Get Mystery Box with random crypto!

ነቢዩ ኢሥማዒል በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 19፥54 በመጽ | ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

ነቢዩ ኢሥማዒል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥54 በመጽሐፉ ኢሥማዒልን አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ መልክተኛ ነቢይም ነበር፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا

አምላካችን አሏህ ወደ ኢሥማዒል ወሕይ አውርዷል፥ አሏህ ስለ ኢሥማዒል ሲናገር "በኢሥማዒል... ላይ በተወረደው አመንን በሉ" በማለት ግህደተ-መለኮት ወርዶለት እንደነበር በሡረቱል አለ ዒምራን 3፥84 በሡረቱል በቀራህ 2፥136 እና በሡረቱ አን-ኒስሳእ 4፥163 ላይ ይናገራል። ኢሥማዒል መልክተኛ እና ነቢይ ነበር፥ ቤተሰቦቹንም በሶላት እና በዘካህ ያዝ ነበር፦
19፥54 በመጽሐፉ ኢሥማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ መልእክተኛ ነቢይም ነበር፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا
19፥55 ቤተሰቦቹንም በሶላት እና በዘካህ ያዝ ነበር፡፡ እጌታውም ዘንድ ተወዳጅ ነበር፡፡ وَكَانَ يَأْمُرُ أَهْلَهُ بِالصَّلَاةِ وَالزَّكَاةِ وَكَانَ عِندَ رَبِّهِ مَرْضِيًّا

"እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረ" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! ይህም ቀጠሮ ኢብራሂም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፤ እርሱም «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አሏህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፦
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡ فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعْىَ قَالَ يَٰبُنَىَّ إِنِّىٓ أَرَىٰ فِى ٱلْمَنَامِ أَنِّىٓ أَذْبَحُكَ فَٱنظُرْ مَاذَا تَرَىٰ ۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفْعَلْ مَا تُؤْمَرُ ۖ سَتَجِدُنِىٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ

ይህ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፥ አሏህ ኢብራሂምን ልጁን እንዲሠዋ በጠየቀው ቃላት ፈተነው፦
37፥106 ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلْبَلَٰٓؤُا۟ ٱلْمُبِينُ
2፥124 ኢብራሂምንም ጌታው በቃላት በፈተነው እና በፈጸማቸው ጊዜ አስታውስ! «እኔ ለሰዎች መሪ አድራጊህ ነኝ» አለው፡፡ «ከዘሮቼም አድርግ» አለ፡፡ ቃል ኪዳኔ በዳዮቹን አያገኝም አለው፡፡ وَإِذِ ٱبْتَلَىٰٓ إِبْرَٰهِـۧمَ رَبُّهُۥ بِكَلِمَٰتٍۢ فَأَتَمَّهُنَّ ۖ قَالَ إِنِّى جَاعِلُكَ لِلنَّاسِ إِمَامًۭا ۖ قَالَ وَمِن ذُرِّيَّتِى ۖ قَالَ لَا يَنَالُ عَهْدِى ٱلظَّٰلِمِينَ

ኢብራሂም የተፈተነበት ልጅ ኢሥማዒልን ስለመሆኑ 2፥124 እና 37፥106 ከላይ እና ከታች ዐውደ ንባቡ ያስረዳል፥ "ኢሥማዒል" إِسْمَٰعِيْل የሚለው ስም የሁለት ቃላት ውቅር ነው፥ "ኢሥም" إِسْم የሚለው ቃል "አሥመዐ" أَسْمَعَ‎ ማለት "ሰማ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ይሰማል" ማለት ነው። "ዒል" عِيْل ደግሞ "ኢላህ" إِلَـٰهً ለሚል ምጻረ-ቃል ሲሆን "አምላክ" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "ኢሥማዒል" إِسْمَٰعِيْل ማለት "አምላክ ይሰማል" ማለት ነው። ኢብራሂም፦ "ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ" ብሎ አሏህ ጠይቆ አሏህም ዱዓውን በመስማት ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅ አበሰረው፦
37፥100 ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ፡፡ رَبِّ هَبْ لِى مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
37፥101 *ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው*፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
14፥39 ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነውና፡፡ إِنَّ رَبِّي لَسَمِيعُ الدُّعَاءِ

ኢብራሂም፦ "ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነው" ማለቱ በራሱ ኢብራሂም አሏህን ለምኖ ያገኘው እና ለዕርድ ሲጠየቅ የታገሰ ትእግስተኛ ልጁ ኢሥማዒል መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል። አሏህ በልጅ ጉዳይ ኢብራሂም ያበሰረው ሁለት ጊዜ ነው፥ የመጀመሪያው ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም ሲሆን ሁለተኛው በኢሥሐቅ ነው፦
37፥101 ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
37፥112 በኢሥሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡ وَبَشَّرْنَٰهُ بِإِسْحَٰقَ نَبِيًّۭا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ

"በኢሥሐቅ-"ም" የሚለው ይሰመርበት! "ም" የሚለው ጥገኛ ምዕላድ በዐማርኛ ተጨማሪ ነገርን ያሳያል፥ "አበሰርነው" የሚለው ቃል አንድ ዐውድ ላይ ሁለቴ መምጣቱ ኢሥሐቅ እና ከላይ የተጠቀሰው በዱዓ የመጣው ልጅ ይለያያሉ። በተጨማሪም "ወ" وَ የሚለው አርፉል አጥፍ ብስራቱ ሁለት ጊዜ መሆኑን ያሳያል፥ አንደኛው ረድፍ “ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅ” ሲሆን ሁለተኛው ረድፍ “በኢሥሐቅም አበሰርነው” የሚለው ነው። ኢሥሐቅ ደግሞ ኢብራሂም አሏህን ለምኖ የተሰጠ ልጅ ሳይሆን እርሱ እና ሣራህ አንወልድም ብለው ተስፋ በቆረጡበት የተበሰሩት ልጅ ነው፦
15፥53 «አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለን» አሉት፡፡ قَالُوا۟ لَا تَوْجَلْ إِنَّا نُبَشِّرُكَ بِغُلَٰمٍ عَلِيمٍۢ
15፥54 «እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ» አለ፡፡ قَالَ أَبَشَّرْتُمُونِى عَلَىٰٓ أَن مَّسَّنِىَ ٱلْكِبَرُ فَبِمَ تُبَشِّرُونَ
15፥55 «በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን» አሉ፡፡ قَالُوا۟ بَشَّرْنَٰكَ بِٱلْحَقِّ فَلَا تَكُن مِّنَ ٱلْقَٰنِطِينَ
51፥29 ሚስቱም እየጮኸች መጣች፥ ፊቷንም መታች፡፡ «መካን አሮጊት ነኝ» አለችም። فَأَقْبَلَتِ امْرَأَتُهُ فِي صَرَّةٍ فَصَكَّتْ وَجْهَهَا وَقَالَتْ عَجُوزٌ عَقِيمٌ
11፥71 ሚስቱም የቆመች ስትኾን አትፍራ አሉት፤ ሳቀችም፡፡ በኢሥሐቅም አበሰርናት፡፡ ከኢስሐቅም በኋላ በልጁ በያዕቁብ አበሰርናት፡፡ وَٱمْرَأَتُهُۥ قَآئِمَةٌۭ فَضَحِكَتْ فَبَشَّرْنَٰهَا بِإِسْحَٰقَ وَمِن وَرَآءِ إِسْحَٰقَ يَعْقُوبَ