Get Mystery Box with random crypto!

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የሰርጥ አድራሻ: @wahidcom
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 34.43K
የሰርጥ መግለጫ

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-09-09 20:53:24 ሁሉን ዓቀፍ ደኅንነት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

5፥72 እነሆ በአሏህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ

በኢሥላም አስተምህሮት ሰው በአሏህ ላይ ላሻረከው የሺርክ ወንጀል አሏህ በእርግጥ ጀነትን እርም አድርጎበታል፥ ለሙሽሪክ መኖሪያውም እሳት ናት። አሏህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፥ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል፦
5፥72 እነሆ በአሏህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ
4፥48 አሏህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም ኀጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ

ወደ ባይብል ስንሄድም የማያምኑ የሚቀጡበት ቅጣት ዘውታሪ ቅጣት ለመሆኑ እኵሌቶቹ ወደ እፍረት እና ወደ ዘላለም ጕስቍልና እንደሚሄዱ ይናገራል፦
ዳንኤል 12፥2 በምድርም ትቢያ ውስጥ ካንቀላፉቱ ብዙዎች ይነቃሉ፤ እኵሌቶቹ ወደ ዘላለም ሕይወት፥ እኵሌቶቹም ወደ እፍረት እና "ወደ ዘላለም ጕስቍልና"።
ኤርምያስ 23፥40 የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን "የዘላለምን እፍረት" አመጣባችኋለሁ።

ይህ ሆኖ ሳለ "ሁሉን ዓቀፍ ደኅንነት"universal salvation" የሚባለው ትምህርት "ሰው ሁሉ የሚቀጣው ቅጣት ተቀጥቶ ሁሉም ከገሃነም ይድንና ገነት ይገባል" የሚል ትምህርት ነው፥ ይህንን ትምርህት ከሚያስተምሩት የጥንት የቤተክርስቲያን አበው መካከል፣ በ 180 ድኅረ ልደት ቅዱስ ፔንታነስ፣ በ 150 ድኅረ ልደት የእስክንድርያው ቀለሜንጦስ፣ በ 220 ድኅረ ልደት የእስክንድርያው አርጌንስ እና በ 400 ድኅረ ልደት ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ተጠቃሽ ናቸው። እነርሱም ከሚጠቅሱስ ተወዳጆች ጥቅሳት መካከል ግንባር ቀደም ይህ ነው፦
ማርቆስ 9፥49 ሰው ሁሉ በእሳት ይቀመማልና፥ መሥዋዕትም ሁሉ በጨው ይቀመማል።

መሥዋዕት ሁሉ በጨው የሚቀመመው በጨው እንደሆነ ሰውም በእሳት መቀጣቱ ለእርማት መሆኑን ይናገራሉ፦
ዕብራውያን 12፥9-11 ከዚህም በላይ የቀጡን የሥጋችን አባቶች ነበሩን እናፍራቸውም ነበር፤ እንዴትስ ይልቅ ለመናፍስት አባት አብልጠን ልንገዛና በሕይወት ልንኖር በተገባን? እነርሱ መልካም ሆኖ እንደ ታያቸው ለጥቂት ቀን ይቀጡን ነበርና፥ እርሱ ግን ከቅድስናው እንድንካፈል ለጥቅማችን ይቀጣናል። ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፥ ዳሩ ግን በኋላ ለለመዱት የሰላምን ፍሬ እርሱም ጽድቅን ያፈራላቸዋል።

"እርሱ ግን ከቅድስናው እንድንካፈል ለጥቅማችን ይቀጣናል" በሚለው ውስጥ ሁሉም ጥፋተኛ የጥፋቱን ልክ ተቀጥቶ ወደ ገነት ይገባል የሚል ትምህርት ነው፥ "ቅጣት ሁሉ ለጊዜው የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም" ማለቱ "የገሃነም ቅጣት ጊዜአዊ ነው" የሚል መደምደሚያ ላይ ደርሰዋል፦
1 ጢሞቴዎስ 4፥10 ሰውን ሁሉ ይልቁንም የሚያምኑትን በሚያድን በሕያው አምላክ ተስፋ ስለምናደርግ ነው።

ሕያው አምላክ የሚያምኑት ብቻ ሳይሆን "ሰውን ሁሉ" እንደሚያድን ከላይ ያለው ጥቅስ ፍንጭ ይሰጣል፥ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን ይህ ጸጋ የተገለጠው ሰዎች ሁሉ ሊድኑ በሚወድ በአምላክ ፊት መልካም እና ደስ የሚያሰኝ ጳውሎስ ተናግሯል፦
ቲቶ 2፥11 ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና።
1 ጢሞቴዎስ 2፥3 ሰዎች ሁሉ ሊድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካም እና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው።
ሮሜ 5፥19 በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ፥ እንዲሁ ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።

"ብዙዎች" የሚለው ቃል "ሁሉም" በሚል ይረዱትና ሁሉም ሰው በአንዱ አዳም ኃጢአተኞች ከሆኑ ሁሉም ሰው በአንዱ ክርስቶስ ጻድቃን ይሆናሉ የሚል ትምህርት ነው። ታዲያ ለምን ብዙ ቦታ "በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ" ይላል?፦
2 ተሰሎንቄ 1፥9 ከጌታ ፊት ከኃይሉም ክብር ርቀው በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ። οἵτινες δίκην τίσουσιν ὄλεθρον αἰώνιον ἀπὸ προσώπου τοῦ Κυρίου καὶ ἀπὸ τῆς δόξης τῆς ἰσχύος αὐτοῦ,

እዚህ አንቀጽ ላይ "ዘላለም" የሚለው የግሪከኛ ቃል "አይኦንዮን" αἰώνιον ሲሆን መጨረሻ የሌለው ዝንተ ዓለም ጊዜ ብቻ ሳይሆን የማይታወቅ መጻኢ ውስን ጊዜን ስለሚያመለክት "ቅጣቱ ጊዜአዊ ነው" በማለት "አይኦንዮን" αἰώνιον ለማይታወቅ መጻኢ ውስን ጊዜን የተጠቀመበት ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦
ይሁዳ 1፥7 "በዘላለም እሳት" እየተቀጡ ምሳሌ ሆነዋል። πρόκεινται δεῖγμα πυρὸς αἰωνίου δίκην ὑπέχουσαι.

"ሰዶምና ገሞራ በዙሪያቸውም የነበሩ ከተማዎች የተቀጡት ለውስን ጊዜ ቢሆንም ቅጣታቸውን "በዘላለም እሳት" በማለት ተናገረ ማለት መጨረሻ የሌለው ዝንተ ዓለም ጊዜ አይደለም" በማለት ይሞግታሉ። ይህ ሙግት ሥነ ልቡናዊ ሙግት ቢመስልም ውኃ የሚያነሳ እና የሚቋጥር ሙግት አይደለም፥ ምክንያቱም ሰው በገነት ለሚኖረው ዘላለማዊ ሕይወት የገባው ቃል ተመሳሳይ "አይኦንዮን" αἰώνιον ነው፦
ማቴዎስ 25፥46 እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ። καὶ ἀπελεύσονται οὗτοι εἰς κόλασιν αἰώνιον, οἱ δὲ δίκαιοι εἰς ζωὴν αἰώνιον.

"ዘላለም ቅጣት" ለሚለው የገባው "አይኦንዮን" αἰώνιον የማይታወቅ መጻኢ ውስን ጊዜን ካመለከተ ጻድቃን የሚገቡበት "ዘላለም ሕይወት" ለሚለው የገባው "አይኦንዮን" αἰώνιον የማይታወቅ መጻኢ ውስን ጊዜ ነውን? ገሃነም ጊዜአዊ ከሆነ ቢያንስ "ወደ ገነት ይገባሉ" ይባል ይሆናል፥ ገነት እንደ ገሃነም ጊዜአዊ ከሆነ ከገነት ወደ የት ይገባሉ? ይህ የተመታ እና የተምታታ ትምህርት እነ ቅዱስ ፔንታነስ፣ እነ የእስክንድርያው ቀለሜንጦስ፣ እነ የእስክንድርያው አርጌንስ፣ እነ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ የጠነሰሱት ጥንስስ የጳውሎስን ትምህርት መሠረት አርገው ነው። ዛሬ በዘመናችን ሁሉን ዓቀፍ ደኅንነት የሚባል ትምህርት ከሚያስተምሩ መካከል የእግዚአብሔር መንግሥት ቤተክርስቲያን መስራች ካሳ ኬርጋ እና አዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ የመሳሰሉት ናቸው።
ይህንን ትምህርት የሚያስየምሩት እና ባለማወቅ የሚማሩትን አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
12.7K views17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-06 12:49:00
አሥ ሠላም ዐለይኩም ያ ጀመዓህ!

ወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር ይህንን የሃይማኖት ንጽጽር መተግበሪያ"application" ለሕዝበ ሙሥሊሙ አዘጋጅቷል። በገጠር አውታረ መረብ"network" የሌላቸው እና በከተማ የአውታረ መረብ ችግር ያለባቸው ያለ አውታረ መረብ ይህንን መተግበሪያ በማውረድ መጠቀም ይችላሉ። አውርደው በውስጡ ያለውን ርእሰ ጉዳይ እንዴት መጠቀም እንዳለብዎ እዚህ ላይ የተቀመጠውን ቪድዮ ይመልከቱ!
ሁላችንም በፓስት፣ በኮሜት፣ በራሳችሁ የጊዜ መስመር"timeline" ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ መሆን ይችላሉ።
ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.hexlabs.wahidislamicapologetics
12.8K views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-29 04:34:56
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ያ ጀመዓህ!

ተውሒድ የሁለቱም ዓለም ስኬት ነው፥ በተውሒድ ዙሪያ "ካሊቂ አድን ቢቶ"(ፈጣሪ አንድ ነው) በሚል ርእስ በስልጥኛ ቋንቋ ያዘጋጀነው 6ኛ መጽሐፌ በአት ተውባህ የመጻሕፍት መደብር ያገኙታል። ለበለጠ መረጃ፦
ወንድም ዐብዱር ራሕማን +251920781016 ብለው ይደውሉ!

የስልጤ ሕዝብ ላይ ካንዣበበት የኩፍር ማንዣበብ ነጻ ለማውጣት "ይህ መጽሐፍ ሁነኛ ፍቱን መድኃኒት ነው" ብለን ስለምናምን ለሌሎች ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን ሼር እናድርግ። ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!
13.0K views01:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-30 01:02:02 በቅርብ ቀን በቪድዮ ተከታታይ ትምህርት በዚህ ዩቱብ ቻናል ይለቀቃል። ሰብስክራይብ፣ ሼር እና ላይክ በማድረግ ተደራሽነቱን ይወጡ! https://youtube.com/@Wahidislamicapologist
12.6K views22:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-26 12:12:30 ኢየሱስ አብ ነውን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

59፥24 እርሱ አላህ ፈጣሪው፣ "አስገኚው"፣ ቅርጽን አሳማሪው ነው፡፡ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት፡፡ هُوَ اللَّهُ الْخَالِقُ الْبَارِئُ الْمُصَوِّرُ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ

አምላካችን አሏህ በቁርኣን ከተገለጹ ዘጠና ዘጠኝ ስሞቹ አንዱ "አል ባሪእ" الْبَارِئ ማለትም "አስገኚው" ነው፦
59፥24 እርሱ አላህ ፈጣሪው፣ "አስገኚው"፣ ቅርጽን አሳማሪው ነው፡፡ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት፡፡ هُوَ اللَّهُ الْخَالِقُ الْبَارِئُ الْمُصَوِّرُ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ

በዕብራይስጥ ለአንዱ አምላክ "አብ" אָ֑ב ማለት "አስገኚ" "ምንጭ" ማለት ነው፥ አንዱ አምላክ ሰውን ጭቃ አርጎ ስለ ሠራ "አብ" אָ֑ב ተብሏል፦
ኢሳይያስ 64፥8 ያህዌህ ሆይ! አንተ አባታችን ነህ፤ እኛ ጭቃ ነን አንተም ሠሪያችን ነህ፥ እኛም ሁላችን የእጅህ ሥራ ነን። יְהוָ֖ה אָבִ֣ינוּ אָ֑תָּה אֲנַ֤חְנוּ הַחֹ֙מֶר֙ וְאַתָּ֣ה יֹצְרֵ֔נוּ וּמַעֲשֵׂ֥ה יָדְךָ֖ כֻּלָּֽנוּ׃

እዚህ አንቀጽ ላይ አንዱ አምላክ "አብ" אָ֑ב ሲባል ሰዎች "ጭቃ" ተብለዋል፥ ጭቃው የእጁ ሥራ ሲሆን "አባት" የሚለው "ሠሪ" ማለት ስለሆነ "አባታችን" የሚለው "ሠሪያችን" በሚል ተለዋዋጭ ቃል መጥቷል። "ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? ሲልም "ለሁላችን አንድ ሠሪ" መኖሩን የሚያሳይ ነው፦
ሚልክያስ 2፥10 ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን? הֲלֹ֨וא אָ֤ב אֶחָד֙ לְכֻלָּ֔נוּ הֲלֹ֛וא אֵ֥ל אֶֽחָ֖ד בְּרָאָ֑נוּ
ዮሐንስ 8፥41 አንድ አባት አለን፥ እርሱም አምላክ ነው። ἕνα Πατέρα ἔχομεν τὸν Θεόν.
ኤፌሶን 4፥6 አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ። εἷς Θεὸς καὶ Πατὴρ πάντων,

"አባት" ለአንዱ አምላክ ሲቀጸል በራሱ "አስገኚ" ማለት እንጂ "የባሕርይ አባት" ማለት አይደለም። ይህ ሆኖ ሳለ የሐዋርያት ቤተክርስቲያን በተለምዶው ኢየሱስ ብቻ"only Jesus" የሚባሉት "ኢየሱስ አብ ነው" ብለው ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦
ዮሐንስ 14፥10 ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል። ὁ δὲ Πατὴρ ἐν ἐμοὶ μένων ποιεῖ τὰ ἔργα αὐτοῦ.

ይህ ጥቅስ ጭራሽ "እኔ" የሚለው ማንነት እና "እኔ" በሚለው የሚኖረው አብ ሁለት ማንነት እንደሆኑ ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ እዚህ አንቀጽ ላይ "የሚኖር" ለሚለው የገባው ቃል "ሜኖን" μένων ነው። አብ በኢየሱስ መኖሩ ኢየሱስን አብ ካሰኘውማ በፍቅር የሚኖር ሰው አምላክ ሊሆን ነው፦
1ኛ ዮሐንስ 4፥16 በፍቅርም የሚኖር በአምላክ ይኖራል፥ "አምላክ በእርሱ ይኖራል"። καὶ ὁ μένων ἐν τῇ ἀγάπῃ ἐν τῷ Θεῷ μένει καὶ ὁ Θεὸς ἐν αὐτῷ μένει.

እዚህ አንቀጽ ላይ "ይኖራል" ለሚለው የገባው ቃል "ሜኔይ" μένει ሲሆን ከላይ ካለው ጋር በተመሳሳይ መሠረቱ "ሜኖ" μένω ነው፥ ታዲያ በፍቅር የሚኖር ሰው አምላክ ነውን? በመቀጠል "ኢየሱስ አብ ነው" ብለው ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦
ዮሐንስ 14፥11 እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ። πιστεύετέ μοι ὅτι ἐγὼ ἐν τῷ Πατρὶ καὶ ὁ Πατὴρ ἐν ἐμοί·

"እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ" ማለቱ ኢየሱስን አብ አብን ኢየሱስ ካደረገው ሐዋርያት ኢየሱስ ወይም ኢየሱስ ሐዋርያት ይሆኑ ነበር፦
ዮሐንስ 14፥20 እኔ በአባቴ እንዳለሁ እናንተም በእኔ እንዳላችሁ እኔም በእናንተ እንዳለሁ በዚያን ቀን ታውቃላችሁ። ἐν ἐκείνῃ τῇ ἡμέρᾳ γνώσεσθε ὑμεῖς ὅτι ἐγὼ ἐν τῷ Πατρί μου καὶ ὑμεῖς ἐν ἐμοὶ κἀγὼ ἐν ὑμῖν.

"እናንተም በእኔ እንዳላችሁ እኔም በእናንተ እንዳለሁ" ማለቱ ሐዋርያት ከኢየሱስ ጋር ያላቸውን ግኑኝነት የሚያሳይ እንጂ ሐዋርያትን ኢየሱስ ካላደረገ እንግዲያውስ "እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ" ማለቱ አብ ከኢየሱስ ጋር ያለውን ግኑኝነት የሚያሳይ እንጂ ኢየሱስን አብ አያደርገውም። በነገራችን ላይ ሥላሴአውያን ለኢየሱስ አምላክነት ከሚጠቅሷቸው ተወዳጆች ጥቅስ አንዱ ነውና ሙግቱ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ነው፥ ስለዚህ ኢየሱስ አብ ወይም አምላክ ሳይሆን የአምላክ መልእክተኛ ነው። እናንተንም አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
12.6K views09:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 12:29:22 ኢንጂል

ክፍል አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣንም አስከተልን፥ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰ آثَارِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ وَآتَيْنَاهُ الْإِنجِيلَ

ኢየሱስ ከአምላኩ ግልጠተ መለኮት በተቀበለበት በዐረማይስጥ ቋንቋ "ኢዋንገሊዎን" ܐܘܢܓܠܝܘܢ ማለት "ብሥራት" "የምስራች" "መልካም ዜና" ማለት ሲሆን "ኢዋንገሊዎን" ܐܘܢܓܠܝܘܢ ወደ ዐረቢኛ ሙዐረብ ሆኖ ሲገባ "ኢንጂል" إِنْجِيل ሲባል፣ ወደ ግሪክ ሲገባ "ዩአንጌሎስ" εὐάγγελος ሲባል፣ ወደ ግዕዝ ሲገባ ደግሞ "ወንጌል" ተባለ። አምላካችን አሏህ ለዒሣ ኢንጂልን በመስጠት መልእክተኛ አርጎ ልኮታል፦
57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣንም አስከተልን፥ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰ آثَارِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ وَآتَيْنَاهُ الْإِنجِيلَ

በባይብልም ቢሆን ኢየሱስ ከላከው ከአምላክ መልእክት እየሰማ የሚያስተላለፍ መልእክተኛ ነበር፦
ዮሐንስ 8፥26 የላከኝ እውነተኛ ነው እኔም ከእርሱ "የሰማሁትን" ይህን ለዓለም እናገራለሁ።
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን ከአምላክ "የሰማሁትን" እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ። νῦν δὲ ζητεῖτέ με ἀποκτεῖναι, ἄνθρωπον ὃς τὴν ἀλήθειαν ὑμῖν λελάληκα, ἣν ἤκουσα παρὰ τοῦ Θεοῦ·

እዚህ አንቀጽ ላይ "አምላክ" አሰሚ ባለቤት ሲሆን "ሰው" ሰሚ ተሳቢ ነው፥ በአምላክ እና በሰው መካከል "የሰማሁት" የሚል አጫፋሪ ግሥ"transitive verb" አለ። መልእክተኛው ኢየሱስ የሚናገረው የላከው እንደነገረው እንጂ ከራሱ ምንም አልተናገረም፦
ዮሐንስ 12፥50 ስለዚህ እኔ የምናገረውን አብ እንደ ነገረኝ እንዲሁ እናገራለሁ።
ዮሐንስ 12፥49 እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን "የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ"።

"ትእዛዝ ሰጠኝ" የሚለው ይሰመርበት! ይህቺም ትእዛዝ ታላቂቱ እና ፊተኛይቱ ትእዛዝ "ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው" የምትል ተውሒድ ስትሆን የዘላለም ሕይወት ናት፦
ዮሐንስ 12፥50 "ትእዛዙም የዘላለም ሕይወት እንደ ሆነች" አውቃለሁ።
ማቴዎስ 22፥38 ታላቂቱ እና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።
ማርቆስ 12፥29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ "እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው"..የምትል ናት።

ጥንትም በቅዱሳን ነቢያት ቀድሞ የተባለውን ቃል እና በሐዋርያትም ከኢየሱስ የተገኘው ትእዛዝ "ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው" የሚል ጭብጥ ነው፦
2 ጴጥሮስ 3፥2 በቅዱሳን ነቢያትም ቀድሞ የተባለውን ቃል እና በሐዋርያቶቻችሁም ያገኛችኋትን የጌታን እና የመድኃኒትን ትእዛዝ እንድታስቡ በሁለቱ እያሳሰብኋችሁ ቅን ልቡናችሁን አነቃቃለሁ።

ኢየሱስ "የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ" ሲል ይህንን የአምላክ ትእዛዝ ከአምላክ ተቀብሎ ለሐዋርያት የሰጠው ቃል የአምላክ ቃል ነው፦
ዮሐንስ 17፥8 "የሰጠኸኝን ቃል" ሰጥቻቸዋለሁና።
ዮሐንስ 17፥14 እኔ "ቃልህን" ሰጥቻቸዋለሁ።

ኢየሱስ ወደ አምላኩ ሲጸልይ በሁለተኛ መደብ "ቃልህን" ማለቱ በራሱ የተሰጠው "ቃል" የአምላክ ቃል ነው፥ ሕዝቡም ሲሰማ የነበረው ቃል የላከው የአምላክ ቃል እንጂ የመልእክተኛው የራሱ ቃል አይደለም፦
ዮሐንስ 7፥16 ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው፦ "ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም"።
ዮሐንስ 14፥24 "የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም"።
ሉቃስ 5፥1 ሕዝቡም "የአምላክን ቃል" እየሰሙ ሲያስጠብቡት ሳሉ፥ እርሱ ራሱ በጌንሳሬጥ ባሕር ዳር ቆሞ ነበር።
ዮሐንስ 8፥47 ከአምላክ የሆነ "የአምላክን ቃል" ይሰማል።
ዮሐንስ 3፥34 አምላክ የላከው የአምላክንን ቃል ይናገራልና።

ኢየሱስ መልእክተኛ ነቢይ ሆኖ ከአምላኩ የተሰጠውን የአምላክን ቃል ይናገር ከነበረ እና ከራሱ ምንም ካልተናገረ ኢየሱስ ሙሉ ዕውቀት የለውም፥ ምክንያቱም ከአምላኩ የሚሰማው እርሱ ጋር ከሌለ እና ከአምላኩ ሰምቶ ከተናገረ ከላከው ዕውቀት ጋር እኩል ዕውቀት አይሆንም። እንግዲህ ኢየሱስ ከአምላኩ እየሰማ የተሰጠው የአምላክ ቃል ወንጌል ይባላል፥ ኢንሻላህ በክፍል ሁለት ስለዚህ ወንጌል እናያለን........

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
1.9K views09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 01:43:18 የመለኮት ሙላት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

43፥59 እርሱ በእርሱ ላይ የለገስንለት እና ለእስራኤል ልጆች ተአምር ያደረግነው የኾነ ባሪያ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا عَبْدٌ أَنْعَمْنَا عَلَيْهِ وَجَعَلْنَاهُ مَثَلًا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ

ነገርን መጠምዘዝ የሚቀናቸው ሚሽነሪዎች ያልተፈለገ መባልን ሲሉና "አሃ! እንዲህ ለማለት እኮ ነው!" እያሉ መለኮት በትስብእት እንደተገለጠ አርገው ከሚጠቅሷቸው ቅሰራዊ እና ቅየጣዊ ጥቅሶች መካከል ቆላይስይስ 2፥9 ነው። ባይብል ላይ ኢየሱስ መሢሕ፣ ነቢይ፣ መልእክተኛ መሆኑት በክብር ተቀምጦ ሳለ መለኮትን ለማላበስ በመሞከር የአህያ ሥጋ አልጋ ሲሉት ዐመድ ነገር ሆነዋል። ቆላይስይስ 2፥9 ላይ ያለውን ዐውድ "ውኃን ከጥሩ ነገርን ከሥሩ" የሚለውን አገርኛ ብሒል ይዘን እንሞግት!
"ሶማ" σῶμα ማለት "አካል" ማለት ሲሆን በጳውሎስ ትምህርት ውስጥ ቤተክርስቲያን የክርስቶስ አካል ስለሆነች "ሶማ" σῶμα ተብላለች፦
ቆላስይስ 1፥18 እርሱም የአካሉ ማለት የቤተ ክርስቲያን ራስ ነው። καὶ αὐτός ἐστιν ἡ κεφαλὴ τοῦ σώματος, τῆς ἐκκλησίας·

እነዚ አንቀጽ ላይ "ቤተ ክርስቲያን" ለሚለው የገባው ቃል "ኤክሌሲያ" ἐκκλησία ሲሆን ትርጉሙ "ጉባኤ" "ማኅበር" "ስብስብ" ማለት ነው፥ የምእመናን ስብስብ "ኤክሌሲያ" ይባላል። የመለኮት ሙላት ሁሉ በክርስቶስ በኤክሌሲያ ተገልጦ ይኖራል፦
ቆላስይስ 2፥9 "በ-"እርሱ" የመለኮት ሙላት ሁሉ በአካል ይኖራልና። ὅτι ἐν αὐτῷ κατοικεῖ πᾶν τὸ πλήρωμα τῆς Θεότητος σωματικῶς,

"በ-"እርሱ" የሚለው ይሰመርበት! "እርሱ" የሚለው ተውላጠ ስም "ክርስቶስ" የሚለውን የሚተካ ነው፥ አብ ሙላቱን ሁሉ በክርስቶስ በኩል እንዲኖር ፈቅዷልና፦
ቆላስይስ 1፥19 ሙላቱ ሁሉ በእርሱ እንዲኖር ፈቅዷልና። ὅτι ἐν αὐτῷ εὐδόκησεν πᾶν τὸ πλήρωμα κατοικῆσαι

ዐማርኛ ላይ "እግዚአብሔር" ወይም ኪንግጀምስ ቨርዢን ላይ "አብ" ብለው ያስቀመጡት በውስጠ ታዋቂነት አብን ወይም እግዚአብሔርን ስለሚያመለክት ነው፥ አብ መለኮት ሲሆን ሙላቱን በክርስቶስ በኩል ለቤተክርስቲያን ይገልጣል። በቆላስይ 2፥9 ላይ "አካል" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ሶማቲኮስ" σωματικῶς ሲሆን በጳውሎስ ትምህርት ውስጥ "አንድ አካል አለ" ብሎ የሚናገርላት ቤተክርስቲያን ናት፦ ቆላስይስ 1፥24 ኤፌሶን 4፥4 ሮሜ 12፥4-5 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥12 ቆላስይስ 3፥15 ተመልከት!

"መለኮት" የተባለው አብ ሲሆን ሙላቱ ደግሞ ሰዎች የሚሞሉት ጸጋ ነው፥ እዛው ዐውድ ላይ በክርስቶስ በኩል አማኞች ይህንን ሙላት እንደሚሞሉ ይናገራል፦
ቆላስይስ 2፥10 ለአለቅነትና ለሥልጣንም ሁሉ ራስ በሆነ በእርሱ ሆናችሁ "ተሞልታችኋል"። καὶ ἐστὲ ἐν αὐτῷ πεπληρωμένοι, ὅς ἐστιν ἡ κεφαλὴ πάσης ἀρχῆς καὶ ἐξουσίας,

"ተሞልታችኋል" የሚለው ይሰመርበት! "የመለኮት ሙላት" ማለት እና "መለኮት" ማለት ይለያያል፥ መለኮት አብ ሲሆን ሙላቱ ጸጋው ነው። ይህንን ስታውቁ ሙግቱ እግረ ሰረሰር እንደሚሆንባችሁ እሙን እና ቅቡል ነው፥ ቢመራችሁም ዋጡት። መለኮትን ሰው አይሞላም፥ ነገር ግን ጸጋውን ይሞላሉ፦
ኤፌሶን 3፥19 እስከ አምላክም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ ነው። ἵνα πληρωθῆτε εἰς πᾶν τὸ πλήρωμα τοῦ θεοῦ.

ጋንጩር እንዳለበት ክልው ክልው የሚያደርጋቸው ሚሽነሪዎች ነገርን አቅሎ ማርገብ እና አጃምሎ ማራገብ ስለሚወዱ እንጂ እዚህ አንቀጽ ላይ አማኞች የአምላክ ፍጹም ሙላት እንደሚሞሉ በግልጽ ይናገራል። በክርስቶስ በኩል የአብን ሙላት የሚሞሉት ሰዎች ከሆኑ የመለኮት ሙላት በክርስቶስ በኩል የሚኖረው ቤተክርስቲያን ውስጥ ነው፥ ስለዚህ ቆላስይስ 2፥9 "መለኮት በትስብእት ተገለጠ" ለሚል የክርስትና ተሠግዎት"Incarnation" ትምህርት ማስረጃም መረጃም መሆን አይችልም። እኛ ሙሥሊሞች አይሁዳውያን የሚጠብቁት መሢሕ ኢየሱስ ነው ብለን እናምናለን፥ ኢየሱስ አሏህ መጽሐፍ እና ነቢይነት የለገሰው ባሪያ እና ያለ አባት በመወለድ ለእስራኤልም ልጆች ተአምር የተደረገ ባሪያ ነው፦
43፥59 እርሱ በእርሱ ላይ የለገስንለት እና ለእስራኤል ልጆች ተአምር ያደረግነው የኾነ ባሪያ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا عَبْدٌ أَنْعَمْنَا عَلَيْهِ وَجَعَلْنَاهُ مَثَلًا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ

ለኢየሱስ ነቢይነትን እና መጽሐፍን የሰጠውን አንዱን አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
3.3K views22:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-27 19:06:20
7.5K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-27 13:04:36 እዚህ አንቀጽ ላይ "ይበልጣል" ለሚለው የገባው ቃል "ሜይዞን" μεῖζόν ሲሆን በላጩ አብ ሲሆን ተበላጩ ደግሞ ሁሉም ነው፥ ኢየሱስ አብ ስላልሆነ "ሁሉ" በሚል ቃላት ውስጥ ኢየሱስ ስለሚካተት አብ ኢየሱስን በባሕርይ ይበልጠዋል። ኢየሱስ፦ "ከ"እኔ" አብ ይበልጣል" ብሏል፦
ዮሐንስ 14፥28 "ከ"እኔ" አብ ይበልጣልና። ὁ Πατὴρ μείζων μού ἐστιν.

እዚህ አንቀጽ ላይ "ይበልጣል" ለሚለው የገባው ቃል "ሜይዞን" μείζων ሲሆን በላጩ አብ ሲሆን ተበላጩ ደግሞ ኢየሱስ ነው፥ "ከ" የሚለው መስተዋድድ መነሻ ቅጥያ የሆነለት "እኔ" የሚለው ተሳቢ ተውላጠ ስም የኢየሱስ ሙሉ "እኔነትን" ቁልጭ አርጎ ያሳያል፦
ዕብራውያን 2፥7 ከመላእክት ይልቅ በጥቂት አሳነስኸው። ἠλάττωσας αὐτὸν βραχύ τι παρ’ ἀγγέλους,

"ኤላሶን" ἐλάσσων ማለት "ማነስ" ማለት ሲሆን "ሜይዞን" μείζων ለሚለው ተቃራኒ ነው፥ ኢየሱስ ከመላእክት ያነሰው በባሕርይ ከሆነ ይልቁኑ ከአብ በባሕርይ ምንኛ ያንስ ይሆን?
"ኬኖሲስ" κένωσις የሚለው የግሪክ ኮይኔ ቃል "ኬኖ" κενόω ማለትም "ባዶ አደረገ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ከንቱነት" "ባዶነት"emptiness" ማለት ነው፦
ፊልጵስዩስ 2፥7 ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን "ባዶ አደረገ"። ἀλλὰ ἑαυτὸν ἐκένωσεν μορφὴν δούλου λαβών, ἐν ὁμοιώματι ἀνθρώπων γενόμενος· καὶ σχήματι εὑρεθεὶς ὡς ἄνθρωπος

እዚህ አንቀጽ ላይ "ባዶ አደረገ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ኤኬኖሴን" ἐκένωσεν ሲሆን ሥርወ-ቃሉ "ኬኖ" κενόω ነው፥ "ባዶ አደረገ" የሚለውን አንዳንድ የፕሮቴስታንት አንጃ እና ጎጥ፦ "አምላክነቱን ትቶ መጣ" በሚል ይረዱታል። አምላክነት የሆነ ቦታ አስቀምጠህ የምትመጣበት ጃኬት አይደለም፥ መጨመር እና መጉደል የፍጡር እንጂ የመለኮት ባሕርይ አይደለም። ነገር ግን እንደ ጳውሎስ ትምህርት ኢየሱስ ሕይወቱን በመስጠት ለሰው ልጆች ሲል ድሀ ሆነ ይለናል፦
2 ቆሮንቶስ 8፥9 የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና ሀብታም ሲሆን እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።

"ቸር ስጦታ" የተባለው ሕይወቱን መስጠቱን እንደሆነ ብዙ ቦታ ተናግሯል፦ ገላትያ 1፥4 ቲቶ 2፥14 ተመልከት! "ራሱን ባዶ አደረገ" ማለት "ራሱን አሳልፎ ሰጠ" ማለት ነው፥ ሕይወትን አሳልፎ ከሰጠ ትልቁ ድህነት(ባዶነት) ነው።
"የባሪያ መልክ" ማለት "ባርነት" ማለት ነው፥ ለምሳሌ "የአምልኮ መልክ" ማለት "አምልኮት" ማለት ነው፦
2 ጢሞቴዎስ 3፥5 የአምልኮት "መልክ" አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ። ἔχοντες μόρφωσιν εὐσεβείας τὴν δὲ δύναμιν αὐτῆς ἠρνημένοι· καὶ τούτους ἀποτρέπου.

"ሞርፎሲስ" μόρφωσις ወይም "ሞርፌ" μορφή የሚሉት ቃላት "ሞርፎ" μορφόω ከሚል ግሥ መደብ የመጣ ሲሆን "መልክ"form" ማለት ነው፥ ኢየሱስ ባርነት ይዞ እራሱን አዋረደ፦
ፊልጵስዩስ 2፥8 በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ። ἐταπείνωσεν ἑαυτὸν γενόμενος ὑπήκοος

ኢየሱስ፦ "ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል" ብሎ ባስተማረው መሠረት ራሱን በትህትና በማዋረዱ አምላክ ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው፦
ማቴዎስ 23፥12 ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል። καὶ ὅστις ταπεινώσει ἑαυτὸν ὑψωθήσεται.
ፊልጵስዩስ 2፥9 በዚህ ምክንያት ደግሞ አምላክ ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው። διὸ καὶ ὁ Θεὸς αὐτὸν ὑπερύψωσεν,

ከመላእክት ያሳነሰው እና እራሱን በማዋረዱ ከፍ ከፍ ያደረገው አንዱ አምላክ ከሆነ አንዱ አምላክ እና ኢየሱስ ሁለት ለየቅል ማንነት እና ምንነት ይሆናሉ፥ በምንነት ከተለያዩ ኢየሱስ ከአምላኩ ጋር በባሕርይ ሊስተካከል አይችልም። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
6.4K views10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-27 13:04:08 መተካከል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ

አምላካችን አሏህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል የራሱ ባሕርያት አሉት፥ እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም፦
42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ እና ምክሼ በጭራሽ የለም፦
112፥4 «ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡» وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ
19፥65 እርሱ የሰማያት እና የምድር በሁለቱም መካከል ላለው ሁሉ ጌታ ነው እና አምልከው! እርሱን በአምልኮ ላይ ታገስ! ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን?። رَّبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا فَاعْبُدْهُ وَاصْطَبِرْ لِعِبَادَتِهِ ۚ هَلْ تَعْلَمُ لَهُ سَمِيًّا

እዚህ አንቀጽ ላይ "ለእርሱ ሞክሼን ታውቃለህን" ሲል አሏህን የሚተካከው ብጤ እና ሞክሼ እንደሌለው በቂ ማሳያ ነው።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ኢየሱስ በአምላክ ኃይል በሕይወት ይኖራል፦
2 ቆሮንቶስ 13፥4 ነገር ግን "በ"-አምላክ ኃይል በሕይወት ይኖራል። ἀλλὰ ζῇ ἐκ δυνάμεως Θεοῦ.

"በ" የሚለው መስተዋድድ መነሻ ላይ ያለው "የአምላክ ኃይል" እና ክርስቶስ ሁለት ለየቅል የሆኑ ነገሮች ናቸው፥ በተመሳሳይ "ኃይል" የሚለው "መልክ" በሚል ተዋዋጭ ቃል መጥቷል፦
ፊልጵስዩስ 2፥6 እርሱ "በ-"አምላክ መልክ" ሲኖር ሳለ ከአምላክ ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም። ὃς ἐν μορφῇ Θεοῦ ὑπάρχων οὐχ ἁρπαγμὸν ἡγήσατο τὸ εἶναι ἴσα Θεῷ,

"በ" የሚለው መስተዋድድ መነሻ ላይ ያለው "የአምላክ መልክ" እና ክርስቶስ ሁለት ለየቅል የሆኑ ነገሮች ናቸው፥ "ሲኖር"being" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ሃይፓርኮን" ὑπάρχων ሲሆን ቀጣይነት ያለው የአሁኑ ግሥ ስለሚያመለክት ከመወለዱ በፊት ያለውን ቅድመ ህልውና በጭራሽ አያሳያም፥ ለዚያን ነው በእንግሊዝኛ በአላፊ ግሥ "Who, beinged in the form of God" ሳይሆን Who, being in the form of God" ብለው ያስቀመጡት። አየሱስ እራሱ ከአምላክ ጋር በስምምነት ያስተካከለው በአገልግሎት ዘመኑ እንደሆነ ቅቡል ነው፦
ዮሐንስ 5፥18 ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከአምላክ ጋር አስተካክሎ፦ "አምላክ አባቴ ነው" ስላለ፥ ἀλλὰ καὶ Πατέρα ἴδιον ἔλεγεν τὸν Θεόν, ἴσον ἑαυτὸν ποιῶν τῷ Θεῷ.

"ሳለ" የሚለው ጊዜን ለማመልከት የመጣ ሲሆን በአምላክ ኃይል በሚኖርበት ጊዜ ራሱን ከአምላክ ጋር አስተካክሎ፦ "አምላክ አባቴ ነው" ብሎ ተናገረ። "መተካከል" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ኢሱስ" ἴσος ሲሆን "መስማማት"agreement" ማለት ነው፦
ማርቆስ 14፥56 ብዙዎች በሐሰት ይመሰክሩበት ነበርና፥ ምስክርነታቸው ግን "አልተሰማማም"። πολλοὶ γὰρ ἐψευδομαρτύρουν κατ’ αὐτοῦ, καὶ ἴσαι αἱ μαρτυρίαι οὐκ ἦσαν.

እዚህ አንቀጽ ላይ ያለ አፍራሽ ስናስቀምጥ "መስማማት" ለሚለው የግሥ መደብ የተጠቀመበት በተመሳሳይ "ኢሱስ" ἴσος ነው፥ አምላክ አንድ ከሆነ እና ኢየሱስ ከአንድ አምላክ ጋር መስማማትን እንደ መቀማት አልቆጠረም። "ኢሱስ" ἴσος ገላጭ ቅጽል በተውሳከ ግሥ "ኡስ" ως ሲሆን "ልክ እንደ"as" ማለት ነው፦
ዘካሪያስ 12፥8 የዳዊትም ቤት በፊታቸው "እንደ" አምላክ እንደ ጌታ መልአክ ይሆናል። ὁ δὲ οἶκος Δαυὶδ ὡς οἶκος Θεοῦ, ὡς ἄγγελος Κυρίου ἐνώπιον αὐτῶν.

የዳዊት ቤት(ቤተሰብ) እንደ አምላክ እና እንደ የጌታ መልአክ ይሆናል ሲባል በባሕርይ ይስተካከላል ማለት ነውን? አምላክ፣ መልአክ እና የዳዊት ቤተሰብ በምንነት እንደሚለያዩ ሁሉ ክርስቶስ እና አምላክ በምንነት ይለያያሉ። ኢየሱስን የላከው አብ ከማንም ጋር በባሕርይ አይስተካከልም፦
ኢሳይያስ 46፥5 በማን ትመስሉኛላችሁ? ከማንስ ጋር ታስተካክሉኛላችሁ? τίνι με ὡμοιώσατε; ἴδετε, τεχνάσασθε, οἱ πλανώμενοι.

ይህ አንድ ነጠላ ማንነት "ከምን ጋር" ሳይሆን "ከማን ጋር" ማለቱ አብን በምንነት የሚስተካከል ማንነት እንደሌለ ቁልጭ አርጎ ያሳያል። "ሜጋስ" μέγας ማለት "ታላቅ" ማለት ሲሆን ገላጭ ቅጽል"Adjective" ነው፥ የሜጋስ አንጻራዊ ገላጭ ቅጽል "ሜይዞን" μεῖζόν ሲሆን ይህም አንጻራዊ ገላጭ ቅጽል የባሕርይ መበላለጥን ለማመልከት አገልግሎት ላይ ውሏል፦
ማቴዎስ 12፥6 ነገር ግን እላችኋለሁ ከመቅደስ "የሚበልጥ" ከዚህ አለ። λέγω δὲ ὑμῖν ὅτι τοῦ ἱεροῦ μεῖζόν ἐστιν ὧδε.

እዚህ አንቀጽ ላይ "የሚበልጥ" ለሚለው የገባው ቃል "ሜይዞን" μεῖζόν ሲሆን በላጩ ኢየሱስ ሰው ሲሆን ተበላጩ መቅደስ ደግሞ ድንጋይ በድንጋይ ላይ የተነባበረ ግዑዝ ነገር ነው፥ ይህ የባሕርይ መበላለጥን ያሳያል። ሰው፣ እንስሳ፣ እጽዋት፣ ማዕድናት በባሕርይ የተለያዩ ናቸው፥ የሰው ኑባሬ"being" ሰው ብቻ ነው። እዚህ ድረስ ከተግባባን ከሁሉ በላይ ሁሉን የፈጠረ አንድ አምላክ አብ ከሁሉ ይበልጣል፦
ዮሐንስ 10፥29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል። ὁ Πατήρ μου ὃ δέδωκέν μοι πάντων μεῖζόν ἐστιν
5.2K views10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ