Get Mystery Box with random crypto!

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የሰርጥ አድራሻ: @wahidcom
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 34.43K
የሰርጥ መግለጫ

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-19 18:21:47 አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ያ ጀመዓህ!

ሰዎችን ሸሃዳህ አስይዛችሁ ሥታሠልሙ የሚያሳይ ቪድዮ ሚድያ ላይ ማውጣቱ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል። የሠለሙት ልጆች በዒልም፣ በኢማን፣ በሒክማህ ሳይጠነክሩ ማውጣት አግባብ አይደለም። ከቤተሰባቸው ድብደባ፣ ኩርፊያ እና ነቆራ ሲደርስባቸው ወይ ወደነበሩበት ኩርፍ ይመለሳሉ አሊያም ከቤት ወጥተው ጎዳና ላይ ይወጣሉ። ዞር ብላችሁ ላታያዋቸው ነገር ሚድያችሁን ለማሞቅ ስትሉ የሰውን ሕይወት አታበላሹ! ዲኑል ኢሥላምን መቀበል እና አለመቀበል የጀነት እና የእሳት ጉዳይ ነውና አሏህን ፈርተን ከዚህ ድርጊት እንቆጠብ።

ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
2.6K viewsedited  15:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 07:11:54 ከእኔ በፊት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

17፥55 ከፊሉንም ነቢያት በከፊሉ ላይ በእርግጥ አበለጥን፡፡ وَلَقَدْ فَضَّلْنَا بَعْضَ النَّبِيِّينَ عَلَىٰ بَعْضٍ

"ፈድል" فَضْل የሚለው ቃል "ፈዶለ" فَضَّلَ ማለትም" ሰጠ" "ቸረ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ስጦታ" "ችሮታ" "ጸጋ"Bounty” ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ በሚያወርደው ፈድል ነቢያትን ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አብልጧል፦
17፥55 ከፊሉንም ነቢያት በከፊሉ ላይ በእርግጥ አበለጥን፡፡ وَلَقَدْ فَضَّلْنَا بَعْضَ النَّبِيِّينَ عَلَىٰ بَعْضٍ

እነዚህ አናቅጽ ላይ "አበለጥን" ለሚለው የገባ ቃል "ፈዶልና" فَضَّلْنَا መሆኑን ልብ ብለካልን? በተመሳሳይ በባይብል ነቢዩ ዮሐንስ እና ነቢዩ ኢየሱስ ሁለቱም ነቢይ ናቸው፦
ሉቃስ 1፥76 ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል "ነቢይ" ትባላለህ፥ መንገዱን ልትጠርግ በጌታ ፊት ትሄዳለህና።
ማቴዎስ 21፥11 ሕዝቡም፦ "ይህ ከገሊላ ናዝሬት የመጣ "ነቢዩ" ኢየሱስ ነው" አሉ።

ነገር ግን ነቢዩ ዮሐንስ ከነቢዩ ኢየሱስ በደረጃ የሚያንስ እና ነቢዩ ኢየሱስ ከነቢዩ ዮሐንስ በደረጃ እንደሚልቅ ነቢዩ ዮሐንስ ተናግሯል፦
ዮሐንስ 1፥30 አንድ "ሰው" ከእኔ በኋላ ይመጣል፥ "ከእኔም በፊት ነበርና" ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል። οὗτός ἐστιν ὑπὲρ οὗ ἐγὼ εἶπον Ὀπίσω μου ἔρχεται ἀνὴρ ὃς ἔμπροσθέν μου γέγονεν, ὅτι πρῶτός μου ἦν.

"አነር" ἀνὴρ ማለት "ወንድ ሰው" ማለት ሲሆን የፆታ መደቡ ወንድ ነው፥ ይህ ወንድ የተራክቦ ማድረጊያ በስምንተኛው ቀን የተገረዘ ሰው ነው። ይህ ሰው ማኅፀን ውስጥ ተፈጥሮ እና የተለያየ እድገት አርጎ የመጣ ሲሆን ከዮሐንስ በደረጃ የከበረ ነው፥ በክብር ስለሚበልጥ "ከእኔም በፊት ነበር" በማለት ዮሐንስ ስለ ኢየሱስ ተናግሯል። ቅሉ ግን ዮሐንስ "አንድ ሰው" ያለው ሰው ኢየሱስ ከዮሐንስ በፊት በሰውነት አልነበረም፥ ነገር ግን በክብር መላቅን አመላካች ነው። ለምሳሌ፦ ምናሴ የኤፍሬፍ ታላቅ ወንድም ነው፥ በዕድሜ ምናሴ የዮሴፍ የበኵር ልጅ ሆኖ ኤፍሬምን ይቀድመዋል፦
ዘፍጥረት 41፥51-52 ዮሴፍም የበኵር ልጁን ስም ምናሴ ብሎ ጠራው፥ እንዲህ ሲል፦ "አምላክ መከራዬን ሁሉ የአባቴንም ቤት አስረሳኝ፤ የሁለተኛውንም ስም ኤፍሬም ብሎ ጠራው፥ እንዲህ ሲል፦ "አምላክ በመከራዬ አገር አፈራኝ"።

ነገር ግን ዮሴፍ ኤፍሬምንም ከምናሴ "በፊት" አደረገው፥ ያ ማለት ኤፍሬም ከምናሴ በፊት በአካል ደረጃ ነበረ ማለት ሳይሆን በክብር እና በደረጃ ከምናሴ ይበልጣል ማለት ነው፦
ዘፍጥረት 48፥20 ኤፍሬምንም ከምናሴ "በፊት" አደረገው።
ሰፕቱአጀንት፦ καὶ ἔθηκε τὸν ᾿Εφραΐμ ἔμπροσθεν τοῦ Μανασσῆ.
ማሶሬት፦ וַיָּ֥שֶׂם אֶת־אֶפְרַ֖יִם לִפְנֵ֥י מְנַשֶּֽׁה׃

"ሊፕነ" לִפְנֵ֥י ማለት "በፊት" ማለት ነው። ኤፍሬም ምናሴን በደረጃ እና በክብር ስለበለጠው ምናሴ ከኤፍሬም "በፊት" እንደሆነ ከተነገረ በተመሳሳይም ነቢዩ ኢየሱስ ከነቢዩ ዮሐንስ በክብር ስለበለጠ "ከእኔ በፊት" በማለት ተናግሯል፥ ጉዳዩ የክብር እንጂ የዕድሜ ስላልሆነ እዛው ዐውድ ላይ "ከእኔ ይልቅ የከበረ ሆኖአል" በማለት ተናግሯል። "እኔ" የሚለው ባለቤት ተውላጠ ስም ማንነትን የሚያሳይ ሲሆን ከኢየሱስ ማንነት መፈጠር በፊት የመጡ ሐሰተኛ ነቢያት መምጣታቸውን ኢየሱስ መናገሩ በራሱ የኢየሱስ ማንነት ከዮሐንስ በኃላ የተፈጠረ መሆኑን ቁልጭ አርጎ ያሳያል፦
ዮሐንስ 10፥8 "ከ-"እኔ በፊት" የመጡ ሁሉ ሌቦች እና ወንበዴዎች ናቸው። πάντες ὅσοι ἦλθον πρὸ ἐμοῦ κλέπται εἰσὶν καὶ λῃσταί·

"ከ-"እኔ በፊት" የሚለው ይሰመርበት! "በፊት" የሚለው መስተዋድድ "እኔ" ከሚለው ህልውና አስቀድሞ በኑባሬ ቀድመው የመጡ ፍጡራን እንዳሉ አመላካች ነው። ኢየሱስ ከድንግል ማርያም ከመፈጠሩ በፊት ቴዎዳስ እና የገሊላው ይሁዳ ሐሰተኛ ነቢያት ሆነው ተነስተው ነበር፦
የሐዋርያት ሥራ 5፥36 ከዚህ ወራት አስቀድሞ ቴዎዳስ፦ "እኔ ታላቅ ነኝ" ብሎ ተነሥቶ ነበርና፥ አራት መቶ የሚያህሉ ሰዎችም ከእርሱ ጋር ተባበሩ፤ እርሱም ጠፋ የሰሙትም ሁሉ ተበተኑ እንደ ምናምንም ሆኑ።
የሐዋርያት ሥራ 5፥37 ከዚህ በኋላ ሰዎች በተጻፉበት ዘመን የገሊላው ይሁዳ ተነሣ ብዙ ሰዎችንም አሸፍቶ አስከተለ፤ እርሱም ጠፋ የሰሙትም ሁሉ ተበታተኑ።

በታሪክ ቴዎዳስ ከኢየሱስ ልደት አርባ አራት ዓመት በፊት "መሢሕ ነኝ" ብሎ ተነስቶ ብዙ ተከታዮችን አፍርቶ ነበር። ከእርሱ በኃላ ሰዎች የተጻፉበት ዘመን ከኢየሱስ ልደት ስድስት ዓመት ቀደም ብሎ የተካሄደ ሲሆን በዚያን ጊዜ የገሊላው ይሁዳ "መሢሕ ነኝ" ብሎ የተነሳው ኢየሱስ ከመፈጠሩ በፊት ነው።
ኢየሱስ "ከ-እኔ በፊት" ሲል "እኔ" የሚለው "እኔነቱን" ወደ ህልውና ከመምጣቱ በፊት ቴዎዳስ እና የገሊላው ይሁዳ በህልውና ይቀድሙት ነበር ማለት ነው። ህልውናው ጅማሮ እና መነሾ ያለው ኢየሱስ ከዮሐንስ በፊት በአካል አልነበረም፥ ከዚያ ይልቅ ዮሐንስ ኢየሱስን በአካል በስድስት ወር ይበልጠዋል።
አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
2.2K views04:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 19:23:45 ኢብሊሥ ከጂን ስለሆነ አሏህን የማመጽ እና የመታዘዝ ነጻ ፈቃድ ስላለው በጌታው ላይ አምጾ ኮራ፥ መላእክት ግን የማመጽ እና የመታዘዝ ነጻ ፈቃድ ስለሌላቸው በባሕያቸው ውስጥ ኩራትና አመጽ የለም። አሏህ ያዘዛቸውን ነገር በመጣስ አያምጹም፥ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ፦
38፥74 ኢብሊሥ ብቻ ሲቀር፡፡ "ኮራ"፤ ከከሓዲዎቹም ሆነ፡፡ إِلَّا إِبْلِيسَ اسْتَكْبَرَ وَكَانَ مِنَ الْكَافِرِينَ
16፥49 "እነርሱም አይኮሩም" وَهُمْ لَا يَسْتَكْبِرُونَ
21፥19 እርሱ ዘንድ ያሉትም መላእክት እርሱን ከመገዛት አይኮሩም፡፡ አይሰለቹምም፡፡ وَمَنْ عِندَهُ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِ وَلَا يَسْتَحْسِرُونَ
66፥6 አላህ ያዘዛቸውን ነገር በመጣስ አያምጹም፤ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ፡፡ لَّا يَعْصُونَ اللَّهَ مَا أَمَرَهُمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ

፨ሲያረብብ መላእክት በአሏህ ላይ አምጸው የሚገቡበት ጀሀነም ሆነ ታዘው የሚገቡበት ጀነት የለም። ጂኒዎች ግን በምርጫቸው አምነው ጀነት ወይም ክደው ጀሀነም መግባት ይችላሉ፦
11፥119 የጌታህም ቃል፦ "ገሀነምን ከጂኒዎ እና ከሰዎች ሁሉ በእርግጥ እሞላታለሁ" በማለት ተፈጸመች። وَتَمَّتْ كَلِمَةُ رَبِّكَ لَأَمْلَأَنَّ جَهَنَّمَ مِنَ الْجِنَّةِ وَالنَّاسِ أَجْمَعِينَ
55፥45 ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ? فَبِأَيِّ آلَاءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَان
55፥46 በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሁለት ገነቶች አሉት፡፡ وَلِمَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ جَنَّتَانِ

ሱረቱር ረሕማን ዐውዱ ላይ ያሉት ሰው እና ጃን ናቸው፥ "ጌታችሁ" የሚለው ቃል "ረቢኩማ" رَبِّكُمَا ሲሆን ሁለተኛ መደብ ሙሰና ሰውን እና ጃንን ያመለክታል። “ታስተባብላላችሁ” የሚለው ቃል “ቱከዚባኒ” تُكَذِّبَانِ ሲሆን ሁለተኛ መደብ ሙሰና ሰውን እና ጃንን ያመለክታል፦
55፥14 ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡ خَلَقَ الْإِنسَانَ مِن صَلْصَالٍ كَالْفَخَّارِ
55፥15 "ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው"፡፡ وَخَلَقَ الْجَانَّ مِن مَّارِجٍ مِّن نَّارٍ

የትንሳኤ ቀን ለሁለቱም የተቀጠረ ቀጠሮ ነው፥ የዚያን ቀን የተውበት በር ስለተዘጋ ሰው ሆነ ጂን ከኃጢኣቱ አሏህን ይቅርታ እንዲጠይቅ አይጠየቅም። ከዛ ይልቅ "የዚህንም ቀናችሁን ቅጣት ማግኘትን የሚያስጠነቅቋችሁ ከእናንተው የኾኑ መልእክተኞች አልመጧችሁምን" በመባል ፍርድ ያገኛሉ፦
44፥40 የመለያው ቀን ለሁሉም ቀጠሯቸው ነው፡፡ إِنَّ يَوْمَ الْفَصْلِ مِيقَاتُهُمْ أَجْمَعِينَ
55፥39 በዚያም ቀን ሰው እና ጃን ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡ فَيَوْمَئِذٍ لَّا يُسْأَلُ عَن ذَنبِهِ إِنسٌ وَلَا جَانٌّ
6፥130 የጂኒዎች እና የሰዎች ጭፍሮች ሆይ! አንቀጾቼን በእናንተ ላይ የሚተርኩ የዚህንም ቀናችሁን ቅጣት ማግኘትን የሚያስጠነቅቋችሁ ከእናንተው የኾኑ መልእክተኞች አልመጧችሁምን? ይባላሉ፡፡ يَا مَعْشَرَ الْجِنِّ وَالْإِنسِ أَلَمْ يَأْتِكُمْ رُسُلٌ مِّنكُمْ يَقُصُّونَ عَلَيْكُمْ آيَاتِي وَيُنذِرُونَكُمْ لِقَاءَ يَوْمِكُمْ هَـٰذَا

ለጂኒዎች ጀነት እና ጀሃነም እንዲሁ የትንሳኤ ቀን ቀጠሮ እንዳላቸው እና የተፈጠሩበት አላማ ካየን ዘንዳ በነጻ ምርጫቸው አምነው ሙሥሊም አልያም ክደው ኩፋር የመሆን ምርጫ አላቸው፦
72፥14 «እኛም ከእኛ ውስጥ ሙሥሊሞች አሉ፡፡ ከእኛም ውስጥ በዳዮች አሉ፡፡ የሠለሙም ሰዎች እነዚያ ቅንን መንገድ መረጡ፡፡» وَأَنَّا مِنَّا الْمُسْلِمُونَ وَمِنَّا الْقَاسِطُونَ ۖ فَمَنْ أَسْلَمَ فَأُولَـٰئِكَ تَحَرَّوْا رَشَدًا

ስለዚህ "ኢብሊሥ መልአክ ነበር" የሚለው ትርክት ቁርኣን ላይ ሆነ ሐዲስ ላይ የለም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
1.7K views16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 19:23:32 ፨ሲቀጥል "ለመላእክትም ለአደም ስገዱ! ባልናቸው ጊዜ የሆነውን አስታውስ! ወዲያውም ሰገዱ፥ ኢብሊሥ ብቻ ሲቀር" በሚል አንቀጽ ውስጥ "ሲቀር" "በቀር" ለሚለው የገባው ቃል "ኢላ" إِلَّا ሲሆን ኢሥቲስናእ ነው። "ኢሥቲስናእ" اِسْتِثْنَاء‏ የሚለው ቃል "ኢሥተስና"  اِسْتَثْنَى ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "በስተቀረት"exception" ማለት ነው፥ ኢሥቲስናእ በሁለት ይከፈላል። አንዱ "ኢሥቲስናኡል ሙተሲል" اِسْتِثْنَاء‏ الْمُتَّصِل ሲሆን "ሙተሲል" مُتَّصِل ማለት "የተያያዘ"attached" ማለት ነው፦
43፥67 ወዳጆች በዚያ ቀን ከፊላቸው ለከፊሉ ጠላት ነው፡፡ አላህን ፈሪዎች ብቻ "ሲቀሩ"፡፡ الْأَخِلَّاءُ يَوْمَئِذٍ بَعْضُهُمْ لِبَعْضٍ عَدُوٌّ إِلَّا الْمُتَّقِينَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ኢላ" إِلَّا የሚለው ኢሥቲስናኡል ሙተሲል ስለሆነ ተመሳሳይ ጥንተ ተፈጥሮን ያሳያል፥ ከፊላቸው ለከፊሉ ጠላት የሚሆነው እና አሏህን ፈሪዎች ጥንተ ተፈጥሯቸው ተመሳሳይ ነው። ተጨማሪ ይህንን ጥቅስ መመልከት ይቻላል፦
103፥2 ሰው ሁሉ በእርግጥ በከሳራ ውስጥ ነው፡፡ إِنَّ الْإِنسَانَ لَفِي خُسْرٍ
103፥3 እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ "ሲቀሩ"፡፡ إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَتَوَاصَوْا بِالْحَقِّ وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ

ሁለተኛው ደግሞ "ኢሥቲስናኡል ሙንቀጢዕ" اِسْتِثْنَاء‏ الْمُنقَطِع ሲሆን "ሙንቀጢዕ" مُنقَطِع ማለት "ያልተያያዘ"detached" ማለት ነው፦
26፥77 «እነርሱም ለእኔ ጠላቶች ናቸው፥ ግን የዓለማት ጌታ "ሲቀር"»፡፡ فَإِنَّهُمْ عَدُوٌّ لِّي إِلَّا رَبَّ الْعَالَمِينَ

ኢብራሂም "እነርሱም ለእኔ ጠላቶች ናቸው" ያላቸው እና "ሲቀር" ያለው "የዓለማት ጌታ" ሁለት የተለያዩ ኑባሬዎች እንደሆኑ ሁሉ በተመሳሳይ የሰዋስው አወቃቀር "መላእክት" እና "ኢብሊሥ" ሁለት የተለያዩ ኑባሬዎች ናቸው። በተጨማሪ አንድ ጥቅስ እንመልከት፦
17፥67 በባሕሩም ውስጥ ጉዳት ባገኛችሁ ጊዜ የምትጠሩዋቸው ሁሉ ይጠፋሉ፥ እርሱ(አላህ) "ሲቀር"፡፡ وَإِذَا مَسَّكُمُ الضُّرُّ فِي الْبَحْرِ ضَلَّ مَن تَدْعُونَ إِلَّا إِيَّاهُ

ጣዖታዊያን በባሕሩም ውስጥ ጉዳት ባገኛቸው ጊዜ የሚጠሩዋቸው ጣዖታታት የሰው እጅ ሥራዎች ሲሆኑ ይጠፋሉ፥ አሏህ ግን ሕያው ፈጣሪ ስለሆነ አይጠፋም። ስለዚህ "በቀር" "በስተቀር" ስለተባለ ዐውዱ እና አጠቃላይ አሳቡ ሳይታይ "አንድ ምድብ ነው" ማለት ስህተት እንዳለው ከተረዳን ዘንዳ "በቀር" ስላለ ኢብሊሥን የመላእክት ጥንተ ተፈጥሮ ውስጥ ማካተት ስህተት ነው።
ኢብሊሥ ከጂን እንጂ ከመላእክት አለመሆኑ ሐሠን አል-በስሪይ እንደተናገረው በኢብኑ ጀሪር ተተርኳል፥ በኢሥናዱም ሶሒሕ ነው። ኢብኑ ከሲር በመቀጠል በተፍሢሩ ላይ አድ-ደሓክ፣ ሠዒድ ኢብኑ ጀቢር፣ ኢብኑ ኢሥሐቅ ወዘተ "ኢብሊሥ መልአክ ነበር" ያሉት ከኢሥራዒልያት ትርክት እንደሆነ ተናግሯል፦
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 18፥50
"ሐሠን አል-በስሪይ እንደተናገረው፦ "ኢብሊሥ ከመላእክት አይደለም፥ ለአንዲት ቅጽበት እንኳን አልነበረም። ልክ አደም"ዐ.ሠ." ለሰው ሥረ-መሠረት እንደሆነ ሁሉ ኢብሊሥም ለጂን ሥረ-መሠረት ነው"። ይህ በኢብኑ ጀሪር ተተርኳል፥ በኢሥናዱም ሶሒሕ ነው።  قال الحسن البصري : ما كان إبليس من الملائكة طرفة عين قط ، وإنه لأصل الجن ، كما أن آدم ، عليه السلام ، أصل البشر . رواه ابن جرير بإسناد صحيح
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 18፥50
"በእርግጥ በዚህ ሪዋያህ ከቀደምቶቹ የተተረከው ዘገባ አብዛኛውን ከኢሥራኢልያት እንደሆነ ይጤናል"።  وقد روي في هذا آثار كثيرة عن السلف ، وغالبها من الإسرائيليات التي تنقل لينظر فيها

፨ሢሰልስ መላእክት የተፈጠሩበት ንጥረ ነገር ብቻ ሳይሆን ባሕርያቸውም ይለያል፥ መላእክት ፆታ የላቸውም፦
43፥19 "መላእክትንም እነርሱ የአልረሕማን ባሮች የኾኑትን ሴቶች አደረጉ"፡፡ ሲፈጠሩ ነበሩን? መመስከራቸው በእርግጥ ትጻፋለች፡፡ ይጠየቃሉም፡፡ وَجَعَلُوا الْمَلَائِكَةَ الَّذِينَ هُمْ عِبَادُ الرَّحْمَـٰنِ إِنَاثًا ۚ أَشَهِدُوا خَلْقَهُمْ ۚ سَتُكْتَبُ شَهَادَتُهُمْ وَيُسْأَلُونَ
37፥150 ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው "መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን? أَمْ خَلَقْنَا الْمَلَائِكَةَ إِنَاثًا وَهُمْ شَاهِدُونَ

ከመላእክት መካከል ሴቶች ቢኖሩ ኖሮ ቁሬሾች፦ "መላእክት ሴቶች ናቸው" ማለታቸውን አይቃወምም ነበር፥ አሏህ መላእክትን ሴቶች አድርጎ አልፈጠረም። ጂኒዎች ግን ጾታ አላቸው፥ ዝርያ ስላላቸው የሚራቡ ወንድ እና ሴት ናቸው፦
18፥50 "እርሱን እና ዘሮቹን እነርሱ ለእናንተ ጠላቶች ሲኾኑ ከእኔ ላይ ረዳቶች አድርጋችሁ ትይዛላችሁን? ለበዳዮች ልዋጭነቱ ከፋ! أَفَتَتَّخِذُونَهُ وَذُرِّيَّتَهُ أَوْلِيَاءَ مِن دُونِي وَهُمْ لَكُمْ عَدُوٌّ ۚ بِئْسَ لِلظَّالِمِينَ بَدَلًا
72፥6 እነሆም "ከሰዎች የኾኑ ወንዶች በጂኒ ወንዶች ይጠበቁ ነበሩ"፡፡ ኩራትንም ጨመሩዋቸው፡፡  وَأَنَّهُ كَانَ رِجَالٌ مِّنَ الْإِنسِ يَعُوذُونَ بِرِجَالٍ مِّنَ الْجِنِّ فَزَادُوهُمْ رَهَقًا
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 312
ዘይድ ኢብኑ አርቀም እንደተረከው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ “ቆሻሻ ቦታዎች በሰይጣናት ይጎበኛሉ፥ ከእናንተም ወደዚያ ሲገባ፦ "አሏህ ሆይ! ከወንድ እና ከሴት ሰይጣናት በአንተ እጠበቃለው" ይበል። عَنْ زَيْدِ بْنِ أَرْقَمَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ “‏ إِنَّ هَذِهِ الْحُشُوشَ مُحْتَضَرَةٌ فَإِذَا دَخَلَ أَحَدُكُمْ فَلْيَقُلِ اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنَ الْخُبُثِ وَالْخَبَائِثِ ‏”‏ ‏.‏
1.6K views16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 19:23:09 ኢብሊሥ መልአክ ነበርን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

18፥50 ለመላእክትም ለአደም ስገዱ! ባልናቸው ጊዜ የሆነውን አስታውስ! ወዲያውም ሰገዱ፥ ኢብሊሥ ብቻ ሲቀር ከጂን ነበር ከጌታውም ትእዛዝ ወጣ"፡፡ وَإِذْ قُلْنَا لِلْمَلَائِكَةِ اسْجُدُوا لِآدَمَ فَسَجَدُوا إِلَّا إِبْلِيسَ كَانَ مِنَ الْجِنِّ فَفَسَقَ عَنْ أَمْرِ رَبِّهِ

“ኢብሊሥ” إِبْلِيس  የሚለው ቃል "በለሠ" بَلَسَ ማለትም "ተስፋ ቆረጠ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ተስፋ የቆረጠ" ማለት ነው፥ "ኢብሊሥ” إِبْلِيس  የሚለው ቃል 11 ጊዜ በ 11 ቦታ ከጂን ለሆነ ፍጡር የተሰጠ የግብር ስም ነው፦
18፥50 ለመላእክትም ለአደም ስገዱ! ባልናቸው ጊዜ የሆነውን አስታውስ! ወዲያውም ሰገዱ፥ ኢብሊሥ ብቻ ሲቀር ከጂን ነበር። ከጌታውም ትእዛዝ ወጣ"፡፡ وَإِذْ قُلْنَا لِلْمَلَائِكَةِ اسْجُدُوا لِآدَمَ فَسَجَدُوا إِلَّا إِبْلِيسَ كَانَ مِنَ الْجِنِّ فَفَسَقَ عَنْ أَمْرِ رَبِّهِ

"ከጂን ነበር" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት "ጂኒ" جِنِّيّ የሚለው ቃል "ጀነ" جَنَّ ማለትም "ሰወረ" "ደበቀ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ስውር" "ድብቅ" ማለት ነው፥ "ጂን" جِنّ ደግሞ የጂኒ ብዙ ቁጥር ነው። ኢብሊሥ ጥንተ ተፈጥሮው ከጂን ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 55, ሐዲስ 78
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው፦ የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "መላእክት ከብርሃን ተፈጥረዋል፣ ጃን ከእሳት ነበልባል ተፈጥሯል፣ አደም ለእናንተ እንደተገለጸላችሁ ከሚጭለቀለቅ ሸክላ ተፈጥሯል"፡፡ عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم‏ خُلِقَتِ الْمَلاَئِكَةُ مِنْ نُورٍ وَخُلِقَ الْجَانُّ مِنْ مَارِجٍ مِنْ نَارٍ وَخُلِقَ آدَمُ مِمَّا وُصِفَ لَكُمْ ‏.‏

"ጃን" جَانّ ልክ እንደ "ሰው" ለጂኒዎች ጥቅላዊ ስም ነው፥ መላእክት እና ጃን "ወ" وَ ማለትም "እና" የሚል መስተጻምር መጠቀሙ በራሱ መላእክት እና ጂን ሁለት የተለያዩ ፍጥረታት እንደሆኑ ቁልጭ አርጎ ያሳያል። እዚህ ድረስ ከተግባባን "ኢብሊሥ መልአክ ነበር" ብለው ሚሽነሪዎች የሚሞግቱት በዚህ ጥቅስ ነው፦
17፥61 ለመላእክትም "ለአደም ስገዱ" ባልናቸው ጊዜ አስታውስ! ወዲያውም ሰገዱ፥ ኢብሊስ ብቻ ሲቀር፡፡ وَإِذْ قُلْنَا لِلْمَلَائِكَةِ اسْجُدُوا لِآدَمَ فَسَجَدُوا إِلَّا إِبْلِيسَ

፨ሲጀመር "ለ" የሚለው መስተዋድድ "መላእክት" በሚል መነሻ ቅጥያ ላይ መግባቱ አሏህ "ስገዱ" ያለው "ለመላእክት ብቻ" እንደሆነ ማስረጃ መሆን በፍጹም አይችልም። ይህንን በአንድ ተመሳሳይ ሙግት እንሞግት፦
7፥79 "ለ"-እነርሱም ልቦች አሏቸው፥ ግን አይገነዘቡበትም፣ "ለ"-እነርሱም ዓይኖች አሉዋቸው፥ ግን ዐያዩበትም፣ "ለ"-እነርሱም ጆሮዎች አሉዋቸው ግን አይሰሙበትም፡፡ لَهُمْ قُلُوبٌ لَّا يَفْقَهُونَ بِهَا وَلَهُمْ أَعْيُنٌ لَّا يُبْصِرُونَ بِهَا وَلَهُمْ آذَانٌ لَّا يَسْمَعُونَ بِهَا

ዐውዱ ላይ "እነርሱ" የተባሉት "ይልቁንም እነርሱ በጣም የተሳሳቱ ናቸው፥ እነዚያ ዘንጊዎቹ እነርሱ ናቸው" የተባሉትን ነው፥ ቅሉ ግን "ለ" የሚለው መስተዋድድ "እነርሱ" በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ መምጣቱ ልቦች፣ ዓይኖች፣ ጆሮዎች አሉዋቸው የተባሉት ዘንጊዎቹ እና የተሳሳቱት ብቻ ናቸው እንደማንል ሁሉ አሏህ "ስገዱ" ያለው ለመላእክት ብቻ ሳይሆን ለኢብሊሥም ጭምር ነው፦
7፥12 አላህ፦ «ባዘዝኩህ ጊዜ ከመስገድ ምን ከለከለህ» አለው፡፡قَالَ مَا مَنَعَكَ أَلَّا تَسْجُدَ إِذْ أَمَرْتُكَ

አሏህ ያለው "ባዘዝኳችሁ ጊዜ ከመስገድ ምን ከለከለህ" ሳይሆን "ባዘዝኩህ ጊዜ ከመስገድ ምን ከለከለህ" ነው፥ "ባዘዝኩህ" የሚለው ኃይለ-ቃል አሏህ ለአደም "ስገድ" ብሎ አዞት እንደነበር ቁልጭና ፍንትው አድርጎ ያሳያል። "ከጌታውም ትእዛዝ ወጣ" ማለቱ በራሱ እንዲሰግድ የታዘዙት መላእክት ብቻ አለመሆናቸውን ቁልጭ አርጎ ያሳያል፦
18፥50 ከጌታውም ትእዛዝ ወጣ፡፡ فَفَسَقَ عَنْ أَمْرِ رَبِّهِ
1.7K viewsedited  16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 10:31:44 ዶክተርዎን ይጠይቁ

በሙሥሊም ዶክተሮች የተዘጋጀ ልዩ መርሐ ግብር በቴሌ ግራም፦
https://t.me/askyourdoctorethiopia
2.6K viewsedited  07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 12:27:24 ደዕዋህ ለሁሉም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

16፥125 ወደ ጌታህ መንገድ በጥበብ እና በመልካም ግሳጼ ጥራ፡፡ ادْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِالْحِكْمَةِ وَالْمَوْعِظَةِ الْحَسَنَةِ

"ደዕዋህ” دَعْوَة የሚለው ቃል “ደዓ” دَعَا ማለትም “ጠራ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ጥሪ” ማለት ነው። ይህ ጥሪ ወደ አሏህ ሲሆን ሰዎች አሏህን ብቻ እንዲያመልኩ እና በእርሱ ላይ ማንንምና ምንንም ነገር እንዳያጋሩ በማስተማር ወደ አሏህ መጣራት “ደዕዋህ” دَعْوَة ይባላል፦
16፥125 ወደ ጌታህ መንገድ በጥበብ እና በመልካም ግሳጼ ጥራ፡፡ ادْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِالْحِكْمَةِ وَالْمَوْعِظَةِ الْحَسَنَةِ

ከዚህ ተነስተን ወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር"Wahid islamic apologetics society" የኢሥላምን መልእክት ዐበይት በሚባሉት ቋንቋዎች አዘጋጅቶላችኃል።

፨ወሒድ የሃይማኖት ንጽጽር በኦሮመኛ
https://t.me/Wahidomar1

፨ወሒድ የሃይማኖት ንጽጽር በዐማርኛ https://t.me/Wahidcom

፨ወሒድ የሃይማኖት ንጽጽር በትግሪኛ
https://t.me/wahidtigriga

፨ወሒድ የሐይማኖት ንጽጽር በሲዳሞኛ
https://t.me/wahidcomsidamo

፨ወሒድ የሐይማኖት ንጽጽር በጉራጌኛ
https://t.me/wahidcomguragiga

፨ወሒድ የሐይማኖት ንጽይር በሃይዲይኛ
https://t.me/wahidcomHaydega

፨ወሒድ የሃይማኖት ንጽጽር በአፋረኛ
https://t.me/wahidcomafarega

፨ወሒድ የሃይማኖት ንጽጽር በሶማሌኛ
https://t.me/wahidcomsomaliga

፨ወሒድ የሃይማኖት ንጽጽር በስልጤኛ
https://t.me/wahidcomselitiy

፨ወሒድ የሃይማኖት ንጽጽር በሃላቢኛ
https://t.me/wahidcomhelabega

ከወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር

ወሠላሙ ዐለይኩም
4.0K views09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 10:31:55 ዛፍ ይናገራልን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

55፥6 ሐረግ እና ዛፍ ለእርሱ ይሰግዳሉ፡፡ وَالنَّجْمُ وَالشَّجَرُ يَسْجُدَانِ

ከጂን የኾኑ ጭፈሮች ቁርኣንን አዳምጠው "እኛ አስደናቂ የኾነን ቁርኣን ሰማንም" ማለታቸው ወደ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ተወርዷል፦
72፥1 በል «እነሆ ከጂን የኾኑ ጭፈሮች ቁርኣንን አዳመጡ፡፡‹እኛ አስደናቂ የኾነን ቁርኣን ሰማንም› አሉ ማለት ወደ እኔ ተወረደ፡፡ قُلْ أُوحِيَ إِلَيَّ أَنَّهُ اسْتَمَعَ نَفَرٌ مِّنَ الْجِنِّ فَقَالُوا إِنَّا سَمِعْنَا قُرْآنًا عَجَبًا

"ተወረደ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ኡሒየ" أُوحِيَ ሲሆን "ወሕይ" وَحْي ማለት እራሱ "ግልጠተ መለኮት"Divine revelation" ማለት ነው፥ ከጂኒ የኾኑን ጭፍሮች ቁርኣንን የሚያዳምጡ ሆነው ወደ ነቢያችን"ﷺ" ዞረዋል፦
46፥29 ከጂኒ የኾኑን ጭፍሮች ቁርኣንን የሚያዳምጡ ሲኾኑ ወደ አንተ ባዞርን ጊዜም አስታውስ! በተጣዱትም ጊዜ "ዝም ብላችሁ አዳምጡ" ተባባሉ፡፡ በተጨረሰም ጊዜ አስጠንቃቂዎች ኾነው ወደ ሕዝቦቻቸው ተመለሱ፡፡ وَإِذْ صَرَفْنَا إِلَيْكَ نَفَرًا مِّنَ الْجِنِّ يَسْتَمِعُونَ الْقُرْآنَ فَلَمَّا حَضَرُوهُ قَالُوا أَنصِتُوا ۖ فَلَمَّا قُضِيَ وَلَّوْا إِلَىٰ قَوْمِهِم مُّنذِرِينَ

በተጨረሰም ጊዜ አስጠንቃቂዎች ኾነው ወደ ሕዝቦቻቸው ተመለሱ፥ በሌሊት ጂኒዎች ቁርኣንን መስማታቸውን ለነቢዩ"ﷺ" የተናገረው ዛፍ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63 ሐዲስ 85
ዐብዱ ራሕማን እንደተረከው፦ "እኔም መሥሩቅን፦ "በሌሊት ጂኒዎች ቁርኣንን መስማታቸውን ለነቢዩ"ﷺ" ማን ነገራቸው? ብዬ ጠየኩት፥ እርሱም፦ "አባትህ ዐብደሏህ፦ "ለነቢዩ"ﷺ" ስለ እነርሱ የተናገረው ዛፍ ነው" አለኝ። حَدَّثَنِي عُبَيْدُ اللَّهِ بْنُ سَعِيدٍ، حَدَّثَنَا أَبُو أُسَامَةَ، حَدَّثَنَا مِسْعَرٌ، عَنْ مَعْنِ بْنِ عَبْدِ الرَّحْمَنِ، قَالَ سَمِعْتُ أَبِي قَالَ، سَأَلْتُ مَسْرُوقًا مَنْ آذَنَ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم بِالْجِنِّ لَيْلَةَ اسْتَمَعُوا الْقُرْآنَ‏.‏ فَقَالَ حَدَّثَنِي أَبُوكَ ـ يَعْنِي عَبْدَ اللَّهِ ـ أَنَّهُ آذَنَتْ بِهِمْ شَجَرَةٌ‏.‏

ዛፍ በራሱ የሚናገር እና የሚሰማ ማንነት አይደለም፥ አምላካችን አሏህ ግን ዛፉን ጂኒዎች ቁርኣንን መስማታቸውን ለነቢዩ"ﷺ" እንዲናገር ካረገው በኃላ በቁርኣን ግልጠተ መለኮት ጂኒዎች "እኛ አስደናቂ የኾነን ቁርኣን ሰማንም" ማለታቸውን ወደ ነቢያችን"ﷺ" ወሕይ አድርጎ አወረደ እንጂ እናንተ እንደምትቀጥፉት ዛፉ አሏህ ሆኖ አይደለም። ዛፍ እራሱ ፍጡር ሆኖ ለአሏህ የሚሰግድ ተክል ነው፦
55፥6 ሐረግ እና ዛፍ ለእርሱ ይሰግዳሉ፡፡ وَالنَّجْمُ وَالشَّجَرُ يَسْجُدَانِ

አሏህ ዛፍን እንዲናገር ማድረጉ ከገረማችሁ እና የሐዲሱን አሳብ ማጣመም ከፈለጋችሁ እንግዲያውስ "እባቡ ሰይጣን ነው" ማለት ነው፦
ዘፍጥረት 3፥1 እባብም ያህዌህ አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅ "ብልህ" ነበረ። וְהַנָּחָשׁ֙ הָיָ֣ה עָר֔וּם מִכֹּל֙ חַיַּ֣ת הַשָּׂדֶ֔ה אֲשֶׁ֥ר עָשָׂ֖ה יְהוָ֣ה אֱלֹהִ֑ים

በዐማርኛ ትርጉም ላይ "ተንኮለኛ" ብለው ያስቀመጡት የዕብራይስጡ ቃል "አሩም" עָרוּם ሲሆን "ብልህ"prudent" ማለት ነው፥ ምሳሌ 12፥23 ተመልከት! እባቡ የምድር አውሬ ነው። ሴቲቱን ሲያነጋግር የነበረውም ይህ የምድር አውሬ ነው፥ ሴቲቱን ስላሳሳተ ተብሎ የተረገመው ይህ እባብ ነው፦
ዘፍጥረት 3፥14 ያህዌ አምላክም እባቡን አለው፦ "ይህን ስላደረግህ ከእንስሳት ከምድር አራዊትም ሁሉ ተለይተህ አንተ የተረገምህ ትሆናለህ፤ በሆድህም ትሄዳለህ፥ አፈርንም በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ትበላለህ"።

የዘፍጥረት ዐውደ ንባቡን"contextual passage" ውስጥ ስለ ሰይጣን የሚናገር ምንም ሽታው የለው። ስድሳ ስድስቱ መጽሐፍ ላይ ዲያብሎስ አዳምን እና ሔዋንን እንዳሳሳተ የሚናገር ምንም ጥቅስ የለም፥ ነገር ግን መቃቢያን ላይ ዲያብሎስ አዳምን እና ሔዋንን ሸንግሎ እንዳሳሳታቸው ይናገራል፦
1ኛ መቃብያን 19፥6 ዲያብሎስም “እንደ ፈጣሪያችሁ እንደ እግዚአብሔር ትሆናላችሁ” ብሎ ሸንግሎ አባታችን አዳምን እና እናታችንን ሔዋንን ወደ እርሱ ስሕተት ወሰዳቸው።

ዲያብሎስ የምድር አውሬ የሆነው እባብ ነውን? ዲያብሎስ ጥንተ ተፈጥሮው ከጂን ወይም እንደ እናንተ እምነት ከመላእክት አይደለምን? መልሱ፦ "እባቡ ዲያብሎስ ሳይሆን ዲያብሎስ በእባቡ ተጠቅሞ አሳሳታቸው" ከሆነ እንግዲያውስ ዛፉ አሏህ ሆኖ ሳይሆን አሏህ ዛፉን እንዲናገር ማድረግ ምን ያቅተዋል? በባይብል እኮ ፈጣሪ አህያ እና ድንጋይ እንዲናገሩ የሚያደርግ ነው፦
2 ጴጥሮስ 2፥16 ቃል የሌለው "አህያ" በሰው ቃል ተናግሮ የነቢዩን እብድነት አገደ።
ኢያሱ 24፥27 እነሆ የተናገረንን የያህዌን ቃል ሁሉ ሰምቶአልና "ይህ ድንጋይ" ይመሰክርብናል።

ድንጋይ በጥንተ ተፈጥሮው የሚሰማ እና የሚናገር እንዳልሆነ ቅቡል ቢሆንም ቅሉ ግን በተአምር የያህዌን ቃል ሰምቶ መናገሩ እሙን ነው። አሏህ በትንሳኤ ቀን እኮ መስማት እና መናገር የማይችለውን የሰውን ቆዳ እንዲሰማ እና እንዲናገር ያደርጋል፦
41፥21 ለቆዳዎቻቸውም «በእኛ ላይ ለምን መሰከራችሁብን?» ይላሉ፡፡ «ያ አንዳቹን ነገር ሁሉ ያናገረው አላህ አናገረን፡፡ እርሱም በመጀመሪያ ጊዜ ፈጠራችሁ፡፡ ወደእርሱም ትመለሳላችሁ» ይሏቸዋል፡፡ وَقَالُوا لِجُلُودِهِمْ لِمَ شَهِدتُّمْ عَلَيْنَا ۖ قَالُوا أَنطَقَنَا اللَّهُ الَّذِي أَنطَقَ كُلَّ شَيْءٍ وَهُوَ خَلَقَكُمْ أَوَّلَ مَرَّةٍ وَإِلَيْهِ تُرْجَعُونَ

ስለዚህ "ዛፍ እንዴት ይናገራል" ተብሎ መታመስ እና መተራመስ አስፈላጊ አይደለም። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
4.9K views07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 08:23:34 "ከ-ሚፈጥረው" የሚለውን ይሰመርበት! "የኽሉቁ" يَخْلُقُ የሚለው ፊዕሉል ሙዷሪዕ "የተኺዘ" يَتَّخِذَ ከሚለው ጋር መምጣቱ በራሱ "መያዝ" ልክ እንደ መውለድ የባሕርይ ጉዳይ ሳይሆን ሳይወልዱ ወደ ራስ በማስጠጋት ከሚፈጥረው ፍጡራን መያዝ ነው፥ ጥራት ይገባው! እርሱ አሸናፊው አንዱ አሏህ ነው፡፡ በሌላ አንቀጽ ደግሞ "ከ-እኛ ዘንድ" በማለት እርሱ ዘንድ "ከ-ተፈጠሩ ፍጥረታት" መያዝ ቢፈልግ ልጅ መያዝ ይችል ነበር፥ ነገር ግን ጥራት ይገባው! ይህ ለእርሱ ተገቢ አይደለም፦
21፥17 መጫወቻን "ልንይዝ" ብንፈልግ ኖሮ "ከ-እኛ ዘንድ" በያዝነው ነበር፡፡ ግን ሠሪዎች አይደለንም፡፡ لَوْ أَرَدْنَا أَن نَّتَّخِذَ لَهْوًا لَّاتَّخَذْنَاهُ مِن لَّدُنَّا إِن كُنَّا فَاعِلِينَ

እዚህ አንቀጽ "መጫወቻ" ለሚለው የገባው ቃል "ለህው" لَهْو ሲሆን "መደሰቻ" "መጠቀሚያ" "የዓይን ማረፊያ እና መርጊያ" ማለት ነው፥ ልጅ ለወላጅ ሆነ ለአሳዳጊ መደሰቻ ነው።
21፥17 ላይ በመጀመሪያ መደብ ያለውን ሐረግ የሚፈታልን 39፥4 ላይ በሦስተኛ መደብ ያለው ሐረግ ነው፥ በመጀመሪያ መደብ "አረድና" أَرَدْنَا ብሎ በሦስተኛ መደብ "አራደ" أَرَادَ ይለናል። "ከእኛ ዘንድ" የሚለውን "ከ-ሚፈጥረው" በማለት ይፈታልናል፥ "ከእኛ ዘንድ" የሚለውን ሚሽነሪዎች "ከእኛ ውስጥ" በማለት የአሏህ እኛነትን ብዙ አካላት እንደሆነ ለማመልከት ያጭበረብሩበታል። ነገር ግን "ዘንድ" እና "ውስጥ" የሚባሉትን መስተዋድድ በቅጡ ካለመረዳት የመጣ የተሳከረ፣ የደፈረሰ፣ የተንሸዋረረ ምልከታ ነው፦
19፥5 «እኔም ከበኋላዬ ዘመዶቼን በእርግጥ ፈራሁ፡፡ ሚስቴም መካን ነበረች ስለዚህ "ከ-አንተ ዘንድ" ለእኔ ልጅን ስጠኝ፡፡ وَإِنِّي خِفْتُ الْمَوَالِيَ مِن وَرَائِي وَكَانَتِ امْرَأَتِي عَاقِرًا فَهَبْ لِي مِن لَّدُنكَ وَلِيًّا

ዘከሪያ፦ "ከ-አንተ ዘንድ" ሲል "ከ-አንተ ውስጥ" ማለቱ አልነበረም፥ ቅሉ ግን ልጅ ከአሏህ ዘንድ የሚሰጥ ነው። አሏህ ልክ እንደ ፈርዖን ሚስት እና እንደ ያም ከምስር እንደ ገዛው ሰው መጫወቻ ልጅ መያዝ ቢፈልግ ኖሮ ከሚፈጥረው መያዝ ይችል ነበር፥ ነገር ግን ይህ ለእርሱ ተገቢ እንዳልሆነ እራሱ ተናግሯል። "መጫወቻን ልንይዝ ብንፈልግ ኖሮ ከእኛ ዘንድ በያዝነው ነበር" ሲል ዐውደ ንባቡ ላይ ከፈጠራቸው እርሱ ዘንድ ያሉትም መላእክት ያመለክታል፥ ቁረይሾችም "አልረሕማንም ከመላእክት ልጅን ያዘ" ብለዋልና፦
21፥19 በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉም የእርሱ ነው፡፡ "እርሱ ዘንድ" ያሉትም መላእክት" እርሱን ከማምለክ አይኮሩም፡፡ አይሰለቹምም፡፡ وَلَهُ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ وَمَنْ عِندَهُ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِ وَلَا يَسْتَحْسِرُونَ
21፥26 «አልረሕማንም ከመላእክት ልጅን ያዘ» አሉ፡፡ ጥራት ተገባው፡፡ አይደለም መላእክት የተከበሩ ባሮች ናቸው፡፡ وَقَالُوا اتَّخَذَ الرَّحْمَـٰنُ وَلَدًا ۗ سُبْحَانَهُ ۚ بَلْ عِبَادٌ مُّكْرَمُونَ

"እርሱ ዘንድ" "አንተ ዘንድ" "እኛ ዘንድ" የሚለው እርሱ ዘንድ ያሉትን ፍጡራን ለማመልከት የመጣ ነው፥ ጥቅሉ ግን በአሏህ ባሕርይ መውለድ የሚባል ባሕርይ ካለመኖር ባሻገር ሳይወልድ እንደ ማደጎ ከሚፈጥረው መጫወት ልጅ መያዝ አይፈልግም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
7.5K viewsedited  05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 08:23:18 ልጅን አልያዘም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

39፥4 አላህ ልጅን መያዝ በፈለገ ኖሮ ከሚፈጥረው ውስጥ የሚሻውን ይመርጥ ነበር፡፡ ጥራት ተገባው፡፡ እርሱ አሸናፊው አንዱ አላህ ነው፡፡ لَّوْ أَرَادَ اللَّهُ أَن يَتَّخِذَ وَلَدًا لَّاصْطَفَىٰ مِمَّا يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ سُبْحَانَهُ ۖ هُوَ اللَّهُ الْوَاحِدُ الْقَهَّارُ

አምላካችን አሏህ በእርሱ ባሕርይ ላይ መውለድ እና መወለድ የለውም፥ "አሏህ ወለደ" ያሉት እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፦
112፥3 አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ
37፥152 «አላህ ወለደ፡፡» አሉ፥ እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡ وَلَدَ اللَّهُ وَإِنَّهُمْ لَكَاذِبُونَ
43፥15 ከባሮቹም ለእርሱ ቁራጭን ልጅ አደረጉለት፡፡ ሰው በእርግጥ ግልጽ ከሓዲ ነው፡፡ وَجَعَلُوا لَهُ مِنْ عِبَادِهِ جُزْءًا ۚ إِنَّ الْإِنسَانَ لَكَفُورٌ مُّبِينٌ

ከአንዱ አምላህ ባሕርይ ባሕርይን ወስዶ፣ ከአካሉ አካልን ወስዶ፣ እርሱን አህሎና መስሎ ከእርሱ ወጣ፣ ተወለደ፣ ተገኘ በማለት አሏህን ወላዲ መሢሑን ተወላዲ በማድረግ ለአሏህ ቁራጭን አደረጉለት።
ፈጣሪ እምቅድመ ዓለም "ወለደ" ከሚሉት በተጨማሪ አንዳንድ የክርስትና አንጃዎች "ፈጣሪ ልጅ ይዟል" የሚል አስተምህሮት በጥንት ጊዜ ነበረ፥ ለምሳሌ፦ ኖላዊ ዘሄርማስ(የሄርሜኑ እረኛ)፣ ኢቦናይታውያን ክርስቲያን እና በበባዛንታይኑ ቴዎዶስ እና በአንጾኪያው በጳውሎስ ሳምሳጤ የተጀመረው ዳይናሚክ ሞናርኪዝም"Adoptionism" ሁሉም "ፈጣሪ ልጅ ይዟል" ብለዋል። ነገር ግን አሏህ ምንም ልጅን አልያዘም፦
19፥88 «አር-ረሕማንም ልጅን ያዘ» አሉ፡፡ وَقَالُوا اتَّخَذَ الرَّحْمَـٰنُ وَلَدًا
23፥91 አላህ ምንም ልጅን አልያዘም፡፡ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ

"ኢተኸዘ" اتَّخَذَ የሚሉት "ወለደ" وَلَدَ ከሚለውን እሳቤ ለመሸሽ ያመጡት እሳቤ ነው፥ "መያዝ" እና "መውለድ" ልዩነት አለው፦
28፥9 የፈርዖንም ሚስት፦ "ለእኔ ለአንተም የዓይኔ መርጊያ ነው፤ አትግደሉት፡፡ ሊጠቅመን ወይም "ልጅ አድርገን ልንይዘው ይከጀላልና" አለች፡፡ وَقَالَتِ امْرَأَتُ فِرْعَوْنَ قُرَّتُ عَيْنٍ لِّي وَلَكَ ۖ لَا تَقْتُلُوهُ عَسَىٰ أَن يَنفَعَنَا أَوْ نَتَّخِذَهُ وَلَدًا
12፥21 ያም ከምስር የገዛው ሰው ለሚስቱ፦ «መኖሪያውን አክብሪ! ሊጠቅመን ወይም "ልጅ አድርገን ልንይዘው" ይከጀላልና» አላት፡፡ وَقَالَ الَّذِي اشْتَرَاهُ مِن مِّصْرَ لِامْرَأَتِهِ أَكْرِمِي مَثْوَاهُ عَسَىٰ أَن يَنفَعَنَا أَوْ نَتَّخِذَهُ وَلَدًا

የፈርዖን ሚስት ለፈርዖን ስለ ሙሣ፦ "ልጅ አድርገን ልንይዘው ይከጀላል" ስትል "እንወልደዋለን" ማለቷ አይደለም፥ የተወለደን ልጅ ማደጎ አርጎ መያዟን የሚያመለክት ነው። በተመሳሳይ ዮሡፍን ያም ከምስር የገዛው ሰው ለሚስቱ፦ "ልጅ አድርገን ልንይዘው ይከጀላል" ሲላት "እንወልደዋለን" ማለቱ አይደለም፥ የተወለደን ልጅ ማደጎ አርጎ መያዟን የሚያመለክት ነው። እዚህ ድረስ ከተግባባን አሏህ በማደጎ ልጅ መያዝ አይፈልግም፥ ቢፈልግ ኖሮ ግን "ከ-ሚፈጥረው" ውስጥ መርጦ ይይዝ ነው፦
39፥4 አላህ ልጅን መያዝ በፈለገ ኖሮ "ከ-ሚፈጥረው" ውስጥ የሚሻውን ይመርጥ ነበር፡፡ ጥራት ተገባው፡፡ እርሱ አሸናፊው አንዱ አላህ ነው፡፡ لَّوْ أَرَادَ اللَّهُ أَن يَتَّخِذَ وَلَدًا لَّاصْطَفَىٰ مِمَّا يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ سُبْحَانَهُ ۖ هُوَ اللَّهُ الْوَاحِدُ الْقَهَّارُ
7.4K views05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ