Get Mystery Box with random crypto!

የአሏህ ባሪያ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 19፥30 ሕፃኑም | ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

የአሏህ ባሪያ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥30 ሕፃኑም አለ «እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፡፡ መጽሐፍን ሰጥቶኛል ነቢይም አድርጎኛል፡፡» قَالَ إِنِّي عَبْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَابَ وَجَعَلَنِي نَبِيًّا

"መዕቡድ" مَعْبُود‎ ማለት "ተመላኪ" ማለት ሲሆን "ዓቢድ" عَابِد‎ ማለት ደግሞ "አምላኪ" ማለት ነው፥ በተመላኪ እና በአምላኪ መካከል ያለው ሥርዓት "ዒባዳህ" عِبَادَة‎ ነው። ለአሏህ አምልኮን የሚያቀርብ "ባሪያ" በቁርኣን "ዐብድ" عَبْد ይባላል፥ ዒሣ አሏህን በብቸኝነት ስለሚያመልክ "ዐብዱሏህ" عَبْدُ اللَّه ማለትም "የአሏህ አምላኪ" "የአሏህ ባሪያ" ተብሏል፦
4፥172 አልመሲሕ ለአላህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ
19፥30 ሕፃኑም አለ «እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፡፡ መጽሐፍን ሰጥቶኛል ነቢይም አድርጎኛል፡፡» قَالَ إِنِّي عَبْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَابَ وَجَعَلَنِي نَبِيًّا
43፥59 እርሱ በርሱ ላይ የለገስንለት ለእስራኤለም ልጆች ተዓምር ያደረግነው የኾነ ባሪያ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ إِنْ هُوَ إِلَّا عَبْدٌ أَنْعَمْنَا عَلَيْهِ وَجَعَلْنَاهُ مَثَلًا لِّبَنِي إِسْرَائِيلَ

በዕብራይስጥ "ዔቤድ" עֶבֶד ማለት "ባሪያ" ወይም "አምላኪ" ማለት ሲሆን "ዐባድ" עָבַד ማለትም "አምልኮ" ከሚል የመጣ ቃል ነው፥ ኢየሱስ የአንዱ አምላክ ባሪያ መሆኑን በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ ተቀምጧል፦
ኢሳይያስ 42፥1 እነሆ ደግፌ የያዝሁት ባሪያዬ፤ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ምርጤ፤ በእርሱ ላይ መንፈሴን አድርጌአለሁ፥ እርሱም ለአሕዛብ ፍርድን ያወጣል። הֵ֤ן עַבְדִּי֙ אֶתְמָךְ־בֹּ֔ו בְּחִירִ֖י רָצְתָ֣ה נַפְשִׁ֑י נָתַ֤תִּי רוּחִי֙ עָלָ֔יו מִשְׁפָּ֖ט לַגֹּויִ֥ם יֹוצִֽיא׃
ማቴዎስ 12፥18 እነሆ የመረጥሁት "ባሪያዬ" ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ወዳጄ፤ መንፈሴን በእርሱ ላይ አኖራለሁ፥ ፍርድንም ያወራል። Ἰδοὺ ὁ παῖς μου ὃν ᾑρέτισα, ὁ ἀγαπητός μου ὃν εὐδόκησεν ἡ ψυχή μου· θήσω τὸ πνεῦμά μου ἐπ' αὐτόν, καὶ κρίσιν τοῖς ἔθνεσιν ἀπαγγελεῖ.

ልብ ብላችሁ ከሆነ የብሉይ ግሪክ ሰፕቱአጀንት በኢሳይያስ 42፥1 "ባሪያ" ለሚለው የተጠቀመው ቃል "ፓይስ" παῖς ሲሆን የማቴዎስ ጸሐፊም ከኢሳይያስ 42፥1 ላይ ጠቅሶ በግሪክ ኮይኔ ያስቀመጠውም ቃል "ፓይስ" παῖς ነው፥ ፈጣሪ ኢየሱስን በአገናዛቢ ተውላጠ ስም "ባሪያዬ"my servant" ማለቱ ብቻ ሳይሆን ሐዋርያትም ኢየሱስ ባርነቱ ለአንድ አምላክ ስለሆነ በአገናዛቢ ተውላጠ ስም "ባርያው"his servant" ብለው አስቀምጠዋል፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥13 የአብርሀም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ አምላክ እና የአባቶቻችን አምላክ እናንተ አሳልፋችሁ የሰጣችሁትንና ሊፈታው ቈርጦ ሳለ በጲላጦስ ፊት የካዳችሁትን "ባሪያዬውን" ኢየሱስን አከበረው። ὁ θεὸς Ἀβραὰμ καὶ Ἰσαὰκ καὶ Ἰακώβ, ὁ θεὸς τῶν πατέρων ἡμῶν, ἐδόξασεν τὸν παῖδα αὐτοῦ Ἰησοῦν, ὃν ὑμεῖς μὲν παρεδώκατε καὶ ἠρνήσασθε κατὰ πρόσωπον Πειλάτου, κρίναντος ἐκείνου ἀπολύειν·

እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሪያ" ለሚለው የገባው ቃል "ፓይዳ" Παῖδα ሥረ-መሠረቱ "ፓይስ" παῖς ሲሆን በግልጽ "ባሪያ" ማለት ስለሆነ New International Version ላይ ሳያቅማሙ "ባሪያ"servant" ብለውታል፥ ዐውዱ ላይም አምላክ ለእስራኤል ያስነሳው ነቢዩ ኢየሱስ "ፓይዳ" Παῖδα ተብሏል፦
የሐዋርያት ሥራ 3፥26 ለእናንተ አስቀድሞ አምላክ "ባሪያዬውን" አስነሥቶ እያንዳንዳችሁን ከክፋታችሁ እየመለሰ ይባርካችሁ ዘንድ ላከው። ὑμῖν πρῶτον ἀναστήσας ὁ θεὸς τὸν παῖδα αὐτοῦ ἀπέστειλεν αὐτὸν εὐλογοῦντα ὑμᾶς ἐν τῷ ἀποστρέφειν ἕκαστον ἀπὸ τῶν πονηριῶν ὑμῶν.

እዚህ አንቀጽ ላይ ደግሞ ኢየሱስን በነቢይነት ያስነሳው አምላክ ተመላኪ ሲሆን ኢየሱስ ግን የተላከ ባሪያ ነው። ሚሽነሪዎች ሆይ! እናንተ "ባሪያ" መባል ያፈራችሁበትን ነቢያት እና ሐዋርያት ኢየሱስን "ባሪያ" ብለውታና ለአንዱ አምላክ ባሪያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪአችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም