Get Mystery Box with random crypto!

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የሰርጥ አድራሻ: @wahidcom
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 34.43K
የሰርጥ መግለጫ

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-06-06 18:32:32 በሥመላህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

96፥1 አንብብ በዚያ ሁሉን "በ-"ፈጠረው ጌታህ ስም"፡፡ اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ

ቁርኣን ሲጀምር የሚነበበው ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም ነው፥ ከአንድ ሡራህ በስተቀር እያንዳንዱ ሡራህ ሲጀምር “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው” በሚል ነው። አንድ ሡራህ ከሌላው ሡራህ የሚለየው “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” በሚል ቃል ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 398
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ "ነቢዩ”ﷺ” ሁለት ሡራዎች አይለያዩ በመካከላቸው “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው” የሚለው ቃል ወደ እርሳቸው ቢወርድላቸው እንጂ"። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ كَانَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم لاَ يَعْرِفُ فَصْلَ السُّورَةِ حَتَّى تُنَزَّلَ عَلَيْهِ ‏{‏ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ ‏}

አምላካችን አላህ በጂብሪል ለነቢያችን”ﷺ” “ኢቅራ” اقْرَأْ ማለትም “አንብብ” ብሎ አዟቸዋል፦
18፥27 ከጌታህም መጽሐፍ ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ፡፡ وَاتْلُ مَا أُوحِيَ إِلَيْكَ مِن كِتَابِ رَبِّكَ
29፥45 ከመጽሐፍ ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ፡፡ اتْلُ مَا أُوحِيَ إِلَيْكَ مِنَ الْكِتَابِ
96፥1 አንብብ በዚያ ሁሉን "በ-"ፈጠረው ጌታህ ስም"፡፡ اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ

"አንብብ በዚያ ሁሉን "በ-"ፈጠረው ጌታህ ስም" የሚለው ይሰመርበት! "በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው" የሚለው ቃል እኛ ሁሉን "በ-"ፈጠረው ጌታህ ስም እንድናነበው የወረደው ነው፥ "በሥመላህ" بَسْمَلَة የሚለው ቃል “በሥመለ” بَسْمَلَ‎ ማለትም “ጠራ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “የአላህን ስም መጥራት” ማለት ነው። ይህም ተዝኪራህ "በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው" የሚል ነው፦
1፥1 በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيم

ሡረቱል ፋቲሓህ ሰባት አናቅጽ የያዘች እንደሆነች በቁርኣን እና በሐዲስ ተገልጿል፦
15፥87 ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትን እና ታላቁንም ቁርኣን በእርግጥ ሰጠንህ፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَاكَ سَبْعًا مِّنَ الْمَثَانِي وَالْقُرْآنَ الْعَظِيمَ
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3415
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "አል ሐምዱሊሏህ የቁርኣን "እናት"፣ የመጽሐፉ "እናት" እና ሰባት የተደጋገሙ ናት። عَنِ ابْنِ أَبِي ذِئْبٍ، عَنِ الْمَقْبُرِيِّ، عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْحَمْدُ لِلَّهِ أُمُّ الْقُرْآنِ وَأُمُّ الْكِتَابِ وَالسَّبْعُ الْمَثَانِي ‏

"ሡረቱል ፋቲሓህ ሰባት አንቀጽ ያላት በሥመላህን ጨምሮ ነው ወይስ ሳይጨምር " ለሚለው ጥያቄ መልሱ የሐፍሥ ቂርኣህ በሥመላህን የመጀመሪያው አንቀጽ አርጎ በዚህ መልኩ ያስቀምጧል፦
1፥1 "በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَـٰنِ الرَّحِيمِ
1፥2 ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው። الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ
1፥3 እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ። الرَّحْمَـٰنِ الرَّحِيمِ
1፥4 የፍርዱ ቀን ባለቤት ለኾነው፡፡ مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ
1፥5 አንተን ብቻ እናመልካለን፤ አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን፡፡ إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ
1፥6 ቀጥተኛውን መንገድ ምራን፡፡ اهْدِنَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ
1፥7 የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን፥ በእነርሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትን ሰዎች መንገድ ምራን" በሉ፡፡ صِرَاطَ الَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا الضَّالِّينَ
4.2K viewsedited  15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 14:41:17 ስለ ማርያም በጉራጊኛ ያንብቡ፦ https://t.me/wahidcomguragiga/11
6.2K views11:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 19:46:59 አጥፍቶ ጠፊ

ፕሮቴስታንት በአውሮፓ የተሸመነበት ድርና ማግ እንደሆነ ሁሉ የተዋረደበት ማቅ፣ የተገነዘበት በፍታ፣ የተከፈነበት ግምዣ ነው። አውሮፓ የካቶሊክ አገር በነበረበት ሰዓት ፕሮቴስታንት በሚሽነሪነት እና በጦርነት ተስፋፍቶ ካቶሊክን አዳክሞ ሃይማኖታዊ መንግሥት ሆኖ ነበር። ቅሉ ግን እራሱ ፕሮቴስታንት ውስጥ የኢአማኒነት ዝገት ተፈጥሮ ዛሬ አውሮፓ ከመቶ 65% በፈጣሪ የማያምን ሕዝብ ሆኗል።

ፕሮቴስታንት አጥፍቶ ጠፊ ነው። ፕሮቴስታንት በአገራችንም በኢኮኖሚ እና በፓለቲካ በልጽጎ ኦርቶዶክስን እና ሙሥሊሙን እየቦረቦረ ያለ የኢሉሚናቲ ሕዋስ ነው።

ሥልጣን ላይ ያለው የፕሮቴስታንት መንግሥት ጉልበተኛ ሆኖ በሙሥሊሙ እና በኦርቶዶክሱ የውስጥ ጉዳይ እየገባ እና ቤተ እምነትን እያፈራረሰ ሲለውም ምእመናንን እየገደለ ሕዝቡን እያስለቀሰ ነው። የተበዳይ ጸሎት ደግሞ መሬት ጠብ አይልም፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 36
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሦስት ልመናዎች ያለጥርጥር ተቀባነት አላቸው፥ እነርሱም፦ የተበዳይ ልመና፣ የመንገደኛ ልመና እና ወላጅ ለልጁ የሚያደርገው ልመና ናቸው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ ثَلاَثُ دَعَوَاتٍ يُسْتَجَابُ لَهُنَّ لاَ شَكَّ فِيهِنَّ دَعْوَةُ الْمَظْلُومِ وَدَعْوَةُ الْمُسَافِرِ وَدَعْوَةُ الْوَالِدِ لِوَلَدِهِ ‏"‏
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 48, ሐዲስ 229
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሦስት ሰዎች ልመናቸው ተመላሽ አሆንም፥ እነርሱም፦ "እስኪያፈጥር ድረስ ያለ ፆመኛ፣ ፍትሐዊ መሪ እና የተበዳይ ልመና ናቸው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ ثَلاَثَةٌ لاَ تُرَدُّ دَعْوَتُهُمُ الصَّائِمُ حَتَّى يُفْطِرَ وَالإِمَامُ الْعَادِلُ وَدَعْوَةُ الْمَظْلُومِ "‏

ይህ ፈሣድን በኢትዮጵያ ምድር የሚያስፋፋው የኢሉሚናቲ ሕዋስ በዘረኝነት እና በኢኮኖሚ ምእመናንን አዳክሞ ለማጥፋት ቆርጦ የተነሳ ነው። ነቃ እንበል!
ሙሥሊሙስ በደልን እና ጭቆናን የሚሸከምበት ጫንቃ የለውም። ከታሪክ እንደተማርነው ኢንሻላህ ይህ ሥርዓት ጉልበተኛ ሆኖ አይቀጥልም። አሏህ የተበዳዮችን እንባ የሚታበስበትን ዘመን ያምጣልን! አሚን።

ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
https://t.me/Wahidcom
9.2K viewsedited  16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-31 14:17:30 ነቢዩ ያዕቁብ በትግሪኛ ያንብቡ፦ https://t.me/wahidtigriga/22
8.1K views11:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-31 07:59:36 አሏህ አስገኚ ነው!

ክፍል ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

59፥24 እርሱ አላህ ፈጣሪው፣ አስገኚው፣ ቅርጽን አሳማሪው ነው፡፡ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት፡፡ هُوَ اللَّهُ الْخَالِقُ الْبَارِئُ الْمُصَوِّرُ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ

በዐረቢኛ "አብ" أَب ማለት "ባለቤት" በሚል ይመጣል፥ ለምሳሌ፦ የዐብዱል ሙጧሊብ ልጅ ዐብዱል ዑዛ በቁርኣን "አቢ ለሀብ" أَبِي لَهَب ተብሏል፦
111፥1 የአቡ ለሀብ ሁለት እጆች ከሰሩ፥ እርሱም ከሰረ፡፡ تَبَّتْ يَدَا أَبِي لَهَبٍ وَتَبَّ

"አቢ" أَبِي የሚለው ኢሥሙል መጅሩር "አብ" أَب የሚለውን መደብ አመላካች ነው፥ "ለሀብ" لَهَب ማለት "መንቀልቀል" ማለት ነው። "መንቀልቀል" የተባለው እሳት ጀሀነም ውስጥ ነው፦
111፥3 የመንቀልቀል ባለቤት የኾነችን እሳት በእርግጥ ይገባል፡፡ سَيَصْلَىٰ نَارًا ذَاتَ لَهَبٍ
77፥31 አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው አዝግሙ፡፡ لَّا ظَلِيلٍ وَلَا يُغْنِي مِنَ اللَّهَبِ

በጥቅሉ "አቢ ለሀብ" أَبِي لَهَب ማለት "የመንቀልቀል ባለቤት" ማለት ነው ነው፥ "አብ" أَب እዚህ ዐውድ ላይ ወላጅ "አባት" ማለት ሳይሆን "ባለቤት" ማለት ነው።
አምላካችን አሏህ አስገኚ፣ ዓለማትን የሚያስተናብር ጌታ፣ የንግሥና እና የፍርዱ ቀን ባለቤት መሆኑን በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ በቁርኣን ተቀምጧል።
በባይብል ደግሞ "አብ" אָב የሚለው የዕብራይስጥ ቃል "አስገኚ" ለሚለው ቃል ሥነ-ዘይቤአዊ አገላለጽ"analogical expression" ሆኖ መጥቷል፦
ዘዳግም 32፥6 የገዛህ አባትህ አይደለምን? የፈጠረህ እና የመሠረተህ እርሱ ነው። הֲלוֹא־ הוּא֙ אָבִ֣יךָ קָּנֶ֔ךָ ה֥וּא עָֽשְׂךָ֖ וַֽיְכֹנְנֶֽךָ׃

አንዱ አምላክ ስለ ፈጠረ እና ስለ መሠረተ "አብ" אָב መባሉ በእማሬአዊ "ወላዲ" ሳይሆን በፍካሬአዊ "አስገኚ" ማለት ነው። አምላክ "አባት" መባሉ "ባለቤት" መባልን ያሳያል፥ ለምሳሌ የዮሐንስ የማዕረግ ስም "አቡ ቀለምሲስ" ሲሆን "የራእይ ባለቤት" ማለት ሲሆን "አባ ወራ" እራሱ "ባለቤት" ማለት ነው። የዝናብ ባለቤት አምላክ ሲሆን ለዝናብ አባት ተብሏል፦
ኢዮብ 38፥28 በውኑ ለዝናብ "አባት" አለውን ወይስ የጠልን ነጠብጣብ "የወለደ" ማን ነው? הֲיֵשׁ־לַמָּטָ֥ר אָ֑ב אֹ֥ו מִי־הֹ֝ולִ֗יד אֶגְלֵי־טָֽל׃

እዚህ አንቀጽ ላይ "አባት" ተብሎ በዕብራይስጡ የገባ ቃል "አብ" אָ֑ב መሆኑን ልብ አድርግ! "አባት" ሲባል "ባለቤት" "አስገኚ" "ምንጭ" "ባለቤት" በሚል ቀመር ከተረዳን ዘንዳ የኢየሱስ "አባት" ሲባል የኢየሱስ "አስገኚ" በሚል እንረዳለን፦
ቆላስይስ 1፥3 የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አባት አምላክን ሁልጊዜ እናመሰግናለን። Εὐχαριστοῦμεν τῷ Θεῷ Πατρὶ τοῦ Κυρίου ἡμῶν Ἰησοῦ Χριστοῦ.

አንዱ አምላክ የኢየሱስ "አባት" ነው ሲባል የኢየሱስ "አስገኚ" በሚል ተቀጽሎ እንደመጣ በቀላሉ እንረዳለን። አንዱ አምላክ ሁሉንም አማንያን ስለሚያስተናብር "አንድ አባት" ተብሏል፦
ሚልክያስ 2፥10 ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን? הֲלֹ֨וא אָ֤ב אֶחָד֙ לְכֻלָּ֔נוּ הֲלֹ֛וא אֵ֥ל אֶֽחָ֖ד בְּרָאָ֑נוּ
ዮሐንስ 8፥41 አንድ አባት አለን፥ እርሱም አምላክ ነው። ἕνα Πατέρα ἔχομεν τὸν Θεόν.
ኤፌሶን 4፥6 አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ። εἷς Θεὸς καὶ Πατὴρ πάντων,

እኛ እያንዳንዳችን ወላጅ አባት አለን፥ ወላጃችንን "አባት" ብለን እንጠራለን፥ ኢየሱስ "አንዱ የሰማዩን አምላክ እንጂ "ማንንም "አባት" ብላችሁ አትጥሩ" ሲለን "አባት" የሚለው ካለመኖር ወደ መኖር ያስገኘ "አስገኚ" ብቻ አመላካች ነው፦
ማቴዎስ 23፥9 "አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና" በምድር ላይ ማንንም፦ "አባት" ብላችሁ አትጥሩ። καὶ πατέρα μὴ καλέσητε ὑμῶν ἐπὶ τῆς γῆς· εἷς γάρ ἐστιν ὑμῶν ὁ Πατὴρ ὁ οὐράνιος.

"አባት" ለአንዱ አምላክ ሲቀጸል በራሱ "አስገኚ" "አስተናባሪ" "ተንከባካቢ" ማለት እንጂ "የባሕርይ አባት" ማለት አይደለም። ለምሳሌ፦ አምላክ "እሳት" ተብሏል፦
ዕብራውያን 12፥29 አምላካችን በእውነት የሚያጠፋ "እሳት" ነው።
ዘዳግም 4፥24 አምላክህ ያህዌህ የሚበላ እሳት እና ቀናተኛ አምላክ ነው።

"እሳት" ማለት "ቁጠኛ" "ቀጪ" የሚለውን ለመግለጽ የመጣ ፍካሬአዊ አነጋገር መሆኑን ከተረዳን ዘንዳ በተመሳሳይም "አባት" ማለት "አስገኚ" "አስተናባሪ" "ተንከባካቢ" "ባለቤት" በሚል እንረዳለን። አምላክ "ድንጋይ" ተብሏል፦
ዘዳግም 32፥4 እርሱ "ዓለት" ነው። הַצּוּר֙

"ዓለት" ማለት "ድንጋይ" ማለት ነው፥ "ድንጋይ" ማለት "መሸሸጊያ" "አንባ" የሚለውን ለመግለጽ የመጣ ፍካሬአዊ አነጋገር መሆኑን ከተረዳን ዘንዳ በተመሳሳይም "አባት" ማለት "አስገኚ" "አስተናባሪ" "ተንከባካቢ" "ባለቤት" በሚል እንረዳለን።
በ 325 ድኅረ ልደት የተከናወነው የኒቂያ ጉባኤ፦ "ከአምላክ የተገኘ አምላክ" በማለት አሏህን ወላዲ መሢሑን ተወላዲ በማድረግ ለአሏህ ቁራጭን አደረጉለት፦
43፥15 ከባሮቹም ለእርሱ ቁራጭን ልጅ አደረጉለት፡፡ ሰው በእርግጥ ግልጽ ከሓዲ ነው፡፡ وَجَعَلُوا لَهُ مِنْ عِبَادِهِ جُزْءًا ۚ إِنَّ الْإِنسَانَ لَكَفُورٌ مُّبِينٌ

አሏህ አንድ ነው፥ እርሱ ከማንነቱ እና ከምንነቱ ማንንም አልወለደም። ከእርሱ ማንነት እና ምንነት የተወለደ ማንም የለም፥ ከእርሱ የተወለደ ማንም አምላክ የለም፦
112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
112፥3 አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ
23፥91 አላህ ምንም ልጅን አልወለደም፡፡ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ

“ወለድ” وَلَد የሚለው ቃል “ወለደ” وَلَدَ ማለትም “ወለደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ወልድ” ወይም “ልጅ” ማለት ነው። "ከአምላክ አካል አካልን ወስዶ እና ከባሕርይው ባሕርይን ወስዶ፥ አብን መስሎ እና አህሎ መገኘት ወይም መወለድ" የሚለውን እሳቤ ቁርኣን ስለማይቀበል ወደዚያ የሚጠጋ "አባት" የሚለውን ስያሜ ለአሏህ አይጠቀምም። እኛ ሙሥሊሞችም አንጠቀምም፥ ከዚያ ይልቅ "አብ" የሚለው ትርጉሙ "አስገኚ" ወይም "አስተናባሪ" "ተንከባካቢ" አሊያም "ባለቤት" የሚል ፍቺ ካለው በቁርኣን በግልጽ አሏህ "አስገኚ" የተባለበትን "አል ባሪእ" الْبَارِئ እና "አስተናባሪ" "ተንከባካቢ" የተባለበትን "አር ረብ" الْرَبّ እንዲሁ "ባለቤት" የሚለውን "አል ማሊክ" الْمَالِك እንጠቀማለን።
አምላካችን አሏህ በተውሒድ ሙዋሒድ አርጎ ያጽናን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
8.2K viewsedited  04:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-30 10:21:06 እዚህ አንቀጽ ላይ መካህ "ኡም" أُمّ ተብላለች፥ ወላጅ ስለሆነች ሳይሆን ለዓለማችን ማዕከት ስለሆነች ነው። እንቀጥል፦
3፥7 እርሱ ያ በአንተ ላይ መጽሐፉን ያወረደ ነው፡፡ ከእርሱ ግልጽ የኾኑ አንቀጾች አልሉ፡፡ እነሱ የመጽሐፉ "መሠረት" ነው፡፡ هُوَ الَّذِي أَنزَلَ عَلَيْكَ الْكِتَابَ مِنْهُ آيَاتٌ مُّحْكَمَاتٌ هُنَّ أُمُّ الْكِتَابِ

እዚህ አንቀጽ ላይ አያቱል ሙሕከማት "ኡም" أُمّ ተብለዋል፥ በሌላ አንቀጽ ደግሞ ለሕወል መሕፉዝ "ኡም" أُمّ ተብሏል፦
13፥39 የመጽሐፉ "መሠረት" እርሱ ዘንድ ነው፡፡ وَعِندَهُ أُمُّ الْكِتَابِ
43፥4 እርሱም በመጽሐፉ "እናት" ውስጥ እኛ ዘንድ በእርግጥ ከፍተኛ ጥበብ የተመላ ነው፡፡ وَإِنَّهُ فِي أُمِّ الْكِتَابِ لَدَيْنَا لَعَلِيٌّ حَكِيمٌ

ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ደግሞ በሐዲስ ላይ ሰባት የተደጋገሙ አናቅጽ የያዘችው ሡረቱል ፋቲሓህ "ኡም" أُمّ እንደሆነች ነግረውናል፦
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3415
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "አል ሐምዱሊሏህ የቁርኣን "እናት"፣ የመጽሐፉ "እናት" እና ሰባት የተደጋገሙ ናት። عَنِ ابْنِ أَبِي ذِئْبٍ، عَنِ الْمَقْبُرِيِّ، عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْحَمْدُ لِلَّهِ أُمُّ الْقُرْآنِ وَأُمُّ الْكِتَابِ وَالسَّبْعُ الْمَثَانِي ‏

መካህ፣ አያቱል ሙሕከማት፣ ለሕወል መሕፉዝ እና ሡረቱል ፋቲሓህ "ኡም" أُمّ የተባሉት "ማዕከል" "መሠረት" "ምንጭ" ለማለት መዕነዊይ እንጂ "ወላጅ" ለማለት ሐሣሢይ አይደለም፥ "መዕነዊይ" مَعْنَوِيّ ማለት "ፍካሬአዊ"allegorical" ማለት ሲሆን "ሐሣሢይ حَسَّاسِيّ ማለት ደግሞ "እማሬአዊ"literal" ማለት ነው።

አምላካችን አሏህ ሙሣፊርን "ኢብኑሥ ሠቢል" اِبْن السَّبِيل ይላቸዋል፥ "ኢብን" اِبْن ማለት "ልጅ" ማለት ነው፦
2፥215 ምንን ለማንም እንደሚለግሱ ይጠይቁካል፥ “ከመልካም ነገር የምትለግሱት ለወላጆች፣ ለቅርብ ዘመዶች፣ ለየቲሞችም፣ ለድሆችም እና "ለመንገደኞች" ነው” በላቸው፡፡ يَسْأَلُونَكَ مَاذَا يُنفِقُونَ ۖ قُلْ مَا أَنفَقْتُم مِّنْ خَيْرٍ فَلِلْوَالِدَيْنِ وَالْأَقْرَبِينَ وَالْيَتَامَىٰ وَالْمَسَاكِينِ وَابْنِ السَّبِيلِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "መንገደኞች" ለሚለው የገባው ቃል "ኢብኑሥ ሠቢል" اِبْن السَّبِيل ሲሆን "የመንገድ ልጅ" ማለት ነው፥ መንገደኛ በመንገድ ሥር መሆኑን ለማሳየት የመጣ መዕነዊይ እንጂ ሐሣሢይ አይደለም። "ኢብን" اِبْن ሥርወ ቃሉ "በና"بَنَى‎ ሲሆን "በና"بَنَى‎ ማለት "ገነባ" ማለት ነው፦
66፥11 «ጌታዬ ሆይ! አንተ ዘንድ በገነት ውስጥ ለእኔ ቤትን "ገንባልኝ"፡፡ ከፈርዖን እና ከሥራውም አድነኝ፡፡ ከበደለኞቹ ሕዝቦችም አድነኝ» ባለች ጊዜ፡፡ إِذْ قَالَتْ رَبِّ ابْنِ لِي عِندَكَ بَيْتًا فِي الْجَنَّةِ وَنَجِّنِي مِن فِرْعَوْنَ وَعَمَلِهِ وَنَجِّنِي مِنَ الْقَوْمِ الظَّالِمِينَ

የፈርዖን ሚስት "ገንባ" ላለችበት የገባው ግሥ "ኢብኒ" ابْنِ ነው፥ አሏህ ሰማይን እንደፈጠረ እሙን ቢሆንም "ገነባናት" ለሚለው የገባው ቃል "በነይና-ሃ" بَنَيْنَاهَا ነው፦
56፥47 ሰማይንም በኀይል ገነባናት፡፡ وَالسَّمَاءَ بَنَيْنَاهَا بِأَيْدٍ

ስለዚህ "ኢብን" اِبْن መዕነዊይ በሆነ አገላለጽ ሊመጣ ይችላል። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ በባይብል "አብ" ማለት ምን ማለት እንደሆነ በክፍል ሁለት ኢንሻላህ እንመለከታለን!

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
6.0K viewsedited  07:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-30 10:20:40 አሏህ አስገኚ ነው!

ክፍል አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

59፥24 እርሱ አላህ ፈጣሪው፣ አስገኚው፣ ቅርጽን አሳማሪው ነው፡፡ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት፡፡ هُوَ اللَّهُ الْخَالِقُ الْبَارِئُ الْمُصَوِّرُ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ

በግዕዝ "አስማት" ማለት "ስም" ለሚለው ብዜት ሲሆን "ስሞች" ግን "ስም" ለሚለው ጸያፍ ርቢ ነው፥ ይህንን በአውንታዊ ከተረዳን ዘንዳ አምላካችን አሏህ በቁርኣን የተገለጹ ዘጠና ዘጠኝ ባሕርያቱን የሚገልጹ የተዋቡ አስማት አሉት። ከስሞቹ አንዱ "አል ባሪእ" ነው፥ "አል ባሪእ" الْبَارِئ የሚለው ቃል "በረአ" بَرَأَ‎ ማለትም "ተገኘ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "አስገኚው" ማለት ነው፦
59፥24 እርሱ አላህ ፈጣሪው፣ "አስገኚው"፣ ቅርጽን አሳማሪው ነው፡፡ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት፡፡ هُوَ اللَّهُ الْخَالِقُ الْبَارِئُ الْمُصَوِّرُ ۖ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ

እዚህ አንቀጽ ላይ "አስገኚው" ለሚለው የገባው ቃል "አል ባሪእ" الْبَارِئ ነው፥ አምላካችን አሏህ ፍጥረትን ካለመኖር ወደ መኖር በማስገኘቱ "አስገኚ" ተብሏል። "ተገኚ" ደግሞ "መብሩዕ" مَبْرُوء‎ ሲሆን "ተፈጣሪ" ነው፥ አሏህ አስገኚ ሲሆን ፍጡር ደግሞ "ተገኚ" ነው። "በሪያህ" بَرِيَّة ማለት "ግኝት" ማለት ነው፦
98፥7 እነዚያ ያመኑት እና መልካሞችንም የሠሩት እነዚያ እነርሱ ከ"ፍጥረት" ሁሉ በላጭ ናቸው፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ أُولَـٰئِكَ هُمْ خَيْرُ الْبَرِيَّةِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ፍጥረት" ለሚለው የገባው ቃል "አል በሪያህ" الْبَرِيَّة ሲሆን "ግኝት" ማለት ነው።

"ረብ" رَبّ የሚለው ቃል "ረበ" رَبَّ ማለትም "ጌተ" "ተንከባከበ" "አሳደገ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ጌታ" "ተንከባካቢ" "አሳዳጊ" ማለት ነው፦
17፥24 ለሁለቱም ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው፡፡ «ጌታዬ ሆይ! በትንሽነቴ "እንዳሳደጉኝ" እዘንልላቸውም» በል፡፡ وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ وَقُل رَّبِّ ارْحَمْهُمَا كَمَا رَبَّيَانِي صَغِيرًا

እዚህ አንቀጽ ላይ "እዳሳደጉኝ" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ረበያኒ" رَبَّيَانِي ሲሆን ስንፈለቅቀው ሥርወ ቃሉ "ረበ" رَبَّ ነው፦
26፥18 ፈርዖንም አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ "አላሳደግንህምን"? በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን? قَالَ أَلَمْ نُرَبِّكَ فِينَا وَلِيدًا وَلَبِثْتَ فِينَا مِنْ عُمُرِكَ سِنِينَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ለም" لَمْ የሚለው ሐርፉን ነፍይ ሲነሳ "አሳደግንህ" ለሚለው የገባው ቃል "ኑረባከ" نُرَبِّكَ እንደሆነ ከተግባባን 17፥24 ዐውዱ ላይ በሙሰና "ለሁማ" لَهُمَا የተባሉት ወላጆች ናቸው፦
17፥23 ጌታህም እንዲህ ሲል አዘዘ፡- እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ "በወላጆቻችሁም" መልካምን ሥሩ፡፡ وَقَضَىٰ رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ وَبِالْوَالِدَيْنِ إِحْسَانًا

ወንድ ወላጅ "ዋሊድ" وَالِد ሲባል፣ ሴት ወላጅ "ዋሊዳህ" وَالِدَة ስትባት፣ ሁለቱም በሙሰና ደግሞ "ዋሊደይኒ" وَالِدَيْنِ ይባላሉ፥ ከሁለቱ የሚገኘው ልጅ ደግሞ "ወለድ" وَلَد ይባላል። ወላጆች በሌላ ተለዋዋጭ ቃል "አበዋን" أَبَوَان ይባላሉ፦
12፥100 "ወላጆቹንም" በዙፋኑ ላይ አወጣቸው፡፡ وَرَفَعَ أَبَوَيْهِ عَلَى الْعَرْشِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ወላጆቹ" ለሚለው የገባው ቃል "አበወይሂ" أَبَوَيْهِ ሲሆን መደቡ "አብ" أَب ነው፥ "ኡም" أُمّ የሚለው ቃል "አመ" أَمَّ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "እናት" ማለት ብቻ ሳይሆን "ማዕከል" "ምንጭ" "መሠረት" ማለትም ነው፦
6፥92 የከተሞችን እናት እና በዙሪያዋ ያሉትን ሰዎች ልታስጠነቅቅበት አወረድነው፡፡ وَلِتُنذِرَ أُمَّ الْقُرَىٰ وَمَنْ حَوْلَهَا
5.2K views07:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-28 09:30:00 መሥጂድ ማፍረስ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥114 የአላህንም መስጊዶች በውስጣቸው ስሙ እንዳይወሳ ከከለከለ እና እርሷንም በማበላሸት ከሮጠ ሰው ይበልጥ በዳይ ማነው? እነዚያ ፈሪዎች ኾነው እንጂ ለእነርሱ በቅርቢቱ ዓለም ውርደት አላቸው፡፡ ለእነርሱም በመጨረሻይቱ አገር ታላቅ ቅጣት አላቸው፡፡ وَمَنْ أَظْلَمُ مِمَّن مَّنَعَ مَسَاجِدَ اللَّهِ…
6.4K viewsedited  06:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-28 00:28:39 ሐበሻውያንን የሸገር ከተማ አስተዳደር በሸገር ከተማ  የአሏህ ቤት የሆኑትን መሣጂድ ማፍረሳቸው ልዩ ትርጉም አለው፥ ወደፊት ለሚመጣው "ዙ አሥ-ሡወይቀተይን" መንገድ እየጠረጉለት ነው። በምድር ላይ ያሉት መስጊዶች ሁሉ የአሏህ ብቻ ናቸው፥ በውስጣቸው ከአሏህ ጋር አንድንም አንገዛም። ስሙ በውስጧ እንዲወሳ ባዘዘው ቤቶች ውስጥ እናወድሰዋለን፥ በውስጧ በጧትና በማታ ለእርሱ እናጠራለን። መስጊዶች በውስጣቸው የአሏህ ስሙ እንዳይወሳ የሚከለክሉ እና መስጊዶች በማፈራረስ እንዳይገነባ ከሮጠ ሰው ይበልጥ በዳይ ማነው? እነዚያ ፈሪዎች ኾነው እንጂ ለእነርሱ በቅርቢቱ ዓለም ውርደት አላቸው። ለእነርሱም በመጨረሻይቱ አገር ታላቅ ቅጣት አላቸው፦
2፥114 የአላህንም መስጊዶች በውስጣቸው ስሙ እንዳይወሳ ከከለከለ እና እርሷንም በማበላሸት ከሮጠ ሰው ይበልጥ በዳይ ማነው? እነዚያ ፈሪዎች ኾነው እንጂ ለእነርሱ በቅርቢቱ ዓለም ውርደት አላቸው፡፡ ለእነርሱም በመጨረሻይቱ አገር ታላቅ ቅጣት አላቸው፡፡ وَمَنْ أَظْلَمُ مِمَّن مَّنَعَ مَسَاجِدَ اللَّهِ أَن يُذْكَرَ فِيهَا اسْمُهُ وَسَعَىٰ فِي خَرَابِهَا ۚ أُولَـٰئِكَ مَا كَانَ لَهُمْ أَن يَدْخُلُوهَا إِلَّا خَائِفِينَ ۚ لَهُمْ فِي الدُّنْيَا خِزْيٌ وَلَهُمْ فِي الْآخِرَةِ عَذَابٌ عَظِيمٌ

መሥጂድ ሲያፈራርሱ እጃችሁን አጣምራችሁ እዩ አልተባለም። ነገር ግን ለእነዚያ ለሚገደሉት ምእመናን እነርሱ የተበደሉ በመኾናቸው መጋደል ተፈቅዶልናል፦
22፥39 ለእነዚያ ለሚገደሉት ምእመናን እነርሱ የተበደሉ በመኾናቸው መጋደል ተፈቀደላቸው፡፡ አላህም እነርሱን በመርዳት ላይ በእርግጥ ቻይ ነው፡፡ أُذِنَ لِلَّذِينَ يُقَاتَلُونَ بِأَنَّهُمْ ظُلِمُوا ۚ وَإِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ نَصْرِهِمْ لَقَدِيرٌ

አንቀጹ ይቀጥልና ሲበደሉ ፍትሕ የሚያስተካክሉ አካላት ከሌሉ ገዳማት፣ ቤተክርስቲያኖች፣ ምኩራቦች እና በውስጣቸው የአሏህ ስም በብዛት የሚወሳባቸው መስጊዶች ይፈርሳሉ ይለናል፦
22፥40 ለእነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ከማለታቸው በስተቀር ያለ አግባብ ከአገራቸው የተባረሩ ለሆኑት ተፈቀደ፡፡ ”አላህ ሰዎችን ከፊላቸውን በከፊሉ መገፍተሩ ባልነበረ ኖሮ ገዳማት፣ ቤተክርስቲያኖችም፣ ምኩራቦችም እና በውስጣቸው የአላህ ስም በብዛት የሚወሳባቸው መስጊዶችም "በተፈረሱ" ነበር፡፡ አላህም ሃይማኖቱን የሚረዳውን ሰው በእርግጥ ይረዳዋል፡፡ አላህ ብርቱ አሸናፊ ነውና፡፡ الَّذِينَ أُخْرِجُوا مِن دِيَارِهِم بِغَيْرِ حَقٍّ إِلَّا أَن يَقُولُوا رَبُّنَا اللَّهُ ۗ وَلَوْلَا دَفْعُ اللَّهِ النَّاسَ بَعْضَهُم بِبَعْضٍ لَّهُدِّمَتْ صَوَامِعُ وَبِيَعٌ وَصَلَوَاتٌ وَمَسَاجِدُ يُذْكَرُ فِيهَا اسْمُ اللَّهِ كَثِيرًا ۗ وَلَيَنصُرَنَّ اللَّهُ مَن يَنصُرُهُ ۗ إِنَّ اللَّهَ لَقَوِيٌّ عَزِيزٌ

ስለዚህ ገዳማት፣ ቤተክርስቲያኖችን፣ ምኩራቦችን እና መስጊዶችን ማፍረስ ወሰን ማለፍ ነው። “አላህ ሰዎችን ከፊላቸውን በከፊሉ መገፍተሩ” የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! አንደኛው በሌላኛ ፍትሕ ለማስከበር መገፍተሩ ማለትም መጋደል ከሌለ ወሰን አላፊዎች ምድሩቱን ያበላሻሉ፦
2፥190 እነዚያንም የሚጋደሉዋችሁን በአላህ መንገድ ተጋደሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ አላህ ወሰን አላፊዎን አይወድምና፡፡ وَقَاتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ الَّذِينَ يُقَاتِلُونَكُمْ وَلَا تَعْتَدُوا ۚ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ الْمُعْتَدِينَ

"በአላህ መንገድ ተጋደሉ" የሚለው ይሰመርበት! በአሏህ መንገድ ለአሏህ ብሎ ጅሁድ ማድረግ ከዘውግ፣ ከብሔር፣ ከፓለቲካ የጸዳ እና ከስሜታዊነት የጸዳ ነው። ስለዚህ የሸገር ከተማ አስተዳደር አርፎ ካልተቀመጠ በመላው ሙሥሊም ተደራጅቶ መጋደል አለበት! ለዚህ ጅሁድ በነሲብ፣ በስሜት፣ በጭፍን ሳይሆን በሐልዮ፣ በአርምሞ፣ በነቢብ እና በገቢር ምክክር ያስፈልጋል። መሣጂድን የሚያፈርሱትን አሏህ ቡዲንያ ላይ ቅጣታቸውን ያሳየን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
8.7K viewsedited  21:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-28 00:28:39 መሥጂድ ማፍረስ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥114 የአላህንም መስጊዶች በውስጣቸው ስሙ እንዳይወሳ ከከለከለ እና እርሷንም በማበላሸት ከሮጠ ሰው ይበልጥ በዳይ ማነው? እነዚያ ፈሪዎች ኾነው እንጂ ለእነርሱ በቅርቢቱ ዓለም ውርደት አላቸው፡፡ ለእነርሱም በመጨረሻይቱ አገር ታላቅ ቅጣት አላቸው፡፡ وَمَنْ أَظْلَمُ مِمَّن مَّنَعَ مَسَاجِدَ اللَّهِ أَن يُذْكَرَ فِيهَا اسْمُهُ وَسَعَىٰ فِي خَرَابِهَا ۚ أُولَـٰئِكَ مَا كَانَ لَهُمْ أَن يَدْخُلُوهَا إِلَّا خَائِفِينَ ۚ لَهُمْ فِي الدُّنْيَا خِزْيٌ وَلَهُمْ فِي الْآخِرَةِ عَذَابٌ عَظِيمٌ

የአክሱም መንግሥት ንጉሥ ካሌብ እስከ የመን ድረስ ይገዛ ነበር፥ በጃሂሊያህ ጊዜ የካሌብ ጦር መሪ አብረሃህ አል አሽረም ነበረ። በ 570 ድኅረ ልደት "አብረሃህ አል አሽረም" أَبْرَهَة ٱلْأَشْرَم እና ጭፍሮቹ የአሏህን ቤት ለማፍረስ በዝሆን ጋልበው ወደ መካ መጡ፥ አሏህም እነዚህን የዝሆን ባለቤቶችን ተንኮል በጥፋት ውስጥ ከንቱ አደረገ፦
105፥1 በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ
105፥2 ተንኮላቸውን በጥፋት ውስጥ ከንቱ አላደረገምን? أَلَمْ يَجْعَلْ كَيْدَهُمْ فِي تَضْلِيلٍ

አምላካችን አሏህ በእነርሱም ላይ ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ ማለትም በሸክላ”brick” የሚወረውሩባቸው መንጎች የኾኑን አዕዋፍን በመላክ ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው፦
105፥3 “በእነርሱም ላይ መንጎች የኾኑን አዕዋፍን ላከ”፡፡ وَأَرْسَلَ عَلَيْهِمْ طَيْرًا أَبَابِيلَ
105፥4 “ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ የምትወረውርባቸው የኾነችን አዕዋፍ”፡፡ تَرْمِيهِم بِحِجَارَةٍ مِّن سِجِّيلٍ
105፥5 “ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው”፡፡ فَجَعَلَهُمْ كَعَصْفٍ مَّأْكُولٍ

ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ቁረይሾች ጊዜ ሲቆጥሩ እራሱ “ዓሙል ፊል” عامُ الْفِيل ማለትም “የዝሆን ዓመት” እያሉ ነበር። ታላቁን የአሏህ ቤት መሥጂድ ለማፍረስ የቋመጠው የካሌብ ጦር መሪ አብረሃህ አል አሽረም ከሐበሻህ ምድር እንደነበር ልብ አድርግ! “አሏህ” “አሏህ” የሚል ሲጠፋ እና ቁርኣን ከሰዎች ልብ ሲወሰድ ከሐበሻህ የሚመጣ ሰው ዙ አሥ-ሡወይቀተይን የአሏህን ቤት ከዕባህን ያፈርሳል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 25, ሐዲስ 82
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ከሐበሻህ የሆነ ዙ አሥ-ሡወይቀተይን ከዕባህን ያፈርሳል”። أَنَّ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ يُخَرِّبُ الْكَعْبَةَ ذُو السُّوَيْقَتَيْنِ مِنَ الْحَبَشَةِ ‏”‌‏
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 73
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ከሐበሻህ የሆነ ዙ አሥ-ሡወይቀተይን የአሏህ ዐዘ ወጀልን ቤት ያፈርሳል”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ ذُو السُّوَيْقَتَيْنِ مِنَ الْحَبَشَةِ يُخَرِّبُ بَيْتَ اللَّهِ عَزَّ وَجَلَّ ‏”‏ ‏

“ዙ አሥ-ሡወይቀተይን” ذُو السُّوَيْقَتَيْنِ ማለት “ባለ ሁለት ትንሽ ቅልጥም” ወይም “ባለ ሁለት አጭር ቅልጥም” ማለት ነው፥ በተንኮል የአሏህን ቤት አፍርሶ የከዕባን ሀብት ለማውጣት የሚፈልግ ይህ ሰው ነው።
8.1K viewsedited  21:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ