2021-02-16 17:33:27
ሱዳን ?
• ሱደን በምዕራብ ጎንደር ዞን ከቋራ እስከ አቡጢር ድረስ ሰፊ ቦታ በጉልበት ተቆጣጥራለች።
• ሱዳን በፈፀመችው ወረራ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፤ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የንብረት ዝርፊያ ተፈፅሟል።
• ከምድረገነት በቅርብ ርቀት በምትገኘው ሰላም በር ቀበሌ በርካታ የአካባበው ነዋሪዎች ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል። የአርሶ አደሮችና የባለሀብቶች ሰብል ፣ ትራክተሮችና ካምፖች ውድመትና ዝርፊያ ተፈፅሞባቸዋል።
የሱዳን ታጣቂዎች አስካሁን ድረስ "በምድረ ገነት ከተማ" በማኅበረሰቡ ላይ ትንኮሳ እያደረጉ መሆኑን እና የአካባቢው ነዋሪዎችም ስጋት እንዳደረባቸውን የምድረ ገነት ከተማ ከንቲባ አይሸሽም ጓንቼ ተናግረዋል።
የአካባቢው መስተዳደር አካላት ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ማኅበረሰቡን ለማረጋጋት ጥረት እያደረጉ መሆኑን ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ሱዳን ከጥቅምት 24 በፊት ወደነበረችበት እንድትመለስ እየሠራ ነው፡፡
ነገር ግን የመንግሥት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ውጤታማነት የሚለካው ሱዳንን ወደነበረችበት መመለስ ሲቻል መሆኑን ተገልጿል።
"የእርሻ ጊዜ አልፎ" የሱዳን ታጣቂዎች ካደረሱት ጉዳት በላይ የከፋ ችግር እንዳይገጥም በተጀመረው አግባብ ፈጣን መፍትሔ እንዲገኝ ጥረቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል።
በአካባቢው የሚኖረው ማኅበረሰብ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚያሳልፈውን ውሳኔ በትግሥት እየተጠባበቀ መሆኑን ተሰምቷል።
መረጃው የተገኘው ከአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት/ ከምዕራብ ጎንደር ዞን ብልፅግና ፅህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ከሆኑ አቶ ሁናለም አሻግሬ ነው።
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
7.3K viewsedited 14:33