከተው መግለጫው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
10.0K views18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-26 20:55:10
የኤርትራ ምላሽ ፦

የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገ/መስቀል ዛሬ ከሰዓት በኋላ በትዊተር ባሰፈሩት ጽሁፍ የአገራቸው ወታደሮች አክሱም ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ስለመግደላቸው አምነስቲ ኢንተርናሽናል ያወጣውን ሪፖርት እንዳጣጣሉት ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።

ሚኒስትሩ ኤርትራ በሪፖርቱ መቆጣቷንና የተሳሳተ ነው ያሉትን ሪፖርት ሙሉ ለሙሉ እንደማትቀበለው በመግለጽ ሪፖርቱ በአብዛኛው መሰረት ያደረገው ሱዳን ውስጥ ባለው "ሐምዳይት የስደተኞች መጠለያ" ውስጥ ያሉ 31 ግለሰቦችን ነው ብለዋል።

ሚኒስትሩ አቶ የማነ ጨምረውም ፥ "በዚህ መጠለያ ውስጥ ያሉት አብዛኞቹ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን በተገደሉበት የማይካድራው ጭፍጨፋ ተሳታፊ ሆነው የሸሹ የህወሓት ሚሊሻዎች መሆናቸው ይታወቃል" በማለት በትዊተር ገጻቸው ላይ ስፍረዋል።

የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት ከእውነት የራቀ መሆኑን በመግለጽ አገራቸው እንዳማትቀበለው አሳውቀዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
9.3K views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-26 20:45:10
የአርቲስት ጥላሁን ገሰሰ አልበም ምርቃትና ዝክረ ጥላሁን ገሰሰ ኮንሰርት ሊካሄድ ነው።

የተወዳጁ ድምፃዊ ጥላሁን ገሠሠን 80ኛ ዓመት የልደትንና ከዚህ ዓለምና ከሚወደው የሙዚቃ ጥበብ የተለየበትን 12ኛ ዓመት በማስመልከት ስለሚዘጋጀው ገጸ ብዙ ዝክር እና ድምፃዊው በሕይወት በነበረበት ጊዜ ያዘጋጀው እና ሀገሩን የመረቀበትን “ቆሜ ልመርቅሽ” የሚለውን ዘፈን ጨምሮ 10 ዘፈኖች የያዘ አልበም የማስመረቂያ መርሃ ግብር አስመልክቶ ዝግጅቱን በዋናነት የሚያስተባብሩ አዘጋጆች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ።

ከድምፃዊው ድንቅ እና አዲስ ስራዎች ሁለቱ በዛሬው እለት ለህዝብ በዩቲዩብ የሚለቀቁ ሲሆን የተቀሩት ስራዎቹ በኤስ ኤም ኤስ እና በአውታር በኩል በድረገፅ ለህዝብ ለሽያጭ ይቀርባሉ። ከዚህም ጋር አያይዞ ጥላሁንን ለመዘከር ስለሚዘጋጁት ልዩ ልዩ ዝግጅቶች “የገበታ ለሀገር” የእራት ግብዣን ጨምሮ ማብራሪያ ተሰጥቷል። ለታላቁ ድምፃዊ ስራዎችም ከሁለት ወራት በኋላ ተዘዋዋሪ ኮንሰርት የሚዘጋጅበትን እና በዝግጅቱ የሚሳተፉ ታዋቂ እና ተወዳጅ አርቲስቶችን ተለይተዋል ።

ፕሮግራሙን ያዘጋጁት ቤተሰቦቹና ቪጅ አይ ኢትዮጵያ ሲሆኑ ገቢውም ለገበታ ለሀገር ነው ተብሏል። ጥላሁን የሚወደስበት የእራት ምሽት የሚዘጋጅ ሲሆን በዚህ ምሽት እያንዳንዳቸው አስር ሰው የሚይዙ እና በአንድ ሚሊዮን ብር የሚሸጡ 300 ጠረጴዛዎች ተዘጋጅተዋል።

ምንጭ : ዳሰሳ አዲስ
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
9.3K viewsedited  17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-26 17:55:10
ወልዲያ: በ15 ቀናት ውስጥ 76 ሰዎች በእብድ ውሻ ተነከሱ!

በወልድያ ከተማ እና አካባቢው በ15 ቀናት ውስጥ በእብድ ውሻ የተነከሱ 76 ሰዎች ለህክምና ወልድያ ሆስፒታል መሄዳችው ተገልጿል።

ከተነከሱት መካከል 6ቱ ህጻናት ሲሆኑ ከአንድ ዓመት ህጻን እስከ 82 ዓመት አዛውንት ይገኙበታል ተብሏል።

በአጠቃላይ ተጎጂዎቹ 68ቱ ከወልድያ ከተማ እንዲሁም 8ቱ ከሰሜን ወሎ አምስት ወረዳዎች የመጡ መሆናቸው ተነግሯል።

ከተጎጂዎቹ መካከል ለ21 ህሙማን በወልድያ ሆስፒታል ህክምና እንደተሰጣቸው የተገለፀ ሲሆን ቀሪዎቹ ሆስፒታሉ ውስጥ ባለው የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት ምክንያት ወደ ደሴ ሆስፒታል ተልከው ህክምና እንዲያገኙ መደረጉ ታውቋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
10.0K views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-26 17:35:04
“በትግራይ ምርመራ ለማካሄድ አቅም ያላቸው ሁሉ ቢያግዙኝ ፍቃደኛ ነኝ” የኢትዮጵያ መንግስት


የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ባወጣው መግለጫ እንዳለው ከሆነ መንግስት በትግራይ “ሕግ የማስከበር ዘመቻ” ሲል የሰየመውን ጦርነት ተከትሎ በክልሉ ተፈፅመዋል የሚባሉ ወንጀሎችን ለማጣራት በሚያደርገው ጥረት ውስጥ ዓለምአቀፍ የቴክኒክ እርዳታ እንደሚቀበልና አቅም ያላቸው ሁሉ ከመንግስት ጋር በጥምረት ምርመራውን እንዲያካሄዱ ግብዣ አቅርቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
9.3K views14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-26 17:23:12
ምስራቅ ሸዋ: የባቡር ሃዲድ ብረቶችን የሰረቀው ግለሰብ ተቀጣ!

በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ የባቡር ሃዲድ ብረቶች የሰረቀው ግለሰብ በእስራት እና በገንዘብ ተቀጥቷል።

መሐመድ አባተ የተባለው ይሄው ግለሰብ ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን የካቲት 13 ቀን 2013 ዓ.ም ከለሊቱ 9 ሰዓት የታርጋ ቁጥሩ ኮድ 3 - 80256 አ.አ በሆነ አይሱዙ እና ኮድ 3 - 61468 አ.አ በሆነ ኤፍ ኤስ አር የጭነት ተሽከርካሪዎች የዘረፈውን የባቡር ሃዲድ ብረቶች ጭኖ ለመሰወር ሲሞክር በፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተነግሯል።

የምስራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የግለሰቡ ድርጊት በሰውና ሰነድ ማስረጃ በመረጋገጡ የካቲት 16 ቀን 2013 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ3 ዓመት እስራትና በ4 ሺህ ብር ቅጣት ወስኖበታል።

ግብረ አበሮቹ ለጊዜው ቢያመልጡም ለመያዝ ክትትል እየተደረገባቸው ነው ተብሏል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
8.8K views14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 17:33:27
ሱዳን ?

• ሱደን በምዕራብ ጎንደር ዞን ከቋራ እስከ አቡጢር ድረስ ሰፊ ቦታ በጉልበት ተቆጣጥራለች።

• ሱዳን በፈፀመችው ወረራ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፤ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የንብረት ዝርፊያ ተፈፅሟል።

• ከምድረገነት በቅርብ ርቀት በምትገኘው ሰላም በር ቀበሌ በርካታ የአካባበው ነዋሪዎች ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል። የአርሶ አደሮችና የባለሀብቶች ሰብል ፣ ትራክተሮችና ካምፖች ውድመትና ዝርፊያ ተፈፅሞባቸዋል።

የሱዳን ታጣቂዎች አስካሁን ድረስ "በምድረ ገነት ከተማ" በማኅበረሰቡ ላይ ትንኮሳ እያደረጉ መሆኑን እና የአካባቢው ነዋሪዎችም ስጋት እንዳደረባቸውን የምድረ ገነት ከተማ ከንቲባ አይሸሽም ጓንቼ ተናግረዋል።

የአካባቢው መስተዳደር አካላት ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ማኅበረሰቡን ለማረጋጋት ጥረት እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ሱዳን ከጥቅምት 24 በፊት ወደነበረችበት እንድትመለስ እየሠራ ነው፡፡

ነገር ግን የመንግሥት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ውጤታማነት የሚለካው ሱዳንን ወደነበረችበት መመለስ ሲቻል መሆኑን ተገልጿል።

"የእርሻ ጊዜ አልፎ" የሱዳን ታጣቂዎች ካደረሱት ጉዳት በላይ የከፋ ችግር እንዳይገጥም በተጀመረው አግባብ ፈጣን መፍትሔ እንዲገኝ ጥረቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል።

በአካባቢው የሚኖረው ማኅበረሰብ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚያሳልፈውን ውሳኔ በትግሥት እየተጠባበቀ መሆኑን ተሰምቷል።

መረጃው የተገኘው ከአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት/ ከምዕራብ ጎንደር ዞን ብልፅግና ፅህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ከሆኑ አቶ ሁናለም አሻግሬ ነው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
7.3K viewsedited  14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 16:54:04
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ላይ ውሳኔ ተላለፈ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኦብነግን አስመልክቶ ውሳኔ አስተላልፏል።

በእነ አቶ ራያል ሃሙድ በኩል ከጥር 12-15 ቀን 2013 ዓ.ም ተካሂዷል የተባለው አስቸኳይ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ስለመጠራቱ የሚያሳይ ሰነድ ያልቀረበ መሆኑን ምርጫ ቦርድ በውሳኔው አስታውሷል።

በአስቸኳይ ስብሰባው ላይ ተገኙ ከተባሉት 47 ሰዎች መሃል 10 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ብቻ በመሆናቸው በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀፅ 11.2 እና በአንቀፅ 13.1 መሠረት ምልአተ ጉባኤ ሳይሟላ የተካሄደ ስብሰባ መሆኑንም አንስቷል።

በእለቱ የተካሄደውን ስብሰባ የመሩትና የፓርቲው “ምክትል ሊቀመንበር” እንደሆኑ የተገለፁት አቶ ራያል ሃሙድ በቦርዱ ጽሕፈት ቤት በሚገኘው የፓርቲው ሰነድ ላይ የሚታወቁት በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ሲሆን የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ አህመድ ያሲን ሼክ ኢብራሂም መሆናቸውን አስታውቋል።

የፓርቲው ሊቀ-መንበር የፈፀሟቸው ጉዳዮች በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀፅ 33 መሠረት በዲስፕሊን ኮሚቴ ስለመታየታቸው የቀረበ ሰነድ ያለመኖሩንም ነው ቦርዱ የገለፀው።

በዕለቱ በተካሄደው ስብሰባ አስራ አምስት “የሽግግር ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ” እና ሶስት የውስጥ ኦዲት መመረጡን መግለፁ ስብሰባው ምልአተ ጉባኤ ሳይሟላ የተካሄደ ከመሆኑ በተጨማሪ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ስለ “ሽግግር ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ” የተደነገገ እንደሌለም ነው ምርጫ ቦርድ በውሳኔው የገለፀው።

ቦርዱ ከላይ የተገለፁት በፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አስቸኳይ ስብሰባ ተላልፈዋል የተባሉት ውሣኔዎች በሙሉ ተቀባይነት የላቸውም ሲል ወስኗል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
7.2K viewsedited  13:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 13:27:12
ፌዴራል ፖሊስ በ3 አይሱዙ የጭነት!

መኪና በሕገ-ወጥ መንገድ ከአዲስ አበባ ሊወጣ የነበረ ዘይት በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ገለፀ !

በሦስት አይሱዙ የጭነት መኪና በሕገ-ወጥ መንገድ ከአዲስ አበባ ሊወጣ የነበረ ዘይት በቁጥጥር ሥር መዋሉን ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ማስታወቁን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ቁጥጥር ሥር የዋለው ዘይት የካቲት 6 ቀን 2013 ዓ.ም ጀሞ ሚካኤል ልዩ ስሙ አንበሳ ጋራዥ አካባቢ በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለው 2 ሚሊዮን ሊትር በላይ ዘይት ቀድሞ ሊወጣ የነበረ መሆኑን ነው ፖሊስ የገለጸው።

"አፍሪካ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር" በተሰኘው ድርጅት ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባው የፓልም ዘይት በመንግሥት ፈቃድ ያገኘው በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ እንዲያከፋፍል ነበር ተብሏል።

ሆኖም በሦስት አይሱዙ የጭነት መኪና ተጭኖ ወደ ጅማ ሊወጣ ሲል በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ጅማ በር ፖሊስ ጣቢያ እና በፌዴራል ፖሊስ ትብብር በቁጥጥር ስር ውሏል።

በቁጥጥር ሥር የዋለው ዘይት 994 ጀሪካን ባለ 20 ሊትር እና 3 ሺህ ጀሪካ ባለ 3 ሊትር ፓልም ዘይት እንደሆነ ፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
8.5K viewsedited  10:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-16 10:13:05
ዘይቱን ያከማቸው አካል ታወቀ !

ከሰሞኑ በግለሰብ መጋዘን በህገወጣ መንገድ የተከማቸው 2 ሚሊዮን ጀሪከን የፓልም ዘይት መያዙ ሲገለፅ ነበር።

ነገር ግን ይህ ዘይት በማን እንዴት ሊከማች እንደቻለ ይፋዊ መረጃ ከመንግስት በኩል ሳይሰጥ ቆይቷል።

ዛሬ ማለዳ ዘይቱን ያከማቸው አፍሪካ ሃ/የተ/የግ/ማህበርና የሮዛ ዳቦ ባለቤት እንደሆነ ተሰምቷል።

የላፍቶ ክ/ከተማ ነዋሪዎች በተለያየ ግዜ ለወረዳቸው እና ለክፍለ ከተማቸው ሲያሳውቁና ሲጠይቁ መቆየታቸው ተገልጿል።

ነዋሪው አቅርቦት በማጠሩ በተፈጠረው የዋጋ ውድነት የተነሳ ወደ አከፋፋይ ድርጅቱ አፍሪካ ሃ/የተ/የግ /ማህበር በመሄድ ቢጠይቁም ያገኙት የነበረው መልስ የውጭ ምንዛሪ ስላጣን መግዛት አልቻልንም፤ ከወደብ አልተነሣም፤ መንግስት ሁኔታዎችን አላመቻቸልንም የሚል ነበር።

ነገር ግን በድርጅቱ መጋዘን የፓልም ዘይት ሲወርድና ሲራገፍ ፤ እና ከመጋዘኑ በአሳቻ ሰዓት ወደ ተለያዩ አካባቢዎች እየተጫነ ሲጋዝ በተከታታይ ማየታቸውንና ድርጊቱ አግባብ አለመሆኑን በመረዳት ለክፍለ ከተማው መጠቆማቸው ተገልጿል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
9.3K views07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ