Get Mystery Box with random crypto!

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የሰርጥ አድራሻ: @wahidcom
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 34.43K
የሰርጥ መግለጫ

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 30

2022-06-27 09:37:49 የአሏህ ባሪያ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥30 ሕፃኑም አለ «እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፡፡ መጽሐፍን ሰጥቶኛል ነቢይም አድርጎኛል፡፡» قَالَ إِنِّي عَبْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَابَ وَجَعَلَنِي نَبِيًّا

"መዕቡድ" مَعْبُود‎ ማለት "ተመላኪ" ማለት ሲሆን "ዓቢድ" عَابِد‎ ማለት ደግሞ "አምላኪ" ማለት ነው፥ በተመላኪ እና በአምላኪ መካከል ያለው ሥርዓት "ዒባዳህ" عِبَادَة‎ ነው። ለአሏህ አምልኮን የሚያቀርብ "ባሪያ" በቁርኣን "ዐብድ" عَبْد ይባላል፥ ዒሣ አሏህን በብቸኝነት ስለሚያመልክ "ዐብዱሏህ" عَبْدُ اللَّه ማለትም "የአሏህ አምላኪ" "የአሏህ ባሪያ" ተብሏል፦
4፥172 አልመሲሕ ለአላህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ
19፥30 ሕፃኑም አለ «እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፡፡ መጽሐፍን ሰጥቶኛል ነቢይም አድርጎኛል፡፡» قَالَ إِنِّي عَبْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَابَ وَجَعَلَنِي نَبِيًّا
43፥59 እርሱ በርሱ ላይ የለገስንለት ለእስራኤለም ልጆች ተዓምር ያደረግነው የኾነ ባሪያ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا عَبْدٌ أَنْعَمْنَا عَلَيْهِ وَجَعَلْنَاهُ مَثَلًا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ

በዕብራይስጥ "ዔቤድ" עֶבֶד ማለት "ባሪያ" ወይም "አምላኪ" ማለት ሲሆን "ዐባድ" עָבַד ማለትም "አምልኮ" ከሚል የመጣ ቃል ነው፥ ኢየሱስ የአንዱ አምላክ ባሪያ መሆኑን በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ ተቀምጧል፦
ኢሳይያስ 42፥1 እነሆ ደግፌ የያዝሁት ባሪያዬ፤ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ምርጤ፤ በእርሱ ላይ መንፈሴን አድርጌአለሁ፥ እርሱም ለአሕዛብ ፍርድን ያወጣል። הֵ֤ן עַבְדִּי֙ אֶתְמָךְ־בֹּ֔ו בְּחִירִ֖י רָצְתָ֣ה נַפְשִׁ֑י נָתַ֤תִּי רוּחִי֙ עָלָ֔יו מִשְׁפָּ֖ט לַגֹּויִ֥ם יֹוצִֽיא׃
ማቴዎስ 12፥18 እነሆ የመረጥሁት "ባሪያዬ" ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ወዳጄ፤ መንፈሴን በእርሱ ላይ አኖራለሁ፥ ፍርድንም ያወራል። Ἰδοὺ ὁ παῖς μου ὃν ᾑρέτισα, ὁ ἀγαπητός μου ὃν εὐδόκησεν ἡ ψυχή μου· θήσω τὸ πνεῦμά μου ἐπ' αὐτόν, καὶ κρίσιν τοῖς ἔθνεσιν ἀπαγγελεῖ.

ልብ ብላችሁ ከሆነ የብሉይ ግሪክ ሰፕቱአጀንት በኢሳይያስ 42፥1 "ባሪያ" ለሚለው የተጠቀመው ቃል "ፓይስ" παῖς ሲሆን የማቴዎስ ጸሐፊም ከኢሳይያስ 42፥1 ላይ ጠቅሶ በግሪክ ኮይኔ ያስቀመጠውም ቃል "ፓይስ" παῖς ነው፥ ፈጣሪ ኢየሱስን በአገናዛቢ ተውላጠ ስም "ባሪያዬ"my servant" ማለቱ ብቻ ሳይሆን ሐዋርያትም ኢየሱስ ባርነቱ ለአንድ አምላክ ስለሆነ በአገናዛቢ ተውላጠ ስም "ባርያው"his servant" ብለው አስቀምጠዋል፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥13 የአብርሀም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ አምላክ እና የአባቶቻችን አምላክ እናንተ አሳልፋችሁ የሰጣችሁትንና ሊፈታው ቈርጦ ሳለ በጲላጦስ ፊት የካዳችሁትን "ባሪያዬውን" ኢየሱስን አከበረው። ὁ θεὸς Ἀβραὰμ καὶ Ἰσαὰκ καὶ Ἰακώβ, ὁ θεὸς τῶν πατέρων ἡμῶν, ἐδόξασεν τὸν παῖδα αὐτοῦ Ἰησοῦν, ὃν ὑμεῖς μὲν παρεδώκατε καὶ ἠρνήσασθε κατὰ πρόσωπον Πειλάτου, κρίναντος ἐκείνου ἀπολύειν·

እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሪያ" ለሚለው የገባው ቃል "ፓይዳ" Παῖδα ሥረ-መሠረቱ "ፓይስ" παῖς ሲሆን በግልጽ "ባሪያ" ማለት ስለሆነ New International Version ላይ ሳያቅማሙ "ባሪያ"servant" ብለውታል፥ ዐውዱ ላይም አምላክ ለእስራኤል ያስነሳው ነቢዩ ኢየሱስ "ፓይዳ" Παῖδα ተብሏል፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥26 ለእናንተ አስቀድሞ አምላክ "ባሪያዬውን" አስነሥቶ እያንዳንዳችሁን ከክፋታችሁ እየመለሰ ይባርካችሁ ዘንድ ላከው። ὑμῖν πρῶτον ἀναστήσας ὁ θεὸς τὸν παῖδα αὐτοῦ ἀπέστειλεν αὐτὸν εὐλογοῦντα ὑμᾶς ἐν τῷ ἀποστρέφειν ἕκαστον ἀπὸ τῶν πονηριῶν ὑμῶν.

እዚህ አንቀጽ ላይ ደግሞ ኢየሱስን በነቢይነት ያስነሳው አምላክ ተመላኪ ሲሆን ኢየሱስ ግን የተላከ ባሪያ ነው። ሚሽነሪዎች ሆይ! እናንተ "ባሪያ" መባል ያፈራችሁበትን ነቢያት እና ሐዋርያት ኢየሱስን "ባሪያ" ብለውታና ለአንዱ አምላክ ባሪያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪአችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
10.2K viewsedited  06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 08:34:23 እዚህ ድረስ ካየን ዘንዳ አምላካችን አሏህ እራሱን በቁርኣን የወሰፈበትን ወስፍ የነገረን ሲሆን የእርሱ ሲፋህ የተሰየመበት ስሞች በቁርኣን ውስጥ የተገለጹት ዘጠና ዘጠኝ ናቸው፥ ከእነዚህ ስሞች ውስጥ ታላቁ ስም ተገልጿል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 30
አል-ቃሲም እንደተረከው፦ "የአሏህ ታላቁ ስም በእርሱ በተማጸኑት ጊዜ የሚቀበልበት ነው፥ ይህም በሦስት ሡራዎች በበቀራህ፣ በአለ-ዒምራን እና በጧሀ ውስጥ ይገኛል"። عَنِ الْقَاسِمِ، قَالَ اسْمُ اللَّهِ الأَعْظَمُ الَّذِي إِذَا دُعِيَ بِهِ أَجَابَ فِي سُوَرٍ ثَلاَثٍ الْبَقَرَةِ وَآلِ عِمْرَانَ وَطَهَ ‏.‏

"አልሐይ" الْحَيّ ማለት "ሕያው"the living one" ማለት ነው፥ "አልሐይ" الْحَيّ ማለት "እንዲሆን የሚያደርግ"He Causes to Become" የሚል ትርጉምም አለው፦
18፥16 ከነገራችሁም ለእናንተ መጠቃቀሚያን ያደርግላችኋል፡፡ وَيُهَيِّئْ لَكُم مِّنْ أَمْرِكُم مِّرْفَقًا

እዚህ አንቀጽ "ያደርጋል" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ዩሐዪ" يُهَيِّئْ ሲሆን "እንዲሆን ያደረጋል" ማለት እንደሆነ ልብ አድርግ! ይህ ታላቅ ስም በሡረቱል በቀራህ፣ በሡረቱል አለ-ዒምራን እና በሡረቱ አጥ-ጧሀ ውስጥ በግልጽ ተቀምጧል፦
2፥255 አላህ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ "ሕያው" ራሱን ቻይ ነው፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ
3፥2 አላህ ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ "ሕያው" ሁሉን ነገር አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ
20፥111 ፊቶችም ሁሉ "ሕያው" አስተናባሪ ለኾነው አላህ ተዋረዱ፡፡ በደልንም የተሸከመ ሰው በእርግጥ ከሰረ፡፡ وَعَنَتِ الْوُجُوهُ لِلْحَيِّ الْقَيُّومِ ۖ وَقَدْ خَابَ مَنْ حَمَلَ ظُلْمًا
ተፍሢር ኢብኑ ከሲር 2፥255
"አቡ ኡማማህ እንደተረከው ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የአሏህ ታላቁ ስም በእርሱ በተማጸኑት ጊዜ የሚቀበልበት ነው፥ ይህም በሦስት ቦታ በሱረቱል በቀራህ፣ አለ-ዒምራን እና ጣሃ ውስጥ ይገኛል"። «اسْمُ اللهِ الْأَعْظَمُ، الَّذِي إِذَا دُعِيَ بِهِ أَجَابَ، فِي ثَلَاثٍ: سُورَةِ الْبَقَرَةِ وَآلِ عِمْرَانَ وَطه»

ዛሬ በመላው ዓለም የምንገኘው ሙሥሊሞች ጠዋት እና ማታ አያቱል ኩርሢይን ስንቀራ ይህንን ታላቅ ስም በመጥራት ጥንት ነቢያት ሲያመልኩት የነበረውን አንዱን አምላክ አሏህን ለማምለካችን በቂ ማሳያ ነው። ኢሥላም ዐቂደቱ አር-ረባንያህ ስንል አርቲ ቡርቲና ቶራ ቦራ የሆነ ስሑትና መሪር የቡና ወሬ ይዘን ሳይሆን ስሙርና ጥዑም ማስረጃ ይዘን ነው። አምላካችን አሏህ ታላቁ ስሙን በመጥራት ዱዓቸው መቅቡል ከሆኑት ያርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
9.5K viewsedited  05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 08:33:56 ታላቁ ስም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥2 አላህ ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ "ሕያው" ሁሉን ነገር አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْحَيُّ الْقَيُّومُ

በአንድ ወቅት ሙሴ አምላክን፦ "እነሆ እኔ ወደ እስራኤል ልጆች በመጣሁ ጊዜ፦ "የአባቶቻችሁ አምላክ ወደ እናንተ ላከኝ" ባልሁም ጊዜ፦ "ስሙስ ማን ነው? ባሉኝ ጊዜ፥ ምን እላቸዋለሁ? አለው፦
ዘጸአት 3፥13 ሙሴም ኤሎሂምን፦ "እነሆ እኔ ወደ እስራኤል ልጆች በመጣሁ ጊዜ፦ "የአባቶቻችሁ አምላክ ወደ እናንተ ላከኝ" ባልሁም ጊዜ፦ "ስሙስ ማን ነው? ባሉኝ ጊዜ፥ ምን እላቸዋለሁ? አለው። ויאמר משה אל־האלהים הנה אנכי בא אל־בני ישראל ואמרתי להם אלהי אבותיכם שלחני אליכם ואמרו־לי מה־שמו מה אמר אלהם׃

አምላክም ሙሴን፦ «ኤህዬህ አሼር ኤህዬህ» አለው፥ እንዲህ ለእስራኤል ልጆች፦ «ኤህዬህ» ወደ እናንተ ላከኝ" ትላለህ" አለው፦
ዘጸአት 3፥14 ኤሎሂምም ሙሴን፦ «ኤህዬህ አሼር ኤህዬህ» አለው፤ እንዲህ ለእስራኤል ልጆች፦ «ኤህዬህ» ወደ እናንተ ላከኝ ትላለህ" አለው። וַיֹּ֤אמֶר אֱלֹהִים֙ אֶל־מֹשֶׁ֔ה אֶֽהְיֶ֖ה אֲשֶׁ֣ר אֶֽהְיֶ֑ה וַיֹּ֗אמֶר כֹּ֤ה תֹאמַר֙ לִבְנֵ֣י יִשְׂרָאֵ֔ל אֶֽהְיֶ֖ה שְׁלָחַ֥נִי אֲלֵיכֶֽם׃

በዚህ ዐውድ መሠረት "ኤህዬህ" אֶֽהְיֶ֖ה የአምላክ ስም ነው፥ "ኤህዬህ" אֶֽהְיֶ֖ה ማለት "እሆናለው" "እኖራለው" "እኔ ነኝ" ማለት ነው፦
ዘጸአት 3፥12 በእውነት እኔ ከአንተ ጋር "እሆናለሁ"። וַיֹּ֙אמֶר֙ כִּֽי־אֶֽהְיֶ֣ה עִמָּ֔ךְ

እዚህ አንቀጽ ላይ "እሆናለሁ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ኤህዬህ" אֶֽהְיֶ֖ה ነው፥ "ኤህዬህ አሼር ኤህዬህ" אֶֽהְיֶ֖ה אֲשֶׁ֣ר אֶֽהְיֶ֑ה ማለት "እኔ ነኝ ማን እኔ ነኝ"I am who i am" ማለት ነው። በግዕዝ ንባባት ውስጥ "አህያ ሸራህያ" "ዘሀሎ ወይሄሉ" "እሄሉ ዘይሄሉ" "እከውን ዘእከውን" ይሉታል። በብሉይ ከተገለጹ ሌላው ስሙ "የህ" ወይም "ያህ" ነው፦
መዝሙረ ዳዊት 68፥4 ወደ ደመናዎች ለወጣም መንገድ አድርጉ! ስሙ "ያህ" ነው። סֹ֡לּוּ לָרֹכֵ֣ב בָּ֭עֲרָבֹות בְּיָ֥הּ שְׁמֹ֗ו וְעִלְז֥וּ לְפָנָֽיו׃

"ያህ" יָהּ የሚለው ስም "ያህዌህ" יְהוָ֔ה ለሚለው ስም ምጻረ-ቃል ነው፥ "ያህ" יָהּ በተለይ በሰዎች የተጸውዖ ስም ላይ በመነሻ ቅጥያ አሊያም በመድረሻ ቅጥያ ይመጣል። ለምሳሌ፦ "ኤል-ያህ" אֵלִיָּה በግዕዝ "ኤል-ያስ" በዐረቢኛ "ኢል-ያሥ" إِلْيَاس ሲሆን በመድረሻ ቅጥያ ላይ አለ፥ "ያህ-ሁ" יֵהוּא በግዕዝ "ኢዩ" በዐረቢኛ "ያ-ሁወ" يَاهُو ሲሆን በመነሻ ቅጥያ ላይ አለ። ቁርኣን ውስጥ "ያሥ" يَاس ወይም "ያ" يَّا ይህንኑ ምጻረ ቃል የሚያሳይ ነው፦
137፥123 ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡ وَإِنَّ إِلْيَاسَ لَمِنَ الْمُرْسَلِينَ
19፥2 ይህ ጌታህ ባሪያውን ዘከሪያን በችሮታው ያወሳበት ነው፡፡ ذِكْرُ رَحْمَتِ رَبِّكَ عَبْدَهُ زَكَرِيَّا

"ኢል-ያሥ" إِلْيَاس ማለት "ያህ አምላክ ነው" ማለት ሲሆን "ዘከሪ-ያ" زَكَرِيَّا ማለት ደግሞ "ያህ ያወሳው" ማለት ነው። ያህ ምጻረ-ቃል የሆነበት ስም "ቴትራግራማተን" ወይም "ቴትራግራማቶን" τετραγράμματος ይባላል፥ "ቴትራስ" τέτταρες ማለት "አራት" ማለት ሲሆን "ግራማ" γράμμα ደግሞ "ፊደል" ማለት ነው። ከቀኝ ወደ ግራ የሚነበቡ አራቱ ተነባቢ ፊደላት "ዮድ" י‎ "ሔ" ה‎ "ዋው" ו‎ "ሔ" ה ወይም "የሐዋሐ" ሲሆኑ የፈጣሪ ታላቅ ስም ነው፦
ኢሳይያስ 42፥8 እኔ ያህዌህ ነኝ፥ ስሜ ይህ ነው። אֲנִ֥י יְהוָ֖ה ה֣וּא שְׁמִ֑י
ኤርምያስ 44፥26 "እነሆ በታላቅ ስሜ ምያለሁ" ይላል ያህዌህ፡፡הִנְנִ֨י נִשְׁבַּ֜עְתִּי בִּשְׁמִ֤י הַגָּדֹול֙ אָמַ֣ר יְהוָ֔ה

"ሃሼም" השם‌‎ ማለት "ስሙ" ማለት ሲሆን ይህ ታላቅ ስም በማሶሬት ጽሑፍ ውስጥ 6,518 ቦታ ተጠቅሷል፥ ቅሉ ግን አይሁዳውያን ይህንን ታላቅ ስም በከንቱ ላለመጥራት "አዶናይ" אֲדֹנָ֥י የሚለውን ስም ይጠቀሙ ነበር። "አዶናይ" אֲדֹנָ֥י ከሚለው ቃል "አታፍ ባታህን" א "ኦላም" o "ቃሜጽ" o‌ የሚባቡትን አናባቢ ፊደላት በ "ዮድ-ሄ-ዋው-ሄ" י‎ה‎ו‎ה ላይ ሲደቅሉት "ያህዌህ" יְהוָ֔ה የሚባል ስም ተፈጠረ፥ ይህንን የተለያዩ መድብለ ዕውቀቶች ያትታሉ፦
፨"ያህዌህ፦ ባዕድ ከሆነ ድምጽ ሰጪ ፊደላት ተዋቅሮ ያህዌህ በመባል በስህተት የተነበበ ነው"። Encyclopedia international volume 9, 1974 Edition.
፨"ያህዌህ፦ የቴትራግራማቶን የተሳሳተ አነባነብ ነው"። The universal jewish encyclopedia volume 6, 1948 Edition.
፨"ያህዌህ፦ ለእስራኤል አምላክ የተሳሳተ ስም ነው"። Encyclopedia Americana volume 16, 1976 Edition.

ላቲኖቹ ደግሞ "የ" የሚለውን "ጀ" እንዲሁ "ወ" የሚለውን "ቨ" በመጠቀም "ጆሆቫህ" በማለት ይጠቀማሉ። ከመነሻው ነቢያት ሲጠቀሙበት የነበረው ዕብራይስጥ ፓሌዎ ዕብራይስጥ እንጂ ማሶሬት ዕብራይስጥ አይደለም፥ ስለዚህ በፓሌዎ ዕብራይስጥ የተቀመጠው "ዮድ-ሄ-ዋው-ሄ" 𐤉𐤄𐤅𐤄 አጠራሩ በትክክል አይታወቅም። ሆነም ቀረ "ዮድ-ሄ-ዋው-ሄ" י‎ה‎ו‎ה የሚለው ቃል "ሀ-ወ-ሀ" הוה ማለትም "ኖረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሐዋሕ" חַוָּה ማለትም "ሕያው"the living one" ማለት ነው።
8.2K viewsedited  05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 01:40:56 ማዛጋት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

24፥21 እርሱ በመጥፎ እና በሚጠላ ነገር ያዛልና፡፡ فَإِنَّهُ يَأْمُرُ بِالْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ

አምላካችን አሏህ መጥፎ ነገር እንድናደርግ አያዝም፥ ከዚያ ይልቅ በመልካም ነገር ያዛል። በተቃራኒው ከፈሕሻእ እና ከሙንከር ይከለክላል፦
7፥28 «አላህ በመጥፎ ነገር አያዝም፡፡ በአላህ ላይ የማታውቁትን ትናገራላችሁን» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّ اللَّهَ لَا يَأْمُرُ بِالْفَحْشَاءِ ۖ أَتَقُولُونَ عَلَى اللَّهِ مَا لَا تَعْلَمُونَ
16፥90 አላህ በማስተካከል፣ በማሳመርም እና ለዝምድና ባለቤት በመስጠትም ያዛል፡፡ ከመጥፎ እና ከሚጠላም ነገር ሁሉ፣ ከመበደልም ይከለክላል፡፡ إِنَّ اللَّهَ يَأْمُرُ بِالْعَدْلِ وَالْإِحْسَانِ وَإِيتَاءِ ذِي الْقُرْبَىٰ وَيَنْهَىٰ عَنِ الْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ وَالْبَغْيِ

"ፈሕሻእ" فَحْشَاء ማለት "መጥፎ" ማለት ሲሆን "ሙንከር" مُنكَر ደግሞ "የሚጠላ" ማለት ነው፥ ፈሕሻእ እና ሙንከር የሸይጧን እርምጃዎች ናቸው። ሸይጧን በፈሕሻእ እና በሙንከር ያዛልና፦
24፥21 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሰይጣንን እርምጃዎች አትከተሉ፡፡ የሰይጣንንም እርምጃዎች የሚከተል ሰው ኀጢአትን ተሸከመ፡፡ እርሱ(ሰይጣን) በመጥፎ እና በሚጠላ ነገር ያዛልና፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا تَتَّبِعُوا خُطُوَاتِ الشَّيْطَانِ ۚ وَمَن يَتَّبِعْ خُطُوَاتِ الشَّيْطَانِ فَإِنَّهُ يَأْمُرُ بِالْفَحْشَاءِ وَالْمُنكَرِ ۚ

ስለዚህ አንድ ድርጊት "ከአሏህ ነው" ማለት "ሐላል ነው" ማለት ሲሆን "ከሸይጧን ነው" ማለት ደግሞ "ሐራም ነው" ማለት ነው። እዚህ ድረስ ከተግባባን ማስነጠስ ከአሏህ ነው፥ ማዛጋት ደግሞ ግን ከሸይጧን ነው፦
ጃሚዒ አት-ተርሚዚይ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 16
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ ሲሉ አሉ፦ "ማስነጠስ ከአሏህ ነው፥ ማዛጋት ግን ከሸይጧን ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ الْعُطَاسُ مِنَ اللَّهِ وَالتَّثَاؤُبُ مِنَ الشَّيْطَانِ

"ማዛጋት ግን ከሸይጧን ነው" ማለት "ማዛጋት ሐራም ነው" ማለት ሲሆን ማዛጋት ክልክልነቱ ኢሥቲስናእ ሆኖ የመጣ ነው፥ ኢሥቲስናእ" اِسْتِثْنَاء‏ ማለት "ፍትቅታ"exceptional" ማለት ሲሆን ማዛጋት ክልክልነቱ በሶላት ውስጥ ነው፦
ጃሚዒ አት-ተርሚዚይ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 222
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ አሉ፦ "ማዛጋት በሶላት ውስጥ ከሸይጧን ነው፥ ከእናንተ አንደኛችሁ የሚያዛጋ በተቻለ መጠን ያፍነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ التَّثَاؤُبُ فِي الصَّلاَةِ مِنَ الشَّيْطَانِ فَإِذَا تَثَاءَبَ أَحَدُكُمْ فَلْيَكْظِمْ مَا اسْتَطَاعَ ‏"‏ ‏

ሶላት ክቡር እና ክቡድ ሲሆን በሶላት ውስጥ የሚረብሽ ነገር መቆጣጠር አለብን፥ ማዛጋት በማፈን የምንጎዳን የጤና እክል ስለሌለው እና በሶላት ውስጥ ማፈን ለሶላታችን ጥቅም አለው። በሶላት ውስጥ ማዛጋትን ማፈን ሲቻል ማስነጠስን ማፈን ግን ፈጽሞ ከባድ ነው፥ ማስነጠስን ማፈን ከጤና አንጻር ወደ ታምቡር ስብራት ሊያመራ ይችላል። ምክንያቱም ማስነጠስን ማፈን ኃይለኛ የአየር ፍሰት በአፍንጫው በኩል አይወጣም፣ ወደ ውጭ ያልወጡ በሽታ አምጪ ተህዋሲያን ማይክሮቦች ወደ ጆሮው ክፍል ውስጥ ይገባሉ፣ የደም ሥሮች መሰባበር እና አልፎ አልፎም ዓይነ ስውርነትን ያስከትላል። ይህ ጉዳት ስላለው በሶላት ውስጥ ማስነጠስ እና "አል-ሓምዱ ሊሏህ" ማለት ሐላል ነው፥ ዋቢ ማስረጃዎች ይመልከቱ፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 5, ሐዲስ 192
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 15, ሐዲስ 126

እንግዲህ ኢሥልምና ዱር ሙሥሊሙ ሐሩር እንዲሆን ቀን ከሌሊት ደፋ ቀና እና ጠብ እርግፍ የሚሉት አግድም አደግ ዕውቀት ያላቸው ሚሽነሪዎች በኢሥላም ላይ ለሚቀጥፉት ቅጥፈት እኛ ዐቃቢያነ እሥልምና የኢሥላምን መሠረትና ውቅር፣ ዋልታና ማገር፣ ጥልቀትና ስፋት፣ ድርና ማግ በቅጡ ተረድተን ለሚቀጥፉት ቀጣፊዎች በምንተ አፍረት ሳይሆን በምንተ እዳ እንዲህ መልስ መስጠት እና የታሪክ ምፀት ከዐሊሞቻችን ለሚቀጥለው ትውልድ የሚሆን ሰፊ ምዕላድ ትተን መሄድ ግድ ይለናል።
አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
8.2K viewsedited  22:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ