Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮ መረጃ - NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_mereja_news — ኢትዮ መረጃ - NEWS
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja_news
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 58.43K
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@biruke_promotion

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-07-05 09:32:42 በኦሮሚያ ክልል በአንድ ሳምንት ውስጥ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ18 ሰዎች ህይወት አልፏል

በኦሮሚያ ክልል ከግንቦት 19 እስከ ግንቦት 26  ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናቶች በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች የ18 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በ25 ሰዎች ላይ ከባድ እና በ36  ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን በኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ መረጃ ጥናት እና አገልግሎት ዲቪዥን ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ታደለ ሌጂሳ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

አደጋዎቹ በምዕራብ አርሲ ገዳ አሳሳ ፣ምዕራብ ጉጂ ቡሌ ሆራ ፣ምስራቅ ሀረርጌ ሆሮ ጉድሩ፣ ምስራቅ ወለጋ ሲቡ ስሬ ወረዳዎች እና ምስራቅ ጉጂ አዶላ ዋቱ ፣ሮቤ ከተማዎች እንዲሁም ሻሸመኔ ከተማ አብቹ ክ/ከተማ የደረሱ ናቸው።


አደጋዎቹ ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 8 ሰዓት የተመዘገቡ ሲሆን የሞት አደጋዎች የደረሱት በጭነት ተሽከርካሪ፣ በህዝብ ማመላለሻ ፣በሶስት እግር (ባጃጅ)እና በሞተር ሳይክል ተሸርከርካሪዎች የተከሰቱ መሆናቸው ተገልጿል፡።

የአደጋዎቹ ሁኔታ ካለፈው ሳምንት ጋር ሲነፃፀር የቀነሰ ሲሆን ፤ መንስኤዎቹ ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት፣ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር 3፣የተሽከርካሪ የቴክኒክ ችግር፣ርቀትን ጠብቆ አለማሽርከር መሆኑን ረዳት ኢንስፔክተር ታደለ ሌጂሳ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
7.5K views06:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-05 08:12:16 ዐበይት ዜናዎች

1፤ ገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ ፌደራል መንግሥቱ ለአዲስ ቤተመንግሥት ግንባታ የጠየቀው በጀት የለም ሲሉ ትናንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መናገራቸውን ዶይቸቨለ ዘግቧል። ለቤተመንግሥቱና ሌሎች በጠቅላይ ሚንስትሩ ክትትል ስር ላሉ ፕሮጀክቶች በመጽደቅ ላይ ያለ በጀት እንደሌለም አሕመድ ገልጸዋል ተብሏል። ሚንስትሩ ይህን ያሉት፣ ለአዲስ ቤተ መንግሥት ግንባታና "ገበታ ለአገር" ለተሰኙ ፕሮጀክቶች እየተሰበሰበ እንደኾነ የሚነገርለት 500 ቢሊዮን ብር በመንግሥት ቋት ውስጥ ገብቶ እንደሆነ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ እንደሆነ ተገልጧል። አሕመድ የቤተ መንግሥትና ሌሎች በጠቅላይ ሚንስትሩ ክትትል ስር የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ማሰሪያ ገንዘብ ከተለያዩ ምንጮች የተገኘና ለጠቅላይ ሚንስትሩ ፕሮጀክቶች የተሰጠ ድጋፍ መኾኑን ተናግረዋል ተብሏል።

2፤ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር ከደቡብ ሱዳን ጋር በሚያዋስኗት ድንበሮች የሚካሄደውን ኢመደበኛ የጠረፍ ንግድ ሕጋዊ እውቅና ለመስጠት የሕግ ማዕቀፍ ማዘጋጀቱን ፎርቹን ዘግቧል። ሚንስቴሩ በኢትዮጵያ-ጅቡቲ ድንበር ላይ የሚካሄደውን ኢመደበኛ ንግድ ሕጋዊ የሚያደርግ ሕግ ማዘጋጀቱን ዋዜማ ትናንት ዘግባ ነበር። ይሄው የሕግ ማዕቀፍ በኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን ድንበር ላይ የሚካሄደውን ኢመደበኛ ንግድ ጭምር እንደሚያካትት የፎርቹን ዘገባ አመልክቷል። የሕግ ማዕቀፉ ዓላማ፣ በኢትዮጵያና ደቡብ ሱዳን ድንበር ላይ ኮንትሮባንድ ንግድን መግታት ነው።

3፤ አምነስቲ ኢንተርናሽናል የሱዳን ጎረቤቶች ከሱዳኑ ግጭት በሚሸሹ ስደተኞች ላይ የመግቢያ ገደቦችን ባስቸኳይ እንዲያነሱ በምሥራቅ አፍሪካ ቢሮው በኩል ባወጣው መግለጫ ጥሪ አድርጓል። አምነስቲ፣ አገራቱ የሱዳን ስደተኞች መታወቂያ ወይም ቪዛ ባለመያዛቸው ከመግባት እንዳይከለከሉ፣ የጥገኝነት ምዝገባ እንዲያፋጥኑላቸው፣ አንዳችም አድልዖ እንዳይፈጽሙባቸውና አስፈላጊው የደኅንነት ጥበቃ እንዲያደርጉላቸው ጭምር ጠይቋል። ድርጅቱ ስደተኞቹ ከሰነድ ጋር በተያያዘ በርካታ ችግሮች እየገጠሟቸው እንደኾነ ገልጧል።

4፤ ሱዳን ከሩሲያ ተዋጊ አውሮፕላኖችን የመግዛት ፍላጎት እንዳላት የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤቱ ምክትል ሊቀመንበር ማሊክ አጋር ለአንድ የሩሲያ ጋዜጣ ጋር አጋር ተናግረዋል። ማሊክ አጋር የሱዳን ጦር ሠራዊት በሩሲያ ሥልጠና እያገኘ. መኾኑንም መናገራቸውን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ጠቅሰዋል። ምዕራባውያን በሩሲያ ላይ ማዕቀቦችን ቢጥሉባትም፣ ሱዳን ግን ክፕሩሲያ ጋር ወታደራዊና የቴክኒክ ትብብሮቿን እንደምትቀጥል አጋር ተናግረዋል ተብሏል።

5፤ የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ለዓመታት የተራዘመው ጠቅላላ ምርጫ በቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት መጨረሻ በታቀደው መሠረት ይካሄዳል ሲሉ ቃል መግባታቸውን የፈረንሳይ ዜና ወኪል ዘግቧል። ኪር ፕሬዝዳንታዊ ምርጫው ሲካሄድ፣ በዕጩነት እንደሚቀርቡ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ኪር እና የተቃዋሚ መሪ ሬክ ማቻር የአንድነት ሽግግር መንግሥቱን ቆይታ ባለፈው ነሐሴ ለሁለት ተጨማሪ ዓመታት ማራዘማቸው ይታወሳል። [ዋዜማ]

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
7.7K views05:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-05 08:11:26 መርጌታ  መንግስቱ ጥላሁን መድህኒት ፈውስ እና ጥበብ ይፈልጋሉ:
09 86 79 39 33
+251 9 18 46 04 92
በውጭ ሀገር ለሚኖሩም መምጣት ሳያስፈልግ ባሉበት እንሰራለን 
የምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል
1 ለመፍትሄ ሀብት
2 ለህማም
3 ለመስተፋቅር
4 ቡዳ ለበላው
5 ለገበያ
6 የዛር ውላጅ ለተዋረሰው
7 ነገረ ሚስጥራት(ሚስጥር የሚነግር)
8 ነገረ ራዕይ(ራዕይ የሚያሳይ)
9 ለዓቃቤ ርዕስ
10 ለመክስት
11 ለቀለም(ለትምህርት)
12 ሰላቢ የማያስጠጋ
13 ለመፍትሔ ስራይ
14 ጋኔን ለያዘው ሰው
15 ለሁሉ ሠናይ
16 ለቁራኛ
17 ለአምፅኦ
23 ለጠላት (ጠላት እንዳይጎዳ የሚያደርግ)
24 ለግርማ ሞገስ
25 መርበቡተ ሰለሞን
26 ለዓይነ ጥላ
27 ምስሐበ ንዋይ ወምስሐበ ሰብእ
28 ለሁሉ መስተፋቅር
29 ጸሎተ ዕለታት
30 ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
31 ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
32 ለትዳር የሚሆን የኮከብ ቆጠራ
33 ለድምፅ
34 ለብልት
35 በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ሰወች ደግሞ ከምንሰራቸው ስራዎች በጥቂቱ
7.5K views05:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 21:43:44
የክርስቲያን ታደለ እና የገንዘብ ሚንስትሩ ፍጥጫ!!

“ለቤተ መንግስት ግንባታ የተጠየቀ በጀት የለም፤ እየጸደቀ ያለ በጀትም የለም” የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ።

የፌደራል መንግስት “ለአዲስ ቤተ መንግስት ግንባታ ያቀረበው የበጀት ጥያቄም ሆነ እያጸደቀ ያለው በጀት አለመኖሩን” የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ፡፡ አቶ አህመድ ይህንን የተናገሩት ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 27፤ 2015 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡
በዛሬው መደበኛ ስብሰባ የፌደራል መንግስት ባቀረበው 2016 በጀት ላይ ከምክር ቤቱ የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም ከሌሎች የምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች የገንዘብ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ስብሰባ ላይ ከተነሱ ጥያቄዎች ውስጥ “ለቤተመንግስት እና ገበታ ለሀገር” ፕሮጀክቶች “እየተሰበሰበ ነው” የተባለን “500 ቢሊዮን ብር” የተመለከተው ይገኝበታል፡፡

ይህንን ጥያቄ ያነሱት የተቃዋሚው የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባል የሆኑት አቶ አበባው ደሳለው፤ የገንዘብ አሰባሰቡ “የመንግስትን አሰራር እና መመሪያ” ተከትሎ እየተፈጸመ ነው ወይ ብለዋል፡፡ እኚሁ የፓርላማ አባል፤ “ይህ ብር የመንግስት ቋት ውስጥ አለ ወይ?” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቀዋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ለዚህ ጥያቄ የተወሰነ ማብራሪያ እየሰጡ ባሉበት ወቅት ከሌላው የአብን የፓርላማ አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ ተቋርጧል፡፡ “የስነ ስርዓት ጥያቄ” ያነሱት አቶ ክርስቲያን፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ የሚሰጡት ምላሽ የምክር ቤቱን “የህግ እና የስነ ስርዓት ጉዳዮችን የጣሰ” እንደሆነ ገልጸው “እርምት እንዲደረግ” ጠይቀዋል፡፡

via (ethiopianinsider)

@ethio_mereja_news
9.2K views18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 19:16:46
ሸዋሮቢት

የሸዋሮቢት ከተማ የአስተዳደርና ፀጥታ ዘርፍ ም/ኃላፊ አቶ አብዱ ሁሴን ማንነታቸው ካልታወቁ ሰዎች በተተኮሰ ጥይት መገደላቸው ተሰምቷል።

ከስፍራው የደረሰን መረጃ ከቢሮ ወጥተው ወደ መኪና ሲገቡ ጥቃቱ እንደተፈፀመባቸው ያመለክታል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
9.8K viewsedited  16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 16:59:11
እስከ 40 ሺሕ የሚደርሱ የአማራ ተወላጆች ተገድለዋል ተባለ!!

በኢትዮጵያ የመንግሥት ለውጥ ከተደረገበት 2010 ወዲህ ባሉት ዓመታት ከ25 ሺሕ እስከ 40 ሺሕ የሚገመቱ የአማራ ተወላጆች በአክራሪ ብሔርተኞች መገደላቸውን ካውንተር ፓንች በድህረ ገጹ አስነብቧል።

ዘገባው አብዛኞቹ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በሚል በሚጠራው እና በመንግሥት “ኦነግ ሸኔ” ተብሎ በተፈረጀው ኃይል የተገደሉ መሆናቸውን መገለጹን አዲስ ማለዳ ከድህረ ገጹ ዘገባ ተመልክታለች፡፡

ከዚህ ባለፈም፤ ከአምስት እስከ ሰባት ሚሊዮን የሚደርሱ ዜጎች በየጊዜው በሚፈጠሩ ግጭቶች ምክንያት ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀላቸው ነው የተገለጸው። እንዲሁም በአገሪቱ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ከጊዜ ወደ ጊዜ አደጋ ውስጥ እየገባ ነው የተባለ ሲሆን፤ የመሰበሰብ፣የሚዲያ ነጻነት እና ሌሎች ተያያዥ ዴሞክራሲያዊ መብቶች አደጋ ውስጥ መግባታቸው ተጠቅሷል።

በዚህም ተቃዋሚ ፖለቲከኞች፣ የአገር ውስጥ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣በግልጽ የሚናገሩ ጋዜጠኞች እና የግል የሚዲያ ተቋማት በነጻነት የመናገርና የመስራት መብታቸውን አጥተዋል ሲል የካውንተር ፓንች ዘገባ አመላክቷል።

ዘገባው መሰረቱን በአሜሪካ ያደረገ“ፍሪደም ሃውስ”የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅትን መረጃ ጠቅሶ፤በኢትዮጵያ በስፋት መንግሥትን የሚተቹ አካላት ከእውቅናቸው ውጭ በሆነ መንገድ በመንግሥት የደህንነት አካላት በእጅ ስልካቸው ላይ ሳይቀር ሚስጥራዊ ክትትል እንደሚደረግባቸው ጠቁሟል።

በአገሪቱ የዘፈቀደ እስራት በተደጋጋሚ እንደሚፈጸም በመጥቀስም፤ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ አክቲቪስቶችና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሠራተኞች ከመኖሪያ ቤታቸው፣ ከሥራ ቦታቸው ወይም ከመንገድ ላይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በደህንነቶች ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ እንደሚወሰዱም ተገልጿል።
 
@ethio_mereja_news
10.1K viewsedited  13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 14:48:37 የፖሊስ ልብስ በለበሱ ሰዎች ታግቼ ነበር ያለው ሾፌር የጫነውን ንብረት መሸጡ ተደረሰበት!!

የፀጥታ ኃይል ልብስ በለበሱ ሰዎች ታግቼ ከ2 ሚሊዮን ብር  በላይ ንብረት ተዘርፍኩ ያለው አሽከርካሪ ንብረቱን  ሸጦ የሀሰት ክስ መመስረቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

አሽከርካሪው ሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ/ም የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-35747 ኢ/ት በሆነ ተሽከርካሪ አዳማ ከሚገኝ ድርጅት ግምቱ 2 ሚሊዬን 7መቶ ሰላሳ ሺ 240  ብር የሚያወጣ የፌሮ ብረት መርካቶ ከሚገኝ የግል ተበዳይ ሱቅ ለማራገፍ ይጭናል።

የፀጥታ ኃይል ልብስ የለበሱ አካላት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ አግተው ንበረቱን እንደዘረፉት በአቃቂ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለቃሊቲ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ያመለክታል፡፡

ፖሊስ ጣቢያው ለጉዳዩ ልዮ ትኩረት በመስጠት ወንጀል ፈፃሚዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ንብረቱን ለማስመለስ ባደረገው በርቱ ክትትልና ባሰባሰበው መረጃ አሽከርካሪው ብረቱን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ  ወረዳ 13 አካባቢ ሸጦ ተሽከርካሪውን ጀሞ አካባቢ ማቆሙን ይደርስበታል፡፡

በግለሰቡ ላይ ምርመራው ቀጥሎ ከተሰረቀው ንብረት መካከል ግምቱ 648ሺ 432 ብር የሚያወጣ ብረት ማስመለሱን ፖሊስ ጣቢያው አስታውቋል። የተጣለበትን እምነት ወደኋላ በማለት ንብረቱን ሸጦ ሳይታገት ታግቻለሁ በማለት ፖሊስን ለማሳሳት ሀሰተኛ ክስ የመሰረተው አሽከርካሪ እና  የተሰረቀውን ንብረት የገዛውን ጨምሮ በአጠቃላይ  ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን መቀጠሉን ፖሊስ አስታውቋል።

አንዳንድ ግለሰቦች ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማቀድ ሳይታገቱ ታግተናል በማለት ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጬ እና ሳይዘረፋ ተዘርፈናል በማለት የግል ጥቅማቸውን በህገወጥ መንገድ ለሟሟላት የሚሯሯጡ መኖራቸውን ያስታወቀው የአዲስ አበባ ፖሊስ የተለያዩ ሚዲያዎች የእነዚህ ህገወጦች መጠቀሚያ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ መልእክቱን አስተላልፏል ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
9.7K viewsedited  11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 13:07:20
ተሰርዘዋል

በሬሜዲያ ፈተና ሂደት ወቅት በተፈጠሩ ችግሮች ምክንያት የትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔዎች አሳልፏል።
የ2014 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ረሜዲያል ተጠቃሚ ተማሪዎች ፈተና ትናንት ሰኔ 26/2015 ዓ.ም በዩኒቨርስቲዎች መሰጠት መጀመሩ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ በፈተና ሂደት በተፈጠሩ ችግሮች ምክንያት የትምህርት ሚኒስቴር የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል።

1) ሰኔ 26/2015 የተሰጡት የሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች ተሰርዘው ተማሪዎች በቀሩት የትምህርት ዓይነቶች ብቻ እንዲመዘኑ።

2) ቀደም ብሎ በሁሉም ሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ተማሪዎች ባላቸው ተቋማት ፈተናውን በአንድ ጊዜ ለመስጠት የታቀደው ተሻሽሎ በተለይም ከ150 በላይ የሆኑና ከ200 በላይ ካምፓስ ያላቸውን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈተና ቀርቶ ወደ ፊት በሚወሰን አግባብ ፈተናው በመስከረም ወር 2016 ዓ.ም እንዲሰጥ።

3) በመንግስት ተቋማት የሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑትን ተማሪዎች በተያዘው ፕሮግራም መሰረት ይሰጣል።

(ትምህርት ሚኒስቴር)
NB. ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ዛሬ ይፋ ባደረገው መረጃ ትላንት ፈተናው መሰጠት ከተጀመረ በኃላ ተፈጥረዋል ያላቸውን ችግሮችን በዝርዝር አላሳወቀም።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
10.0K views10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 08:15:08 ዐበይት ዜናዎች

1፤ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከታጣቂዎች እገታ የተለቀቁ ሽፌሮችና ቤተሰቦቻቸው መንግሥት በአጋቾች ላይ ርምጃ አለመውሰዱ እንዳስገረማቸው መናገራቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። ሰኔ 10 ቀን ዓሊዶሮ በተባለ ቦታ ሹፌሮችና ረዳቶችን ጨምሮ በታጣቂዎች 79 ሰዎች ታግተው እንደነበር አንድ 500 ሺህ ብር ከፍሎ የተለቀቀ ሹፌር መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል። በምሥራቅ ጎጃም ዞን ማቻከል ወረዳ አማኑኤል ከተማ ደሞ አንድ ታጋች በጉልት ንግድ የሚተዳደሩት አባቱ ቤታቸውን አስይዘው እንዳስለቀቁት ተናግሯል ተብሏል። እገታው በተፈጸመበት ቦታ በቅርብ ርቀት ላይ የመከላከያ ሠራዊት ካምፕ እንደሚገኝ ታግተው የተለቀቁት ግለሰቦች መናገራቸውንም ዘገባው ጨምሮ ገልጧል።

2፤ ትናንት በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትና ውርጃን በማውገዝ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄዳቸውን ዶይቸቨለ ዘግቧል። የተቃውሞ ሰልፉን ያዘጋጁት፣ ሀዋሳ ከተማ ውስጥ የሚገኙ የፕሮቴስታንት እምነት ቤተክርስቲያናት እንደኾኑ ዘገባው እአመልክቷል።

3፤ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ወረዳ አንድ ታጣቂ የወረዳውን ፖሊስ አዛዥና ምክትላቸውን መግደሉን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። የፖሊስ አዛዡ ኢንስፔክተር ዘውዱ ታደሠ እና ምክትላቸው ወርቁ ሽመልስ የተገደሉት የ8ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና አሰጣጥ ጸጥታ ኹኔታን ለመመልከት አባይ ሸለቆ ውስጥ ወደሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት በተሽከርካሪ ሲጓዙ እንደኾነ የወረዳው ኮምንኬሽን ቢሮ መናገሩን ዘገባው አመልክቷል። የፖሊስ አዛዦቹ ሹፌር በጥቃቱ ቆስሏል ተብሏል። የወረዳው ጸጥታ ኃይሎች ገዳዩን ለማፈላለግ ባካባቢው እንደተሠማሩ ተገልጧል።

4፤ ዓለማቀፍ የፍልሰት ድርጅት የመንና ጅቡቲ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የወሰዷቸው ርምጃዎች ከአፍሪካ ቀንድ ወደ ባሕረ ሰላጤው የሚደረገውን የፍልሰተኞች ጉዞ ባለፈው ግንቦት ብቻ በ15 በመቶ እንደቀነሰው ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። የየመን ጸጥታ ኃይሎች በቅርብ በሕገወጥ ፍልሰተኞች መተላለፊያ ላይ የወሰዱት ርምጃ ሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎችን እንዳስበረገጋቸው ዘገባው ጠቅሷል። ከሱማሊያ ወደ የመን የሚገቡ ፍልሰተኞች ብዛት ግን በዚያው ወር ከ70 በመቶ በላይ መጨመሩን ድርጅቱ ገልጧል።. [ዋዜማ]

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
10.3K viewsedited  05:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 22:16:20 #Update

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም እንዲጠናቀቅ የጋራ የፀጥታ ዕቅድ ላይ ምክክር መደረጉን ለማወቅ ተችሏል።

በመድረኩ፦
- የትምህርት ሚኒስቴር፣
- የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣
- የክልል ፖሊስ ኮሚሽነሮች፣  የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች እና የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ፤ ከሐምሌ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በ102 የፈተና ጣቢያዎች የሚካሄደው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሀገራዊ የፀጥታ ሁኔታውንና የክረምቱን የአየር ሁኔታ ያገናዘበ በርካታ የሰው ኃይል መመደቡን አሳውቋል።

ፈተናው ከሥርቆት በፀዳ መልኩ እንዲካሄድ ሁሉም ኃላፊነቱን ወስዶ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባም ኮሚሽኑ አሳስቧል።

በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች በፈተና ጣቢያዎች የፀጥታ ችግሮች እንዳይከሰቱ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በቂ ዝግጅት ማድረጉንም ኮሚሽኑ አሳውቋል።

ተማሪዎች ለፈተና ሲመጡ ፦

- የሀኪም ማዘዣ የሌለው መድሃኒት በሽሮፕም ሆነ በታብሌት፣
- የህክምና መስጫ መርፌ፣
- የአንገት ሀብል፣
- የፀጉርና የጆሮ ጌጥ፣
- ከጋብቻ ቀለበት ውጭ ፈርጥ ያለው የጣት ቀለበት እና የእጅ አንባር አድርገው መምጣት እንደማይችሉ ፖሊስ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

በተጨማሪም ፦
- ተንቀሳቃሽ  ስልክ፣ 
- አይ-ፓድ፣
- ታብሌት፣
- ላፕቶፕ፣
- ስማርት ሰዓት፣
- ሲዲ፣
- ሚሞሪ ሪደርና ኦ-ቲጂ ኮንቨርተር እንዲሁም ፎቶ የሚያነሱ እና ድምፅ የሚቀርፁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ይዞ መገኘት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ተገልጿል።

የተከለከሉ መሣሪያዎችን በዩኒቨርሲቲዎቹ ግቢ ውስጥም ሆነ በዙሪያው ይዞ መገኘት፣ ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል መግባት እና ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ከፈተና ክፍል መውጣት እንዲሁም በዩኒቨርሲቲ ግቢ ወስጥ በግልም ሆነ በቡድን ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት የተከለከለ ነው።

ይህንን ተላልፎ በተገኘ ተማሪ ላይ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ አንዳንድ የትራንስፖርት ችግሮችን ለመቅረፍ፣ ለተማሪዎች ከትምህርት ቤት ጀምሮ በወረዳና በዞን ትምህርት ቢሮ አማካኝነት የፈተና መመሪያ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እንደተደረገ መሆኑን አሳውቋል።

መረጃው የፌዴራል ፖሊስ ነው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
12.6K views19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ