Get Mystery Box with random crypto!

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የሰርጥ አድራሻ: @wahidcom
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 34.43K
የሰርጥ መግለጫ

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 29

2022-07-08 14:44:48 በሙሴ ሕግ አስቀድሞ የተወለደው የበኲር ልጅ ለያህዌህ ይሆናል፥ የበኵር ልጅ በእርሱ ፋንታ እንስሳ ይታረዳል። ይህንን ሕግ አብርሃም ፈጽሞታል፦
ዘጸአት 13፥2 በእስራኤል ልጆች ዘንድ ከሰውም ከእንስሳም ማሕፀንን የሚከፈት በኵር ሁሉ ለእኔ ቀድስልኝ የእኔ ነው።
ዘፍጥረት 26፥5 አብርሃም ቃሌን ሰምቶአልና፥ ፍርዴን ትእዛዜን ሥርዓቴን "ሕጌንም ጠብቆአልና"።

አብርሃም ሕጉ ከጠበቀ የበኵር ልጁ ሊሰዋ ነበር ማለት ነው። አምላካችን አሏህ ሁሉንም ነገር ዐዋቂ ነው፥ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው ይህ አንዱ አምላክ ቁርኣንን ወደ ነቢያችን"ﷺ" አውርዷል፦
33፥54 አላህ ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው። فَإِنَّ اللَّهَ كَانَ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا
25፥6 «ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው አወረደው፡፡ እርሱ መሓሪ አዛኝ ነውና» በላቸው፡፡ قُلْ أَنزَلَهُ الَّذِي يَعْلَمُ السِّرَّ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ إِنَّهُ كَانَ غَفُورًا رَّحِيمًا

"ነበእ" نَبَأ የሚለው ቃል "ነበአ" نَبَّأَ ማለትም "አወራ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ነቢብ" "የሩቅ ወሬ" ማለት ነው፥ ከአሏህ ዘንድ የሩቅ ወሬ የሚወርድለት ሰው "ነቢይ" نَبِيّ ሲባል "ነባቢ" "የሩቅ ወሬ አውሪ" ማለት ነው። ከአሏህ ዘንድ ወደ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ከወረደው የሩቅ ወሬ አንዱ ስለ ኢብራሂም እና ስለ ቤተሰቡ ነው፦
26፥69 በእነርሱም ላይ የኢብራሂምን "ወሬ" አንብብላቸው፡፡ وَاتْلُ عَلَيْهِمْ نَبَأَ إِبْرَاهِيمَ
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡ فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعْىَ قَالَ يَٰبُنَىَّ إِنِّىٓ أَرَىٰ فِى ٱلْمَنَامِ أَنِّىٓ أَذْبَحُكَ فَٱنظُرْ مَاذَا تَرَىٰ ۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفْعَلْ مَا تُؤْمَرُ ۖ سَتَجِدُنِىٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ

ኢብራሂም ሊሰዋው የነበረው ልጅ ኢስማኤል እንደሆነ ከቁርኣን ብቻ ሳይሆን ከባይብልም መለኮታዊ ቅሪት ከላይ እንዳብራራነው እናገኛለን። አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
8.2K viewsedited  11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 14:44:48 የዕርዱ ልጅ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡ فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعْىَ قَالَ يَٰبُنَىَّ إِنِّىٓ أَرَىٰ فِى ٱلْمَنَامِ أَنِّىٓ أَذْبَحُكَ فَٱنظُرْ مَاذَا تَرَىٰ ۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفْعَلْ مَا تُؤْمَرُ ۖ سَتَجِدُنِىٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ

"ኢሽማኤል" יִשְׁמָעֵאל‎ የሚለው ቃል የሁለት ዕብራይስጥ ቃላት ውቅር ነው፥ "ኢሽማ" שָׁמַע ማለት "ይሰማል" ማለት ሲሆን "ኤል" אֵל ማለት "አምላክ" ማለት ነው። በጥቅሉ "ኢሽማኤል" יִשְׁמָעֵאל‎ ማለት "አምላክ ጸሎቴን ሰማኝ" ማለት ነው፥ ይህ ስም የወጣበት ምክንያት አብርሃም፦ "አቤቱ ያህዌህ ሆይ! ምንን ትሰጠኛለህ? ያለ ልጅ እሄዳለሁ” ብሎ ለለመነው ልመና መልስ ፈጣሪም፦ "ከጉልበትህ የሚወጣው ይወርስሃል" በማለት ይመልስለታል፦
ዘፍጥረት 15፥2 አብራምም፦ አቤቱ አቤቱ ያህዌህ ሆይ! ምንን ትሰጠኛለህ? ያለ ልጅ እሄዳለሁ።
ዘፍጥረት 15፥4 እነሆም የያህዌህ ቃል እንዲህ ሲል መጣለት፦ ይህ አይወርስህም፤ ነገር ግን ከጉልበትህ የሚወጣው ይወርስሃል።

ፈጣሪም ከአብርሃም ጉልበት ስለወጣው የአብራኩ ክፋይ ሲናገር፦ "ስለ እስማኤልም ሰምቼሃለሁ፤ እነሆ ባርኬዋለሁ" በማለት ጸሎቱን ሰምቶታል፥ አብርሃምም አምላክ ጸሎቱን ስለሰማው የልጁን ስም "እስማኤል" ብሎ ጠራው፦
ዘፍጥረት 17፥20 ስለ እስማኤልም ሰምቼሃለሁ፤ እነሆ "ባርኬዋለሁ"።
ዘፍጥረት16፥15 አብራምም አጋር የወለደችለትን የልጁን ስም እስማኤል ብሎ ጠራው።

"ልጁን" የሚለው ይሰመርበት! አንዳንድ ዐላዋቂ የክርስትና መምህራን እስማኤል የአብርሃም ልጅ እንዳልሆነ እና እንዳልተባረከ ሲናገሩ ስንስማ ምን ያክል ባይብልን እንዳማያነቡ ያሳብቅብባቸዋል። አጋር የሳራ ባሪያ ብትሆንም ለአብርሃም ሚስቱ ነእንደነበረች እሙን እና ቅቡል ነው፥ ስለዚህ ልጇ ለኢብራሂም ሕጋዊ ልጅ ነው፦
ዘፍጥረት 16፥3 የአብራም ሚስት ሦራ ግብፃዊት ባሪያዋን አጋርን ወስዳ ለባልዋ ለአብራም ሚስት ትሆነው ዘንድ ሰጠችው።

አጋር የሳራ ባሪያ የነበረች መሆኗ በእስማኤል ልጅነት ላይ የሚፈይደው አሉላዊ ቁብ የለውም። ለምሳሌ ባላን የራሔል ባሪያ ስትሆን ለያዕቆብ ግን ሚስት ነበረች፥ ከእርሷም የተወለዱት ዳን እና ንፍታሌም ሕጋዊ ልጆች ናቸው፦
ዘፍጥረት 30፥4 ባሪያዋን ባላንም ሚስት ትሆነው ዘንድ ለእርሱ ሰጠችው፤ ያዕቆብም ደረሰባት።

በተጨማሪም ዘለፋ የልያ ባሪያ ስትሆን ለያዕቆብ ግን ሚስት ነበረች፥ ከእርሷም የተወለዱት ጋድ እና አሴር ሕጋዊ ልጆች ናቸው፦
ዘፍጥረት 30፥9 ልያም መውለድን እንዳቆመች ባየች ጊዜ ባሪያዋን ዘለፋን ወሰደች፥ ሚስት ትሆነውም ዘንድ ለያዕቆብ ሰጠችው።

ያዕቆብ አሥራ ሁለት ሕጋዊ ልጆች ያሉት ከባላን እና ከዘለፋ የወለዳቸውን ልጆች ጨምሮ እንደሆነ ሁሉ አብርሃምም ከሳራ ባሪያ ከሚስቱ ከአጋር የወለደው የበኲር ልጁም ሕጋዊ ልጁ ነው፦
ዘፍጥረት 17፥26 በዚያው ቀን አብርሃም ተገረዘ፥ እንዲሁ ልጁ እስማኤልም።
ዘፍጥረት 25፥9 ልጆቹ ይስሐቅ እና እስማኤል.....ቀበሩት።
ዘፍጥረት 16፥15 አብራምም አጋር የወለደችለትን የልጁን ስም እስማኤል ብሎ ጠራው።

ይህ የበኲር ልጅ እስማኤል ሁለተኛው ልጅ ይስሐቅ እስኪወለድ ድረስ የአብርሃም ብቸኛ ልጅ ነው፦
ዘፍጥረት 22፥16 እንዲህም አለው፦ ያህዌህ፦ በራሴ ማልሁ ይላል፤ ይህን ነገር አድርገሃልና፥ ብቸኛ ልጅህንም አልከለከልህምና። וַיֹּ֕אמֶר בִּ֥י נִשְׁבַּ֖עְתִּי נְאֻם־יְהוָ֑ה כִּ֗י יַ֚עַן אֲשֶׁ֤ר עָשִׂ֙יתָ֙ אֶת־הַדָּבָ֣ר הַזֶּ֔ה וְלֹ֥א חָשַׂ֖כְתָּ אֶת־בִּנְךָ֥ אֶת־יְחִידֶֽךָ׃

"ያኺድ" יָחִיד ማለት "ብቸኛ" ማለት ነው፥ እዚህ አንቀጽ ላይ የተቀመጠው ወሳኝ ቃል "ያኺድከ" יְחִידֶֽךָ ማለት "ብቸኛክ" ማለት ሲሆን የበኲር ልጅ ሌላ ልጅ እስኪወለድ ድረስ ለወላጅ ብቸኛ ልጅ ነው፦
ዘካርያስ 12፥10 ሰውም ለብቸኛ ልጁ እንደሚያለቅስ ያለቅሱለታል፥ ሰውም ለበኵር ልጁ እንደሚያዝን በመራራ ኀዘን ያዝኑለታል። אֲשֶׁר־דָּקָ֑רוּ וְסָפְד֣וּ עָלָ֗יו כְּמִסְפֵּד֙ עַל־הַיָּחִ֔יד וְהָמֵ֥ר עָלָ֖יו כְּהָמֵ֥ר עַֽל־הַבְּכֹֽור׃

እዚህ አንቀጽ ላይ የመጀመሪያ ልጅ ብቸኛ ልጅ መባሉን ልብ በል! ስለዚህ አብርሃም ሊሰዋ የነበረው የዕርዱ ልጅ የመጀመሪያ ልጁን ነው። ሲጀመር የዕርዱ ልጅ ይስሐቅ ቢሆን ኖሮ "ብቸኛ ልጅህን" የሚለው ትርጉም ይሰጣልን? ሲቀጥል ይስሐቅ ከመወለዱ በፊት አድጎ ዘር እንደሚኖረው ለአብርሃም ተነግሮታልም ያውቃልም፦
ዘፍጥረት 17፥19 ስሙንም ይስሐቅ ብለህ ትጠራዋለህ፤ ከእርሱ በኋላ ለዘሩ የዘላለም ቃል ኪዳን እንዲሆን ቃል ኪዳኔን ከእርሱ ጋር አቆማለሁ።

ታዲያ አብርሐም ልጁ ይስሐቅ ሳይወለድ ዘሩ እንደሚቀጥል እያወቀ ፈተና ነው ማለት ትርጉም ይኖረዋልን? ምክንያቱም ልጅህን ዕረድልኝ ፈተና ነው፥ ፈተና ትርጉም የሚኖረው ተፈታኙ የሚፈተነውን የማያውቅ ሲሆን ብቻ እና ብቻ ነው፦
ዘፍጥረት 22፥1 ከእነዚህም ነገሮች በኋላ ያህዌህ አብርሃምን "ፈተነው"።
6.9K viewsedited  11:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:08:58 ኢብራሂም በኢሥሐቅ ሲበሰር፦ "እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ?" ማለቱ ለምኖ ያገኘው ልጅ ሳይሆን ያላሰበው ልጅ መሆኑ አስረግጦና ረግጦ ያሳያል፥ ኢብራሂም እና ሣራህ የተበሰሩት በኢሥሐቅ ብቻ ሳይሆን በልጅ ልጃቸውም በያዕቁብም ነው። ኢብራሂም ኢሥሐቅ ሳይታረድ ተርፎ የልጅ ልጁ ያዕቆብ እንደሚወለድ ካወቀማ እና ይሥሐቅም ያዕቁብ የሚባል ልጅ እንደሚኖረዉ አስቀድሞ ከተበሰረ ልጅህን ዕረድልኝ ብሎ ማዘዙ ፈተናው ትርጉም አልባ ይሆን ነበር፥ ምክንያቱም ልጅህን ዕረድልኝ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው። ፈተና ትርጉም የሚኖረው ተፈታኙ የሚፈተነውን የማያውቅ ሲሆን ብቻ እና ብቻ ነው፦
37፥106 ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلْبَلَٰٓؤُا۟ ٱلْمُبِينُ
2፥124 ኢብራሂምንም ጌታው በቃላት በፈተነው እና በፈጸማቸው ጊዜ አስታውስ! «እኔ ለሰዎች መሪ አድራጊህ ነኝ» አለው፡፡ «ከዘሮቼም አድርግ» አለ፡፡ ቃል ኪዳኔ በዳዮቹን አያገኝም አለው፡፡ وَإِذِ ٱبْتَلَىٰٓ إِبْرَٰهِـۧمَ رَبُّهُۥ بِكَلِمَٰتٍۢ فَأَتَمَّهُنَّ ۖ قَالَ إِنِّى جَاعِلُكَ لِلنَّاسِ إِمَامًۭا ۖ قَالَ وَمِن ذُرِّيَّتِى ۖ

ሲጀመር ኢብራሂም የበኲር ልጁን ሊሰዋ ሲል በልጁ ፋንታ ዕርድ በግ መቅረቡ እና ይህም ሥርዓት መሠረት በማድረግ ዕርድ የሚካሄደው መካህ እንጂ ሻም አይደለም። ሲቀጥል አሏህ፦ "ቤቴን ለዘዋሪዎቹ፣ ለተቀማጮቹ፣ ለአጎንባሾቹ እና ለሰጋጆቹ አጥሩ" በማለት ቃል ኪዳን የያዘው ከኢብራሂም እና ከኢሥማዒል ጋር ነው፦
2፥125 ቤቱንም ለሰዎች መመለሻ እና ጸጥተኛ ባደረግን ጊዜ አስታውስ፡፡ ከኢብራሂምም መቆሚያ መስገጃን አድርጉ፡፡ ወደ ኢብራሂምና ወደ ኢስማዒልም፦ "ቤቴን ለዘዋሪዎቹ፣ ለተቀማጮቹ፣ ለአጎንባሾቹ እና ለሰጋጆቹ አጥሩ" ስንል ቃል ኪዳን ያዝን፡፡ وَإِذْ جَعَلْنَا الْبَيْتَ مَثَابَةً لِّلنَّاسِ وَأَمْنًا وَاتَّخِذُوا مِن مَّقَامِ إِبْرَاهِيمَ مُصَلًّى ۖ وَعَهِدْنَا إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ أَن طَهِّرَا بَيْتِيَ لِلطَّائِفِينَ وَالْعَاكِفِينَ وَالرُّكَّعِ السُّجُودِ

ይህ ጊዜው እዛው ዐውድ ላይ፦ "ኢብራሂምንም ጌታው በቃላት በፈተነው እና በፈጸማቸው ጊዜ" በማለት ይናገራል፥ በዚያን ጊዜ ኢብራሂም እና ኢሥማዒል፦ "ጌታችን ሆይ! ከእኛ ተቀበል፡፡ አንተ ሰሚውና ዐዋቂው አንተ ነህና" በማለት የቤቱን መሠረት ከፍ አርገዋል፦
2፥127 ኢብራሂም እና ኢሥማዒል «ጌታችን ሆይ! ከእኛ ተቀበል፡፡ አንተ ሰሚውና ዐዋቂው አንተ ነህና» የሚሉ ሲኾኑ ከቤቱ መሠረቶቹን ከፍ ባደረጉ ጊዜ አስታውስ፡፡ وَإِذْ يَرْفَعُ إِبْرَاهِيمُ الْقَوَاعِدَ مِنَ الْبَيْتِ وَإِسْمَاعِيلُ رَبَّنَا تَقَبَّلْ مِنَّا ۖ إِنَّكَ أَنتَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ

"ኑሡክ" نُسُك ማለት "ሥርዓተ መሥዋዕት" ማለት ሲሆን እዚሁ ቦታ ሥርዓተ መሥዋዕት እንዲፈጸም ወደ አሏህ ዱዓህ ያረጉት ኢብራሂም እና ኢሥማዒል ናቸው፦
2፥128 «ጌታችን ሆይ! ለአንተ ታዛዦችም አድርገን፡፡ ከዘሮቻችንም ለአንተ ታዛዦች ሕዝቦችን አድርግ፡፡ ሥርዓተ መሥዋዕቶቻችንንም አሳየን። رَبَّنَا وَاجْعَلْنَا مُسْلِمَيْنِ لَكَ وَمِن ذُرِّيَّتِنَا أُمَّةً مُّسْلِمَةً لَّكَ وَأَرِنَا مَنَاسِكَنَا

"ሀድይ" هَدْي ማለት "የዕርድ እንስሳ" ማለት ሲሆን ይህም እንስሳ ጊደር፣ በግ፣ ፍየል፣ ጥጃ፣ ግመል ነው፥ ይህም ዕርድ የሚካሄደው መካህ ውስጥ ነው፦
2፥196 ሐጅን እና ዑምራንም ለአላህ ሙሉ፤ ብትታገዱም ከሀድይ የተገራውን መሠዋት አለባችሁ፡፡ وَأَتِمُّوا الْحَجَّ وَالْعُمْرَةَ لِلَّهِ ۚ فَإِنْ أُحْصِرْتُمْ فَمَا اسْتَيْسَرَ مِنَ الْهَدْيِ
5፥97 አላህ ከዕባን የተከበረውን ቤት ለሰዎች መቋቋሚያ አደረገ፣ የተከበረውን ወር ሀድዩን እና ባለ ምልክቶቹንም መንጋዎች አደረገ፡፡ جَعَلَ اللَّهُ الْكَعْبَةَ الْبَيْتَ الْحَرَامَ قِيَامًا لِّلنَّاسِ وَالشَّهْرَ الْحَرَامَ وَالْهَدْيَ وَالْقَلَائِدَ
2፥200 የሐጅ ሥራዎቻችሁንም በፈጸማችሁ ጊዜ አባቶቻችሁን እንደምታወሱ ወይም ይበልጥ የበረታን ማውሳት አላህን አውሱ፡፡ فَإِذَا قَضَيْتُم مَّنَاسِكَكُمْ فَاذْكُرُوا اللَّهَ كَذِكْرِكُمْ آبَاءَكُمْ أَوْ أَشَدَّ ذِكْرًا

"ሥራዎቻችሁ" ለሚለው ቃል የተቀመጠው “መናሢከኩም" مَنَاسِكَكُمْ ሲሆን "ሥርዓተ መሥዋዕቶቻችሁ” ማለት ነው። ኢሥላም ዐቂደቱ አር-ረባንያህ ስንል አርቲ ቡርቲና ቶራ ቦራ የቡና ወሬ ይዘን ሳይሆን የአሏህን ንግግር ደሊል አድርገን ነው። አምላካችን አሏህ ቤቱን ከሚጎበኙት ሑጇጅ ያርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
6.8K viewsedited  08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:08:57 ነቢዩ ኢሥማዒል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥54 በመጽሐፉ ኢሥማዒልን አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ መልክተኛ ነቢይም ነበር፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا

አምላካችን አሏህ ወደ ኢሥማዒል ወሕይ አውርዷል፥ አሏህ ስለ ኢሥማዒል ሲናገር "በኢሥማዒል... ላይ በተወረደው አመንን በሉ" በማለት ግህደተ-መለኮት ወርዶለት እንደነበር በሡረቱል አለ ዒምራን 3፥84 በሡረቱል በቀራህ 2፥136 እና በሡረቱ አን-ኒስሳእ 4፥163 ላይ ይናገራል። ኢሥማዒል መልክተኛ እና ነቢይ ነበር፥ ቤተሰቦቹንም በሶላት እና በዘካህ ያዝ ነበር፦
19፥54 በመጽሐፉ ኢሥማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ መልእክተኛ ነቢይም ነበር፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا
19፥55 ቤተሰቦቹንም በሶላት እና በዘካህ ያዝ ነበር፡፡ እጌታውም ዘንድ ተወዳጅ ነበር፡፡ وَكَانَ يَأْمُرُ أَهْلَهُ بِالصَّلَاةِ وَالزَّكَاةِ وَكَانَ عِندَ رَبِّهِ مَرْضِيًّا

"እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረ" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! ይህም ቀጠሮ ኢብራሂም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፤ እርሱም «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አሏህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፦
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡ فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعْىَ قَالَ يَٰبُنَىَّ إِنِّىٓ أَرَىٰ فِى ٱلْمَنَامِ أَنِّىٓ أَذْبَحُكَ فَٱنظُرْ مَاذَا تَرَىٰ ۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفْعَلْ مَا تُؤْمَرُ ۖ سَتَجِدُنِىٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ

ይህ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፥ አሏህ ኢብራሂምን ልጁን እንዲሠዋ በጠየቀው ቃላት ፈተነው፦
37፥106 ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلْبَلَٰٓؤُا۟ ٱلْمُبِينُ
2፥124 ኢብራሂምንም ጌታው በቃላት በፈተነው እና በፈጸማቸው ጊዜ አስታውስ! «እኔ ለሰዎች መሪ አድራጊህ ነኝ» አለው፡፡ «ከዘሮቼም አድርግ» አለ፡፡ ቃል ኪዳኔ በዳዮቹን አያገኝም አለው፡፡ وَإِذِ ٱبْتَلَىٰٓ إِبْرَٰهِـۧمَ رَبُّهُۥ بِكَلِمَٰتٍۢ فَأَتَمَّهُنَّ ۖ قَالَ إِنِّى جَاعِلُكَ لِلنَّاسِ إِمَامًۭا ۖ قَالَ وَمِن ذُرِّيَّتِى ۖ قَالَ لَا يَنَالُ عَهْدِى ٱلظَّٰلِمِينَ

ኢብራሂም የተፈተነበት ልጅ ኢሥማዒልን ስለመሆኑ 2፥124 እና 37፥106 ከላይ እና ከታች ዐውደ ንባቡ ያስረዳል፥ "ኢሥማዒል" إِسْمَٰعِيْل የሚለው ስም የሁለት ቃላት ውቅር ነው፥ "ኢሥም" إِسْم የሚለው ቃል "አሥመዐ" أَسْمَعَ‎ ማለት "ሰማ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ይሰማል" ማለት ነው። "ዒል" عِيْل ደግሞ "ኢላህ" إِلَـٰهً ለሚል ምጻረ-ቃል ሲሆን "አምላክ" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "ኢሥማዒል" إِسْمَٰعِيْل ማለት "አምላክ ይሰማል" ማለት ነው። ኢብራሂም፦ "ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ" ብሎ አሏህ ጠይቆ አሏህም ዱዓውን በመስማት ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅ አበሰረው፦
37፥100 ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ፡፡ رَبِّ هَبْ لِى مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
37፥101 *ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው*፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
14፥39 ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነውና፡፡ إِنَّ رَبِّي لَسَمِيعُ الدُّعَاءِ

ኢብራሂም፦ "ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነው" ማለቱ በራሱ ኢብራሂም አሏህን ለምኖ ያገኘው እና ለዕርድ ሲጠየቅ የታገሰ ትእግስተኛ ልጁ ኢሥማዒል መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል። አሏህ በልጅ ጉዳይ ኢብራሂም ያበሰረው ሁለት ጊዜ ነው፥ የመጀመሪያው ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም ሲሆን ሁለተኛው በኢሥሐቅ ነው፦
37፥101 ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
37፥112 በኢሥሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡ وَبَشَّرْنَٰهُ بِإِسْحَٰقَ نَبِيًّۭا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ

"በኢሥሐቅ-"ም" የሚለው ይሰመርበት! "ም" የሚለው ጥገኛ ምዕላድ በዐማርኛ ተጨማሪ ነገርን ያሳያል፥ "አበሰርነው" የሚለው ቃል አንድ ዐውድ ላይ ሁለቴ መምጣቱ ኢሥሐቅ እና ከላይ የተጠቀሰው በዱዓ የመጣው ልጅ ይለያያሉ። በተጨማሪም "ወ" وَ የሚለው አርፉል አጥፍ ብስራቱ ሁለት ጊዜ መሆኑን ያሳያል፥ አንደኛው ረድፍ “ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅ” ሲሆን ሁለተኛው ረድፍ “በኢሥሐቅም አበሰርነው” የሚለው ነው። ኢሥሐቅ ደግሞ ኢብራሂም አሏህን ለምኖ የተሰጠ ልጅ ሳይሆን እርሱ እና ሣራህ አንወልድም ብለው ተስፋ በቆረጡበት የተበሰሩት ልጅ ነው፦
15፥53 «አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለን» አሉት፡፡ قَالُوا۟ لَا تَوْجَلْ إِنَّا نُبَشِّرُكَ بِغُلَٰمٍ عَلِيمٍۢ
15፥54 «እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ» አለ፡፡ قَالَ أَبَشَّرْتُمُونِى عَلَىٰٓ أَن مَّسَّنِىَ ٱلْكِبَرُ فَبِمَ تُبَشِّرُونَ
15፥55 «በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን» አሉ፡፡ قَالُوا۟ بَشَّرْنَٰكَ بِٱلْحَقِّ فَلَا تَكُن مِّنَ ٱلْقَٰنِطِينَ
51፥29 ሚስቱም እየጮኸች መጣች፥ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም። فَأَقْبَلَتِ امْرَأَتُهُ فِي صَرَّةٍ فَصَكَّتْ وَجْهَهَا وَقَالَتْ عَجُوزٌ عَقِيمٌ
11፥71 ሚስቱም የቆመች ስትኾን አትፍራ አሉት፤ ሳቀችም፡፡ በኢሥሐቅም አበሰርናት፡፡ ከኢስሐቅም በኋላ በልጁ በያዕቁብ አበሰርናት፡፡ وَٱمْرَأَتُهُۥ قَآئِمَةٌۭ فَضَحِكَتْ فَبَشَّرْنَٰهَا بِإِسْحَٰقَ وَمِن وَرَآءِ إِسْحَٰقَ يَعْقُوبَ
6.4K viewsedited  08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 16:23:01 "ምላጭ ከምሣር እጅጉን የበለጠ ስለት አለው። ነገር ግን እንጨትን ለመቁረጥ አልታደለም አይሳካለትም። ምሣርም ቢሆን የራሱ ስለትና ብርቱ ጉልበት መኖሩ ፀጉርን ለመቁረጥ አይሳካለትም"
ወንድም ዑሥማን(አቡ ማሂራህ)
https://t.me/AbuMahira55
6.7K viewsedited  13:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 07:44:55 የኢብራሂም ሣራህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

51፥29 ሚስቱም እየጮኸች መጣች፥ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም። فَأَقْبَلَتِ امْرَأَتُهُ فِي صَرَّةٍ فَصَكَّتْ وَجْهَهَا وَقَالَتْ عَجُوزٌ عَقِيمٌ

ኢብራሂም የአሏህ ነቢይ ሲሆን ሚስቱ ደግሞ ሣራህ ትባላለች፥ የኢብራሂም ሚስት ሣራህ ማንነቷ እንጂ ስሟ በቁርኣን አልተጠቀሰም። ቅሉ ግን በሐዲስ ላይ ኢብራሂም ከከለዳውያን ወደ ከነዓን በነበረው ስደት ትረካ ላይ ስሟን ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ነግረውናል፦
ቡኻርይ መጽሐፍ 51, ሐዲስ 67
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ኢብራሂም ከሣራህ ጋር ተሰደደ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ هَاجَرَ إِبْرَاهِيمُ بِسَارَةَ،

አሏህ ለተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" የኢብራሂም እንግዶች ወሬ በቁርኣን ተርኮላቸዋል፥ አምላካችን አሏህ መላእክትን ወደ ኢብራሂም በመላክ በኢሥሐቅ አበሰረው፦
51፥24 የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን? هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ ضَيْفِ إِبْرَاهِيمَ الْمُكْرَمِينَ
37፥112 በኢሥሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡ وَبَشَّرْنَاهُ بِإِسْحَاقَ نَبِيًّا مِّنَ الصَّالِحِينَ
11፥69 መልክተኞቻችንም ኢብራሂምን በልጅ ብስራት በእርግጥ መጡለት፡፡ ሰላም አሉት፡፡ ሰላም አላቸው፡፡ ጥቂትም ሳይቆይ ወዲያውኑ የተጠበሰን የወይፈን ስጋ አመጣ፡፡ وَلَقَدْ جَاءَتْ رُسُلُنَا إِبْرَاهِيمَ بِالْبُشْرَىٰ قَالُوا سَلَامًا ۖ قَالَ سَلَامٌ ۖ فَمَا لَبِثَ أَن جَاءَ بِعِجْلٍ حَنِيذٍ
51፥28 ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ፡፡ «አትፍራ» አሉት፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት፡፡ فَأَوْجَسَ مِنْهُمْ خِيفَةً ۖ قَالُوا لَا تَخَفْ ۖ وَبَشَّرُوهُ بِغُلَامٍ عَلِيمٍ

መላእክት ስለ ኢሥሐቅ ለኢብራሂም ያበሰሩትን ብስራት ሣራህ ቆማ ታዳምጥ ስለነበር፦ "መካን አሮጊት ነኝ" በማለት የማይሆን መስሏት በስላቅ ሳቀች፥ አሏህም እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ መሆኑን በመናገር አበሰራት፦
51፥29 ሚስቱም እየጮኸች መጣች፥ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም። فَأَقْبَلَتِ امْرَأَتُهُ فِي صَرَّةٍ فَصَكَّتْ وَجْهَهَا وَقَالَتْ عَجُوزٌ عَقِيمٌ
11፥71 ሚስቱም የቆመች ስትኾን ሳቀችም፡፡ በኢስሐቅ አበሰርናት፡፡ ከኢስሐቅም በኋላ በያዕቁብ አበሰርናት፡፡ وَامْرَأَتُهُ قَائِمَةٌ فَضَحِكَتْ فَبَشَّرْنَاهَا بِإِسْحَاقَ وَمِن وَرَاءِ إِسْحَاقَ يَعْقُوبَ
51፥30 ጌታሽ እንደዚህ ብሏል፦ «እነሆ እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ ነውና» አሏት፡፡ قَالُوا كَذَٰلِكِ قَالَ رَبُّكِ ۖ إِنَّهُ هُوَ الْحَكِيمُ الْعَلِيمُ

ከሳቀች በኃላ በኢሥሐቅ ስለተበሰረች ሚሽነሪዎች፦ "ከምን አንጻር እንደ ሳቀች ቅድመ ተከተሉን አልጠበቀም" በማለት ይተቻሉ፥ ቆማ የሳቀችውማ ለእርሷ ከመበሰሩ በፊት ለኢብራሂም በተበሰረው ብስራት ነው። ይህንን በተመሳሳይ ባይብል ላይ አለ፦
ዘፍጥረት 18፥9-11 እነርሱም፦ ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት? አሉት። እርሱም፦ በድንኳኑ ውስጥ ናት፡ አላቸው። እርሱም፦ የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች" አለ። ሣራም በድንኳን ደጃፍ በስተ ኋላው ሳለች ይህንን ሰማች።

ፈጣሪ በመላእክቱ ለአብርሃም ስለ ልጅ ሲነግረው ሣራ በድንኳን ደጃፍ በስተ ኋላው ሆኖ ትሰማ ነበር፥ ሣራ የሳቀችበት ልክ እንደ ቁርኣኑ፦ "ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? ጌታዬም ፈጽሞ ሸምግሎአል" በማለት ነበር፦
ዘፍጥረት 18፥12 ሣራም በራሷ፦ "ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? ጌታዬም ፈጽሞ ሸምግሎአል" ስትል ሳቀች"። וַתִּצְחַ֥ק שָׂרָ֖ה בְּקִרְבָּ֣הּ לֵאמֹ֑ר אַחֲרֵ֤י בְלֹתִי֙ הָֽיְתָה־לִּ֣י עֶדְנָ֔ה וַֽאדֹנִ֖י זָקֵֽן׃

ባይብሉ ታሪኩን ያቀረበው ሣራ የሳቀችው መላእክት ለአብርሃም ስለ ልጅ በነገሩት መሠረት እንደሆነ ሁሉ ቁርኣኑም ያስቀመጠው መላእክት ለኢብራሂም ስለ ልጅ በነገሩት መሠረት እንደሆነ በተዛማች ሙግት"textual approach" የሥነ-አፈታት ጥናት"hermeneutics" መረዳት ይቻላል፥ የተዛማች ሙግት ማለት አንዱ ሡራህ ላይ የተንጠለጠለ አሳብ በሌላ ሡራህ ላይ የሚጨርሰው ሲሆን ከቁርኣን የአነጋገር ውበት አንዱ ነው። አምላካችን አሏህ ስለዚህ እሳቦት እንዲህ ይነግረናል፦
39፥23 አላህ ከዜና ሁሉ መልካምን፣ ተመሳሳይ፣ ተደጋጋሚ የኾነን መጽሐፍ አወረደ፡፡ اللَّهُ نَزَّلَ أَحْسَنَ الْحَدِيثِ كِتَابًا مُّتَشَابِهًا مَّثَانِيَ تَقْشَعِرُّ

አሏህ ጥንት የተከናወኑትን ድርጊቶች በዜና የሚተርክልን ሙተሻቢህ በማድረግ አንዱ ሡራህ ላይ ተናግሮ ያንጠለጠለውን በሌላ ሡራህ ላይ የቀረውን ተመሳሳይ በማምጣት እና መሳኒይ በማድረግ አንዱ ሡራህ ላይ ተናግሮ ያንጠለጠለውን በሌላ ሡራህ ላይ የቀረውን በመድገም ነው፥ "ሙተሻቢህ" مُتَشَٰبِه ማለት "ተመሳሳይ" ማለት ሲሆን "መሳኒይ" مَّثَانِى ማለት "ተደጋጋሚ" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ ቀደም ብለው የተከሰቱትን ክስተቶች የሚተርክልን መልካም፣ ተመሳሳይ እና ተደጋጋሚ ዜና ለእኛ እንድንማርበት ግሳጼ እና ማስታወሻ ነው፦
11፥120 ከመልክተኞቹም ዜናዎች ሁሉንም ልብህን በእርሱ የምናረካበትን እንተርክልሃለን፡፡ በዚህችም እውነቱ ነገር ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ መጥቶልሃል፡፡ وَكُلًّا نَّقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنبَاءِ الرُّسُلِ مَا نُثَبِّتُ بِهِ فُؤَادَكَ ۚ وَجَاءَكَ فِي هَـٰذِهِ الْحَقُّ وَمَوْعِظَةٌ وَذِكْرَىٰ لِلْمُؤْمِنِينَ

"ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ መጥቶልሃል" የሚለው ይሰመርበት! ሲጀመር ቁርኣን ላይ የሚመጣ ትረካ "እከሌ እከሌን ወለደ" የሚል የቀበሌ እና የእድር መጽሐፍ አይደለም። ሲቀጥል ለነቢያችን"ﷺ" የወረደላቸው የኢብራሂም ወሬ ኩረጃ ሳይሆን የሁሉን ዓዋቂው፣ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው የአሏህ ንግግር ነው፦
33፥54 አላህ ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው። فَإِنَّ اللَّهَ كَانَ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا
25፥6 «ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው አወረደው፡፡ እርሱ መሓሪ አዛኝ ነውና» በላቸው፡፡ قُلْ أَنزَلَهُ الَّذِي يَعْلَمُ السِّرَّ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ إِنَّهُ كَانَ غَفُورًا رَّحِيمًا

ስለዚህ ከላይ ያለው የእናንተ የሚሽነሪዎች ኂስ ያልተጠና ኂስ ነው፥ ያልተጠና ኂስ የሚኃይስ ኃያሲ ለማሳለጥ ከሆነ መጥኔ ያጣ መኳተት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
9.8K views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 23:18:50 የጀነት ዛፍ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

76፥14 ዛፎችዋም በእነርሱ ላይ የቀረበች እና ፍሬዎችዋም ለለቃሚዎች መግገራትን የተገራች ስትኾን ገነትን መነዳቸው፡፡ وَدَانِيَةً عَلَيْهِمْ ظِلَالُهَا وَذُلِّلَتْ قُطُوفُهَا تَذْلِيلًا

“ጀናህ” جَنَّة የሚለው ቃል “ጀነ” جَنَّ ማለትም “ተሰወረ” ወይም “ተደበቀ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “ድብቅ” ወይም “ስውር” ማለት ነው፥ በጀነት ውስጥ ያለው ለሙሥሊሞች የተደበቀላቸውን ፀጋ ደግሞ ማንኛይቱም ነፍስ ስለማያውቅ ድብቅ እና ስውር ነው። በሐዲሰል ቁድሢይ ላይ የተዘጋጀው የጀነት ጸጋ ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ መሆኑ ተገልጿል፦
32፥17 ይሠሩትም በነበሩት ለመመንዳት ከዓይኖች መርጊያ ለእነርሱ የተደበቀላቸውን ጸጋ ማንኛይቱም ነፍስ አታውቅም፡፡ فَلَا تَعْلَمُ نَفْسٌ مَّا أُخْفِيَ لَهُم مِّن قُرَّةِ أَعْيُنٍ جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 123:
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ነብዩ”ﷺ” እንዲህ ብለው አሉ፦ “አላህም እንዲህ አለ፦ እኔ ለደጋግ ባሮቼ ዓይን ዓይቶት የማያውቅ፣ ጆሮ ሰምቶት የማያውቅ እና በሰው ልቦና ውል ብሎ የማያውቅ ጸጋን አዘጋጅቻለው”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ قَالَ اللَّهُ أَعْدَدْتُ لِعِبَادِي الصَّالِحِينَ مَا لاَ عَيْنٌ رَأَتْ، وَلاَ أُذُنٌ سَمِعَتْ، وَلاَ خَطَرَ عَلَى قَلْبِ بَشَرٍ ‏”

ስለዚህ በጀነት ውስጥ ያሉትን አሏህ ለባሮቹ ያዘጋጃቸው ፀጋዎች ዓይን ዓይቶት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ ልብ አስቦት የማያውቅ ከሆነ ጀነት ውስጥ ያለው ሙዝ፣ ዘንባባ፣ ወይን፣ ተምር እንዲሁ ዛፍ ከዱንያው ውስጥ ካለው ነገር ጋር የስም መመሳሰል እንጂ ቅርጽና ይዘቱ አሊያም ጥፍጥናውና ጣዕሙ አንድ አይደለም፦
76፥14 ዛፎችዋም በእነርሱ ላይ የቀረበች እና ፍሬዎችዋም ለለቃሚዎች መግገራትን የተገራች ስትኾን ገነትን መነዳቸው፡፡ وَدَانِيَةً عَلَيْهِمْ ظِلَالُهَا وَذُلِّلَتْ قُطُوفُهَا تَذْلِيلًا
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 53 ሐዲስ 7
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በጀናህ ውስጥ በጥላ ሥር ፈረሰኛ መቶ ዓመት የሚምታስጓዝ ዛፍ አለች"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم أَنَّهُ قَالَ ‏ "‏ إِنَّ فِي الْجَنَّةِ لَشَجَرَةً يَسِيرُ الرَّاكِبُ فِي ظِلِّهَا مِائَةَ سَنَةٍ ‏"‏ ‏.‏

ጊዜ የሚለካው በሰከንድ፣ በደቂቃ፣ በሰዓት፣ በቀን፣ በወር፣ በዓመት ሲሆን በተመሳሳይ ከሜትር ቁጥጥር ውጪ ያለ ርዝመት የሚለካው በዓመት ነው፥ በፈረሰኛ መቶ ዓመት መገለጹ በራሱ ጀናህ ምን ያክል ሰፊ እንደሆነች በቀላሉ መረዳት ይቻላል። ቀለብ እንጂ ቀልብ የሌላቸው ሚሽነሪዎች በጀናህ ውስጥ ዛፍ መኖሩ ለመሳቅ እና ለመሳለቅ ሲቃታቸው ዓይተን ነበር፥ እንዚህ ዘንጋታዎች እየተጎማለሉ እና ዘንፈል እያሉ ቁርኣን እና ሐዲስ ውስጥ እንደገቡ እኛም እንዲማሩበት በጨዋ ደንብ እና ሥርዓት ከባይብል በጀነት ውስጥ ዛፍ እንዳለ ጠቅሰንና አጣቅሰን እናቀርባለን፦
ሕዝቅኤል 31፥ 9 በእግዚአብሔርም ገነት በዔድን የነበሩ "ዛፎች" ሁሉ ቀኑበት።
ራእይ 2፥7 ድል ለነሣው በእግዚአብሔር ገነት ካለው ከሕይወት "ዛፍ" እንዲበላ እሰጠዋለሁ።
ራእይ 22፥2 በወንዙም ወዲያና ወዲህ በየወሩ እያፈራ አሥራ ሁለት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት "ዛፍ" ነበረ፥ የዛፉም ቅጠሎች ለሕዝብ መፈወሻ ነበሩ።

እነዚህ ሦስት አናቅጽ ላይ በገነት ውስጥ ዛፎች እንዳሉ አስረግጠውና ረግጠው ያስረዳሉ፥ "የሕይወት ዛፍ" ማለት አዳም እና ሔዋን በገነት እያሉ እንዲበሉት የበቀለ ዛፍ ነው፦
ዘፍጥረት 2፥9 በገነትም መካከል "የሕይወትን ዛፍ"፥ መልካምንና ክፉን የሚያስታውቀውንም ዛፍ አበቀለ።
ዘፍጥረት 2፥16 እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤

እሥልምና እንዲጠፋ ሙሥሊም እንዲገፋ ቀን ከሌሊት የሚዋትሩ እነዚህ እብሪተኞች እና ዳተኞች የሚሰበሰቡበት አዳራሽ ክበብ ይሁን ክለብ ለይተው ሳያውቁ እነዚህ አናቅጽ ያነቡአቸዋል ብለን አናስብም፥ ሚሽነሪዎች ሆይ! መቅኖ አጥታችሁ መቀመቅ ከመውረዳችሁ በፊት ጨርቄን እና ማቄን ሳትሉ ወደ ዱኑል ኢሥላም እንድትመጡ ጥሪአችን ነው። አምላካችን አሏህ ለኢሥላም ጸር እና አጽራር ከመሆን አርነት አውጥቶ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
8.9K viewsedited  20:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 21:20:03
መምህር ምሕረተ አብ፦ "ሰካራሞች የኦርቶዶክስ ተከታዮች ናቸው" የሚል ምጸታዊ ቃላት ተጠቅሟል። ይህ ነውር አይደለምን እንዴ? መምህር ተው! እንዲህ አይባል።

በነገራችን ላይ በኦርቶዶክስ ዶግማ አስካሪ መጠጥ መጠጣት ሐላል ነው፥ እነርሱ ግን አስካሪ መጠጥ ይጨልጣሉ እንጂ አይጠጡም እኮ።

ይህንን ድርጊት እንዲያወግዙ ሼር አርጉላቸው!
8.2K viewsedited  18:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 07:21:12 እነዚህ ዐረብ ጣዖታውያን "መላእክት የአሏህ ሴቶች ልጀች ናቸው" በማለት መላእክትን ሴቶች በማድረግ ለአሏህ የማይገባውን ነገር ተናገሩ፦
53፥27 እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ بِالْآخِرَةِ لَيُسَمُّونَ الْمَلَائِكَةَ تَسْمِيَةَ الْأُنثَىٰ
37፥150 ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን? أَمْ خَلَقْنَا الْمَلَائِكَةَ إِنَاثًا وَهُمْ شَاهِدُونَ
43፥19 መላእክትንም እነርሱ የአልረሕማን ባሮች የኾኑትን ሴቶች አደረጉ፡፡ ሲፈጠሩ ነበሩን? መመስከራቸው በእርግጥ ትጻፋለች፡፡ ይጠየቃሉም፡፡ وَجَعَلُوا الْمَلَائِكَةَ الَّذِينَ هُمْ عِبَادُ الرَّحْمَـٰنِ إِنَاثًا ۚ أَشَهِدُوا خَلْقَهُمْ ۚ سَتُكْتَبُ شَهَادَتُهُمْ وَيُسْأَلُونَ
17፥40 ጌታችሁ በወንዶች ልጆች መረጣችሁ እና ከመላእክት ሴቶችን ልጆች ያዝን? እናንተ ከባድን ቃል በእርግጥ ትናገራላችሁ፡፡ أَفَأَصْفَاكُمْ رَبُّكُم بِالْبَنِينَ وَاتَّخَذَ مِنَ الْمَلَائِكَةِ إِنَاثًا ۚ إِنَّكُمْ لَتَقُولُونَ قَوْلًا عَظِيمًا
16፥57 ለአላህም ከመላእክት ሴቶች ልጆችን ያደርጋሉ። ጥራት ተገባው፡፡ ለእነርሱም የሚፈልጉትን ወንዶች ልጆችን ያደርጋሉ፡፡ وَيَجْعَلُونَ لِلَّهِ الْبَنَاتِ سُبْحَانَهُ ۙ وَلَهُم مَّا يَشْتَهُونَ

ከእነርሱ አንዳቸው ግን ለአልረሕማን ምሳሌ ባደረጉለት ነገር በሴት ልጅ በተበሰረ ጊዜ የተቆጨ ኾኖ ፊቱ ጠቁሮ ይውላል፥ ነገር ግን ለአሏህ መላእክትን ሴቶች ልጆች በማድረግ በአሏህ ላይ ቀጠፉ፦
43፥16 ከሚፈጥረው ውስጥ ሴቶች ልጆችን ያዘን? በወንዶች ልጆችም እናንተን መረጣችሁን? أَمِ اتَّخَذَ مِمَّا يَخْلُقُ بَنَاتٍ وَأَصْفَاكُم بِالْبَنِينَ
52፥39 ወይስ ለእርሱ ሴቶች ልጆች አሉትን? ለእናንተም ወንዶች ልጆች አሏችሁን? أَمْ لَهُ الْبَنَاتُ وَلَكُمُ الْبَنُونَ
16፥58 አንዳቸውም በሴት ልጅ በተበሰረ ጊዜ እርሱ የተቆጨ ኾኖ ፊቱ ጠቁሮ ይውላል፡፡ وَإِذَا بُشِّرَ أَحَدُهُم بِالْأُنثَىٰ ظَلَّ وَجْهُهُ مُسْوَدًّا وَهُوَ كَظِيمٌ
43፥17 አንዳቸውም ለአልረሕማን ምሳሌ ባደረጉለት ነገር በሴት ልጅ በተበሰረ ጊዜ እርሱ በቁጭት የተመላ ኾኖ ፊቱ የጠቆረ ይኾናል፡፡ وَإِذَا بُشِّرَ أَحَدُهُم بِمَا ضَرَبَ لِلرَّحْمَـٰنِ مَثَلًا ظَلَّ وَجْهُهُ مُسْوَدًّا وَهُوَ كَظِيمٌ

እነርሱ ወንድ ልጅ ሲወለድ ለራሳቸው ደስ ሲላቸው በተቃራኒው ሴት ስትወለድ የሚከፋቸው ሲሆን ለአሏህ መላእክትን ሴቶች ልጆች ማድረጋቸው አድሏዊ ንግግር ነው፥ አሏህም፦ "ለእናንተ ወንድ ልጅ ለእርሱም ሴት ልጅ ይኖራልን? ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት" በማለት መልስ ሰጣቸው፦
53፥21 ለእናንተ ወንድ ልጅ ለእርሱም ሴት ልጅ ይኖራልን? أَلَكُمُ الذَّكَرُ وَلَهُ الْأُنثَىٰ
53፥22 ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡ تِلْكَ إِذًا قِسْمَةٌ ضِيزَىٰ

እነዚህን ጣዖታት ሙሽሪኮች እና አባቶቻቸው "ላት፣ ዑዛ እና መናህ" ብለው የሰየሟቸው ስሞች እንጂ መጥቀም ሆነ መጉዳት የሚችሉ አይደሉም፥ አሏህን ሰዎች እነዚህን ጣዖታት እንዲያመልኩ ማስረጃ አላወረደም፦
53፥23 እነርሱንም እናንተ እና አባቶቻችሁ የሰየማኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፥ አላህ በእርሷ ምንም ማስረጃ አላወረደም። إِنْ هِيَ إِلَّا أَسْمَاءٌ سَمَّيْتُمُوهَا أَنتُمْ وَآبَاؤُكُم مَّا أَنزَلَ اللَّهُ بِهَا مِن سُلْطَانٍ

"አህዋእ" أَهْوَآء ማለት "ዝንባሌ"inclination" ማለት ነው፥ ይህ ዝንባሌ ከነፍሢያህ ሲሆን አሏህን ሰዎች እነዚህን ጣዖታት እንዲያመልኩ ማስረጃ ያላወረደበትን ነገር በዝንባሌአቸው ጥርጣሬን እንዲከተሉ ሆነዋል፥ በእርግጥም ከአሏህ ዘንድ የመጣው መመሪያ ቁርኣን አሏህ አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት የመጣ ነው፦
53፥23 ነፍሶች የሚዘነበሉበትን ጥርጣሬን እንጅ ሌላ አይከተሉም፥ በእርግጥ ከጌታቸውም መምሪያ መጥቶላቸዋል። إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا الظَّنَّ وَمَا تَهْوَى الْأَنفُسُ ۖ وَلَقَدْ جَاءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ الْهُدَىٰ
45፥11 ይህ ቁርኣን መመሪያ ነው፡፡ እነዚያም በጌታቸው አንቀጾች የካዱት ለእነርሱ ከብርቱ ቅጣት የኾነ አሳማሚ ስቃይ አላቸው፡፡ هَـٰذَا هُدًى ۖ وَالَّذِينَ كَفَرُوا بِآيَاتِ رَبِّهِمْ لَهُمْ عَذَابٌ مِّن رِّجْزٍ أَلِيمٌ
14፥52 ይህ ቁርኣን ለሰዎች ገላጭ ነው፡፡ በእርሱም ሊያስጠነቅቁበት፣ እርሱም አንድ አምላክ ብቻ መኾኑን ሊያውቁበት፣ የአእምሮ ባለቤቶችም ሊገሰጹበት የተወረደ ነው፡፡ هَـٰذَا بَلَاغٌ لِّلنَّاسِ وَلِيُنذَرُوا بِهِ وَلِيَعْلَمُوا أَنَّمَا هُوَ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ وَلِيَذَّكَّرَ أُولُو الْأَلْبَابِ

አምላካችን አሏህ በተውሒድ የምንጸና ሙዋሒድ ያርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
8.4K viewsedited  04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 07:21:12 ላት፣ ዑዛ፣ መናት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

7፥180 ለአላህም መልካም ስሞች አሉት፡፡ ስትጸልዩ በእርሷም ጥሩት! እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተዋቸው፡፡ ይሠሩት የነበሩትን ነገር በእርግጥ ይመነዳሉ፡፡ وَلِلَّهِ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ فَادْعُوهُ بِهَا ۖ وَذَرُوا الَّذِينَ يُلْحِدُونَ فِي أَسْمَائِهِ ۚ سَيُجْزَوْنَ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ

አምላካችን አሏህ ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰሉ "አል-አሥ ማኡል ሑሥና" الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ ማለትም "የተዋቡ ስሞች" አሉት፦
20፥8 አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ ለእርሱ መልካሞች የኾኑ ስሞች አሉት፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ
7፥180 ለአላህም መልካም ስሞች አሉት፡፡ ስትጸልዩ በ-"እርሷም" ጥሩት! እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተዋቸው፡፡ ይሠሩት የነበሩትን ነገር በእርግጥ ይመነዳሉ፡፡ وَلِلَّهِ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ فَادْعُوهُ بِهَا ۖ وَذَرُوا الَّذِينَ يُلْحِدُونَ فِي أَسْمَائِهِ ۚ سَيُجْزَوْنَ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ

"እርሷ" ለሚለው ተሳቢ ተውላጠ ስም የገባው "ሃ" هَا ሲሆን "አሥማእ" أَسْمَاء የሚለውን ስም ተክቶ የመጣ ነው፥ ሙአነስ አንዳንዴ ጀምዕን ለማመልከት እንደሚመጣ በነሕው ደርሥ ግልጽ ነው። ነገር ግን ቁሬይሾች የአሏህ ስሞችን በማጣመም ነፍሶች የሚዘነበሉበትን ጥርጣሬ ተከትለዋል፥ "አሏህ" اللَّه ከሚለው ስም "ላት" لَّات በማለት፣ "ዐዚዝ" عَزِيزِ ከሚለው ስም "ዑዛ" عُزَّىٰ በማለት፣ "መናን" مَنَّان ከሚለው ስም "መናት" مَنَاة በማለት አጣመዋል፦
53፥19 ላትን እና ዑዛን አያችሁን? أَفَرَأَيْتُمُ اللَّاتَ وَالْعُزَّىٰ
53፥20 ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን አያችሁን? وَمَنَاةَ الثَّالِثَةَ الْأُخْرَىٰ

፨የመጀመሪያይቱ ጣዖት በግሪክ "አቴና" በሮም "ሚነርቫ" በከነዓ "አናት" በግብጽ "ኔዝ" ትባል ነበር፥ ይህቺ የጥበብ፣ የእጅ ሥራ፣ የፍትሕ፣ የሕግ፣ የድል አምላክ ተብላ የምትጠራውን ጣዖት ወደ ጧዒፍ ከተማ በወጅ ሸለቆ አምጥተው ስሟን "አሏህ" اللَّه ከሚለው ስም በማጣመም "ላት" لَّات አሏት። ላት በላይዋ ላይ የተቀረጹ ጽሑፎች ያሏ ነጭ ድንጋይ ነበረች፥ ላት ብለው በአንስታይ የሰየሟት ጣዖት ጥንት በአሏህ ቤት ሐጅ ለሚያደርጉ ሑጃጅ የገብስ ሾርባ የሚያቀርብ ሷሊሕ ሰው ሲሆን እርሱ ሲሞት እሳቤውን ከፓጋን በመውሰድ በእርሱን መቃብር ማምለክ ጀመሩ፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 380
ኢብኑ ዐባሥ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ላት እና ዑዛ" ስለሚለውን ንግግር፦ "ላት ለሐጅ ሰዎች የገብስ ሾርባ የሚያቀርብ ሰው ነበር" አለ። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، رضى الله عنهما فِي قَوْلِهِ ‏{‏اللاَّتَ وَالْعُزَّى‏}‏ كَانَ الَّلاَتُ رَجُلاً يَلُتُّ سَوِيقَ الْحَاجِّ‏.‏

ይህቺን ጣዖት በ 9 የሒጅራህ አቆጣጠር ወይም በ 630 የጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በጥቅም ወር ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" አቡ ሡፍያን ኢብኑ ሐርብን እና አል-ሙጊራህ ኢብኑ ሹዕባህን ልከዋቸው አፈራርሰዋታል።

፨ሁለተኛይቱን በከነዓን "አስታሮት" በባቢሎን "ኤሽታር" በሮም "ቬኑስ" በግሪክ "አፍሮዳይት" በግብጽ "አዞር" ትባል ነበር፥ ይህቺ የጦርነት፣ የፍቅር፣ የአደን አምላክ ተብላ የምትታመን ጣዖትን በመካህ እና በጧዒፍ መካከል ባለው በነኽላህ አምጥተው ስሟን "ዐዚዝ" عَزِيزِ ከሚለው ስም በማጣመም "ዑዛ" عُزَّىٰ አሏት። ዑዛ በመጋረጃ የተኖረች እና በመታሰቢያ ሐውልት የተለወሰች ዛፍ ነበረች፥ በ 8 የሒጅራህ አቆጣጠር ወይም በ 630 የጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በጥር ወር ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ኻሊድ ኢብኑል ወሊድን ልከውት ዑዛ የተባለችውን ጣዖት አፈራርሷል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 11, ሐዲስ 8
ሠዕድ እንደተረከው፦ ስለ ላት እና ዑዛ የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከአሏህ በቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም፥ ለእርሱ አንድም ተጋሪ የለውም"። عَنْ سَعْدٍ، قَالَ حَلَفْتُ بِاللاَّتِ وَالْعُزَّى فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ قُلْ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ وَحْدَهُ لاَ شَرِيكَ لَهُ

፨ሦስተኛይቱ በመካህ እና በመዲናህ መካከል በሚገኘው በሙሸለል አካባቢ የምትመለከው የእጣ፣ የዕድል፣ የጊዜ እና የመዳረሻ አምላክ ተብላ የምትታመነበው የነበረችው መናት ከላት እና ዑዛ በፊት የነበረች ስትሆን ስሟን "መናን" مَنَّان ከሚለው ስም በማጣመም "መናት" مَنَاة አሏት። "ሐናን" حَنَان ማለት "ርኅራኄ" ማለት ሲሆን ከአሏህ የሚሰጥ ነው፦
19፥13 ከእኛም የሆነን ርኅራኄ ንጽሕናንም ሰጠነው፡፡ ጥንቁቅም ነበር፡፡ وَحَنَانًا مِّن لَّدُنَّا وَزَكَاةً ۖ وَكَانَ تَقِيًّا

እዚህ አንቀጽ ላይ "ርኅራኄ" ለሚለው የገባው ቃል "ሐናን" حَنَان ነው። "አል-መናን" الْمَنَّان ደግሞ "ርኅራኄ ሰጪ" ማለት ሲሆን በሐዲስ የተገለጸ የአሏህ ስም ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 32
Iአነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አንድ ሰው(ጂብሪል)፦ "አሏህ ሆይ! በእውነት በጎነት ምስጋና ሁሉ ለአንተ እንዲሆን እለምንሃለው፥ ከአንተ በቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም፥ ለአንተ አንድም ተጋሪ የለህም። አንተ አል-መናን፣ የሰማያት እና የምድር አስገኚ፣ የግርማ እና የክብር ባለቤት ነህ" ሲል ሰምቻለው"። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ سَمِعَ النَّبِيُّ ـ صلى الله عليه وسلم ـ رَجُلاً يَقُولُ اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ بِأَنَّ لَكَ الْحَمْدَ لاَ إِلَهَ إِلاَّ أَنْتَ وَحْدَكَ لاَ شَرِيكَ لَكَ الْمَنَّانُ بَدِيعُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ ذُو الْجَلاَلِ وَالإِكْرَامِ"‏ ‏

በ 8 የሒጅራህ አቆጣጠር ወይም በ 630 የጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ሠዒድ ኢብኑ ዘይድ አል-አሽሀሊይን ልከውት መናህ የተባለችውን ይህቺን ጣዖት አፈራርሷል።
7.4K viewsedited  04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ