Get Mystery Box with random crypto!

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የቴሌግራም ቻናል አርማ wahidcom — ወሒድ የንጽጽር ማኅደር
የሰርጥ አድራሻ: @wahidcom
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 34.43K
የሰርጥ መግለጫ

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-18 07:29:18 ከዕባህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

105፥1 በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ

"ከዕባህ" كَعْبَة ማለት "አንኳር“cube" ማለት ሲሆን አንኳር "ምልዓት" ነው፥ ምልአት ባለ ሦስት ቅጥ ነው። ይህም ቁመት፣ ርዝምት እና ስፋት ነው፥ አምላካችን አሏህ ከዕባን የተቀደሰ ወይም የተከበረ ቤት አደረገው፦
5፥97 "ከዕባን የተከበረውን ቤት፣ ክልክል የኾነውንም ወር፣ መስዋዕቱንና ባለ ምልክቶቹንም መንጋዎች አላህ ለሰዎች መቋቋሚያ አደረገ፡፡ جَعَلَ ٱللَّهُ ٱلْكَعْبَةَ ٱلْبَيْتَ ٱلْحَرَامَ قِيَٰمًۭا لِّلنَّاسِ وَٱلشَّهْرَ ٱلْحَرَامَ وَٱلْهَدْىَ وَٱلْقَلَٰٓئِدَ
3፥96 ለሰዎች መጀመሪያ የተኖረዉ ቤት ቡሩክ እና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ ሲኾን ያ በበካህ ያለው ነው። إِنَّ أَوَّلَ بَيْتٍۢ وُضِعَ لِلنَّاسِ لَلَّذِى بِبَكَّةَ مُبَارَكًۭا وَهُدًۭى لِّلْعَٰلَمِينَ

ከዕባህ ለሰዎች መጀመሪያ የተኖረዉ ቤት ቡሩክ እና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ ሆኖ ሳለ የአክሱም መንግሥት ንጉሥ ካሌብ እስከ የመን ድረስ ይገዛ ነበር። በጃሂሊያህ ጊዜ የካሌብ ጦር መሪ አብረሃህ አል አሽረም በ 527 ድኅረ ልደት በየመን ውስጥ ከአሏህ ቤት ጋር በማፎካከር ቤተክርስቲያን አሠርቷል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 49
ጀሪር ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ “በዘመነ-ጃሂሊያ ዙል-ኸለሷህ የሚባል ቤት ነበረ፥ የቀኝ ከዕባህ ወይም የግራ ከዕባህ ተብሎ ይጠራ ነበር”። عَنْ جَرِيرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ كَانَ فِي الْجَاهِلِيَّةِ بَيْتٌ يُقَالَ لَهُ ذُو الْخَلَصَةِ، وَكَانَ يُقَالُ لَهُ الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَةُ، أَوِ الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّةُ

“ኸለሷህ” خَلَصَة ማለት “ቀሊሥ” قَلِسْ ማለት ነው፥ “ቀሊሥ” ከግሪኩ ኮይኔ “ኤክሌሲያ” εκκλεσια የመጣ ሲሆን በተለምዶ “ቤተ ክርስቲያን” ይባል እንጂ “ጉባኤ” “ማኅበር” “ተጠርተው የወጡ” ማለት ነው። ይህንን ቤት ከከዕባ ጋር ለማመሳሰል “አል ከዕበቱል የማኒያህ” الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَة ወይም “አል ከዕበቱሽ ሸእሚያህ” الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّة ብሎታል። በ 570 ድኅረ ልደት "አብረሃህ አል አሽረም" أَبْرَهَة ٱلْأَشْرَم እና ጭፍሮቹ የአሏህ ቤት ለማፍረስ በዝሆን ጋልበው ወደ መካ መጡ፥ አሏህም እነዚህን የዝሆን ባለቤቶችን ተንኮል በጥፋት ውስጥ ከንቱ አደረገ፦
105፥1 በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ
105፥2 ተንኮላቸውን በጥፋት ውስጥ ከንቱ አላደረገምን? أَلَمْ يَجْعَلْ كَيْدَهُمْ فِي تَضْلِيلٍ

አምላካችን አሏህ በእነርሱም ላይ ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ ማለትም በሸክላ”brick” የሚወረውሩባቸው መንጎች የኾኑን አዕዋፍን በመላክ ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው፦
105፥3 “በእነርሱም ላይ መንጎች የኾኑን አዕዋፍን ላከ”፡፡ وَأَرْسَلَ عَلَيْهِمْ طَيْرًا أَبَابِيلَ
105፥4 “ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ የምትወረውርባቸው የኾነችን አዕዋፍ”፡፡ تَرْمِيهِم بِحِجَارَةٍ مِّن سِجِّيلٍ
105፥5 “ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው”፡፡ فَجَعَلَهُمْ كَعَصْفٍ مَّأْكُولٍ

ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ቁረይሾች ጊዜ ሲቆጥሩ እራሱ “ዓሙል ፊል” عامُ الْفِيلِ ማለትም “የዝሆን ዓመት” እያሉ ነበር።
የአብረሃህ አል አሽረም አድራጎት ይህን ያህል ከተወገዘ ዘንዳ ከዕባን አስመስሎ ሠርቶ "ከዕባህ ነው" ማለት ከላይ እንዳየነው ዋጋ ያስከፍላል፥ የአላባ ሙሥሊሞች በቅንነት ኢሥላምን ለማስተዋወቅ ብለው የከዕባህ ቅርጽ በጊዜአዊነት መሥራታቸው ለማስተማሪያነት እንጂ በቋሚነት መሥጂድ ለማድረግ አልነበረም። ስህተታቸውን በትህትና ከማረም ይልቅ በስድብ ማጥረግረግ ጉዳዩን እንዲጦዝ እና እልክ መግባባት አርጎታል፥ ይህ ደግሞ አሏህ አደራ እንድንባባል ካዘዘን ጋር ይጋጫል፦
90፥17 ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡ ثُمَّ كَانَ مِنَ الَّذِينَ آمَنُوا وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ وَتَوَاصَوْا بِالْمَرْحَمَةِ
103፥3 እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡ إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَتَوَاصَوْا بِالْحَقِّ وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ

አንድ ሰው ሐቅ ስለያዘ ብቻ ሐቁን ለማስተላለፍ ስድብ መፍትሄ አይሆንም፥ ከዚያ ይልቅ አደራ መባባል በሐቅ ብቻ ሳይሆን በትግስት እና በማዘንም ጭምር ቢሆን የተሳሳተው ሰው ከስህተቱ ሊመለስ ዝግጁ ይሆናል። ኢሻሏህ ጠርዝ ይዘው የሚጠዛጠዙ እነዚህ ሁለቱም ጽንፎች ከዚህ ድርጊታቸው እንደሚታረሙ ተስፋ አለኝ!
አምላካችን አሏህ ለሁላችንም ሂዳያህ ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
1.3K views04:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 12:58:44 ስለዚህ ከመነሻው "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" ያለው አሏህ ሳይሆን አሏህ ተወዳጁ ነቢያችን እና ምእመናን እንዲሉ ያዘዘው ትእዛዝ ነው፥ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" ብለው የሚያምኑት ምእመናን ሆነው ሳለ አሏህ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" ብሎ እንደተናገረ አርጎ መረዳት ዓረፍተነገሩን ከዐውዱ ማፋታት ነው። "አመነ" آمَنَ እና "አመና" آمَنَّا የሚል ኃይለ ቃል ከአንቀጹ በማውጣት እና የራስን አሳብ መክተት በሥነ አፈታት ጥናት"hermeneutics" ፈቲሆት"exegesis" ሳይሆን ሰጊዎት"eisegesis" ነው።
አሏህ እኛን፦ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" "በሉ" ያለበት ምክንያት አይሁዳውያን አላህ ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ ከችሮታው ማውረዱን በምቀኝነት በመካዳቸው ነው፦
2፥90 ነፍሶቻቸውን በእርሱ የሸጡበት ነገር ከፋ! እርሱም አላህ ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ ከችሮታው ማውረዱን በመመቅኘት አላህ ባወረደው ነገር መካዳቸው ነው፡፡ بِئْسَمَا اشْتَرَوْا بِهِ أَنفُسَهُمْ أَن يَكْفُرُوا بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ بَغْيًا أَن يُنَزِّلَ اللَّهُ مِن فَضْلِهِ عَلَىٰ مَن يَشَاءُ مِنْ عِبَادِهِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ችሮታ" ለሚለው የገባ ቃል "ፈድል" فَضْل ሲሆን ሲሆን "ስጦታ" "ችሮታ" "ጸጋ"Bounty” ማለት ነው፥ ሥርወ-ቃሉ "ፈዶለ" فَضَّلَ ማለትም" ሰጠ" "ቸረ" ነው። አምላካችን አሏህ በሚያወርደው ፈድል መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አብልጧል፦
2፥253 እነዚህን መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን፡፡ تِلْكَ الرُّسُلُ فَضَّلْنَا بَعْضَهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ
17፥55 ከፊሉንም ነቢያት በከፊሉ ላይ በእርግጥ አበለጥን፡፡ وَلَقَدْ فَضَّلْنَا بَعْضَ النَّبِيِّينَ عَلَىٰ بَعْضٍ

እነዚህ አናቅጽ ላይ "አበለጥን" ለሚለው የገባ ቃል "ፈዶልና" فَضَّلْنَا መሆኑን ልብ ብለካልን? አንደ መልእክተኛ ጋር የተወረደለት ፈድል ሌላው ጋር ሰለሌለ ከፍሉ በከፊሉ ላይ ይበላለጣሉ፥ ለምሳሌ፦ አሏህ ሙሣን በቀጥታ ሲያናግር ሌላውን በመልአክ ወይም በራእይ በማናገር ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አብልጧል፦
2፥253 ከእነርሱ ውስጥ አላህ ያነጋገረው አለ፡፡ مِّنْهُم مَّن كَلَّمَ اللَّهُ
4፥164 አላህ ሙሣን ማነጋገርን አነጋገረው፡፡ وَكَلَّمَ اللَّهُ مُوسَىٰ تَكْلِيمًا

ይህ የደረጃ ልዩነት እንጂ የኑባሬ ልዩነት አይደለም። ለምሳሌ፦ አሏህ ለመርየምን ልጅ ለዒሣ ግልጽ ተአምራትን በመስጠት እና በቅዱሱ መንፈስ በማበረታታት አብልጧል፦
2፥253 ከፊሎቻቸውንም በደረጃዎች ከፍ አደረገ፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣን ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፥ በቅዱሱ መንፈስም አበረታነው፡፡ وَرَفَعَ بَعْضَهُمْ دَرَجَاتٍ ۚ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ وَأَيَّدْنَاهُ بِرُوحِ الْقُدُسِ
2፥87 የመርየምን ልጅ ዒሣን ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፡፡ በቅዱሱ መንፈስም አበረታነው፡፡ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ وَأَيَّدْنَاهُ بِرُوحِ الْقُدُسِ

ግጭት ማለት አሏህ እኛን፦ "እኩል አርጋችሁ እመኑ" ብሎን በተቃራኒው "አንዱን መልእክተኛ ከሌላው አስብልጡ" ቢለን ወይም አሏህ፦ "መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን" ብሎ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል ስንለይ እኩል አርገናል" ቢል ኖሮ ግጭት ነበር። ነገር ግን ቁርኣን የፈጣሪያችን የአሏህ ንግግር ስለሆነ እና የሰው ንግግር ስላልገባበት የእርስ በእርስ ግጭት የለውም፦
4፥82 ቁርኣንን አያስተነትኑምን? ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በእርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡ أَفَلَا يَتَدَبَّرُونَ الْقُرْآنَ ۚ وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا

"ኢኽቲላፍ" اخْتِلَاف ማለት "ግጭት" ማለት ሲሆን ቁርኣን ከአሏህ ዘንድ በግልጠተ መለኮት የመጣ የአሏህ ንግግር ስለሆነ እርስ በእርስ አይጋጭም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
2.4K views09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 12:58:06 ይጋጫልን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

4፥82 ቁርኣንን አያስተነትኑምን? ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በእርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡ أَفَلَا يَتَدَبَّرُونَ الْقُرْآنَ ۚ وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا

ጥያቄ፦
"አሏህ መልእክተኞች እኩል አድርጓል ወይስ አላደረገም?
A. እኩል አድርጓል፦
2፥285 "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّن رُّسُلِهِ

B. እኩል አላደረገም፦
2፥253 "እነዚህን መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን"፡፡ تِلْكَ الرُّسُلُ فَضَّلْنَا بَعْضَهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ

መልስ፦
ለአይሁዳውያን፦ «አላህም ባወረደው ሁሉ እመኑ» በተባሉ ጊዜ «በእኛ ላይ በተወረደው ብቻ እናምናለን» ይላሉ፥ "በእኛ ላይ በተወረደው" ለሚሉት ለነቢያት ወሕይ አረጋጋጭ የሆነው ቁርኣን በመካድ በከፊሉ በማመን እና በከፊሉ በመካድ አስተባብለዋል፦
2፥91 ለእነርሱ «አላህም ባወረደው ሁሉ እመኑ» በተባሉ ጊዜ «በእኛ ላይ በተወረደው ብቻ እናምናለን» ይላሉ፥ ከእርሱ በኋላ ያለው እርሱ ከእነርሱ ጋር ላለው አረጋጋጭ እውተኛ ሲኾን ይክዳሉ፡፡ وَإِذَا قِيلَ لَهُمْ آمِنُوا بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ قَالُوا نُؤْمِنُ بِمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا وَيَكْفُرُونَ بِمَا وَرَاءَهُ وَهُوَ الْحَقُّ مُصَدِّقًا لِّمَا مَعَهُمْ

አምላካችን አሏህ ተወዳጁ ነቢያችንን "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በእርሳቸው ላይ በተወረደው ቁርኣን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ በተወረደው ወሕይ "አመንን" እንዲሉ አዟል፦
3፥84 በል፦ "በአላህ እና በእኛ ላይ በተወረደው አመንን" قُلْ آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا
3፥84 "በኢብራሂም፣ በኢስማዒል፣ በኢስሓቅ፣ በያዕቆብ፣ በነገዶችም ላይ በተወረደው፣ ለሙሳሣ እና ለዒሣ በተሰጡት፣ በዚያም ለነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው አመንን"። وَمَا أُنزِلَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَالنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ

አምላካችን አሏህ ለዚያ ነው፦ "መልእክተኛው ከጌታው ወደ እርሱ በተወረደው አመነ" በማለት የነገረን፦
2፥285 መልእክተኛው ከጌታው ወደ እርሱ በተወረደው አመነ፡፡ آمَنَ الرَّسُولُ بِمَا أُنزِلَ إِلَيْهِ مِن رَّبِّهِ

ሌላ አንቀጽ ላይ ደግሞ አምላካችን አሏህ የተወዳጁ ነቢያችን ተከታዮች ምእመናን "ቁሉ" قُولُوا በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በእነርሱ ላይ በተወረደው ቁርኣን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ በተወረደው ወሕይ "አመንን" እንዲሉ አዟል፦
2፥136 በሉ፦ "በአላህ እና ወደ እኛ በተወረደው አመንን" قُولُوا آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ إِلَيْنَا
2፥136 ወደ ኢብራሂም፣ ወደ ኢስማዒል፣ ወደ ኢስሐቅ፣ ወደ ያዕቁብ እና ወደ ነገዶቹም በተወረደው፣ በዚያም ለሙሣ እና ለዒሣ በተሰጡት፣ በዚያም ለነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጡት አመንን"። وَمَا أُنزِلَ إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَمَا أُوتِيَ النَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ

አምላካችን አሏህ ለዚያ ነው፦ "ምእመናን እንደዚሁ አመኑ" በማለት የነገረን፦
2፥285 ምእመናን እንደዚሁ አመኑ፡፡ وَالْمُؤْمِنُونَ

"ሁሉም" ማለትም ተወዳጁ ነቢያችን እና ምእመናን «ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም» የሚሉ ሲኾኑ አመኑ፦
2፥285 ሁሉም በአላህ፣ በመላዕክቱም፣ በመጻሕፍቱም፣ በመልእክተኞቹም «ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም» የሚሉ ሲኾኑ አመኑ፡፡ كُلٌّ آمَنَ بِاللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّن رُّسُلِهِ
3፥84 "ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም" نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ
2፥136 "ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም" نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ

በሁሉም ነቢያት ላይ የተወረደው የመልእክቱ ጭብጥ ተውሒድ ስለሆነ ከእነርሱ መካከል አንድንም ሳንለይ እናምናለን፥ "ላ ኢላሀ ኢላ አና" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا የሚለው መገሰጫ ለነቢያችን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ የወረደ መገሰጫ ነው፦
21፥24 «አስረጃችሁን አምጡ፡፡ ይህ መገሰጫ እኔ ዘንድ ያለው ከእኔ በፊትም የነበረ መገሰጫ ነው» በላቸው፡፡ قُلْ هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ ۖ هَـٰذَا ذِكْرُ مَن مَّعِيَ وَذِكْرُ مَن قَبْلِي
21፥25 ከአንተ በፊትም፦ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጂ ከመልእክተኛ አንድንም አላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ

"ዚክር" ذِكْر ማለት "መገሰጫ" ማለት ሲሆን ለሁሉም መልእክተኞች የወረደውን መልእክት ተህሊል ስለሆነ አይሁዳውያን በመልእክተኞቹ መካከል ሳይለዩ ማመን ሲገባቸው በተቃራኒው በመካድ «በከፊሉም እናምናለን በከፊሉም እንክዳለን» የሚሉ እነዚያ በእውነት ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው። ለእነርሱ አዋራጅን ቅጣት አሏህ አዘጋጅቷል፦
4፥150 እነዚያ በአላህ እና በመልእክተኞቹ የሚክዱ፣ በአላህ እና በመልእክተኞቹም መካከል መለየትን የሚፈልጉ፣ «በከፊሉም እናምናለን በከፊሉም እንክዳለን» የሚሉ፣ በዚህም መካከል መንገድን ሊይዙ የሚፈልጉ እነዚያ በእውነት ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡ ለከሓዲዎችም አዋራጅን ቅጣት አዘጋጅተናል፡፡ إِنَّ الَّذِينَ يَكْفُرُونَ بِاللَّهِ وَرُسُلِهِ وَيُرِيدُونَ أَن يُفَرِّقُوا بَيْنَ اللَّهِ وَرُسُلِهِ وَيَقُولُونَ نُؤْمِنُ بِبَعْضٍ وَنَكْفُرُ بِبَعْضٍ وَيُرِيدُونَ أَن يَتَّخِذُوا بَيْنَ ذَٰلِكَ سَبِيلًا أُولَـٰئِكَ هُمُ الْكَافِرُونَ حَقًّا ۚ وَأَعْتَدْنَا لِلْكَافِرِينَ عَذَابًا مُّهِينًا
2.3K viewsedited  09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 04:50:57 በነገራችን ላይ እኛ ኢትዮጵያውያን አሳባችንን በቅንነት ከማንሸራሸር እና የሌላውን አሳብ በነጻነት ከመስማት ይልቅ ስድብ ይቀናናል። ቀጣይ ትውልድ ከእኛ ምን እንደሚማር አሏህ ይሁነን። በዚሁ ከቀጠልን መጠፋፋታችን ነው።
በተሳዳቢዎች ጦስ ሙሥሊሙን አንዱ የጽንፍ ክንፍ በዘሩ ይገለዋል፥ ሌላው የጽንፍ ክንፍ በሃይማኖቱ ይገለዋል።
አሏህ ይድረስልን! በዳዮችን የእጃቸው ይስጣቸው።
439 views01:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 04:50:44 የሰው ሸይጧን

በነገራችን ላይ በረመዷን ኩፋሩል ጂን የሆኑ ሸይጧናት ይታሰራሉ።
ቅሉ ግን የማይታሰሩ የሰው ሸይጧናት አሉ፥ "ሸይጧን" شَّيْطَان የሚለው ቃል “ሸጠነ” شَّطَنَ ማለትም “ራቀ” ወይም “ተገለለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ከአሏህ ራሕመት “የተገለለ” ወይም “የራቀ” ማለት ነው፥ ሸያጢን ከአሏህ ራሕመት የራቁ ከጂንም ከሰውም ሊሆኑ ይችላል፦
6፥112 እንደዚሁም ለነቢያት ሁሉ ከሰው እና ከጂን የኾኑን ሰይጣናት ጠላት አደረግን፡፡ وَكَذَٰلِكَ جَعَلْنَا لِكُلِّ نَبِيٍّ عَدُوًّا شَيَاطِينَ الْإِنسِ وَالْجِن
114፥6 «ከጂኒዎችም ከሰዎችም ሰይጣናት እጠበቃለሁ» በል። مِنَ الْجِنَّةِ وَالنَّاسِ
23፥97 በልም «ጌታዬ ሆ! ከሰይጣናት ጉትተጎታዎች በአንተ እጠበቃለሁ» ፡፡ وَقُل رَّبِّ أَعُوذُ بِكَ مِنْ هَمَزَاتِ الشَّيَاطِينِ

እነርሱ ስላልታሠሩ ኢሥቲዓዛህ ማድረግ ግድ ይላል። በረመዷኑ በተለይ በዚህ አሥር ቀናት ውስጥ ሥራዬ ብለው ሰው እና ሰውን በማሰዳደብ እና በማጋጨት የሚያዞላልሙ በሥራቸው ኢብሊሥ የሚቀናባቸው ይመስለኛል። ላይክ እና ኮሜንት ለመሰብሰብ የግድ ሰውን ማጋጨት እኩይ ተግባር ነውና እንታቀብ!
አሏህ ሁላችንንም ያስተካክለን! አሚን።
453 views01:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 20:52:36 "ሚስት ያለ ባሏ ፈቃድ ረመዷንን መጦም አትችልም" ተብሎ የተቀጠፈውን ቅጥፈት ድባቅ የሚያስገባ መጣጥፍ ያንብቡ፦ https://t.me/kNDk0/1041
2.3K viewsedited  17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 20:56:39 የዘካህ አወጣጥ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

2፥110 ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም ስጡ፡፡ وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ

የዘካ ገንዘብ ከተቀማጭ ላይ ከመቶ 2.5 % የሚሰጥ ነው፥ ነቢያችን”ﷺ” ከሁለት መቶ ዲርሀም 5 ዘካህ እንደሚወጣ ተናግረዋል። ያ ማለት የዘካህ ሒሳብ በመቶ ዲርሀም 2.5 ይሆናል፥ ስሌቱ 5፥2=2.5 ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 9, ሐዲስ 18 ዐሊይ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”ሁለት መቶ ዲርሀም ለአንተ በሆነች ጊዜና ዓመት ከሞላች አምስት ደራሂም ይወጣል፥ በአንተ ምንም ነገር አይሆንም ሃያ ዲናር እስኪሆን ድረስ”። عَنْ عَلِيٍّ، – رضى الله عنه – عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم بِبَعْضِ أَوَّلِ هَذَا الْحَدِيثِ قَالَ ‏”‏ فَإِذَا كَانَتْ لَكَ مِائَتَا دِرْهَمٍ وَحَالَ عَلَيْهَا الْحَوْلُ فَفِيهَا خَمْسَةُ دَرَاهِمَ وَلَيْسَ عَلَيْكَ شَىْءٌ – يَعْنِي فِي الذَّهَبِ – حَتَّى يَكُونَ لَكَ عِشْرُونَ دِينَارًا

በዚህ ሐዲስ መሠረት የአንድ ሰው ካፒታል 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ዘካህ ይወጅበታል። በሸሪዓህ የዘካህ አነስተኛ የክፍያ መጠን “ኒሷብ” نِصاب ይባላል፥ ይህም ኒሷብ የሚለካው 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ነው። “ዲናር” دِينَار‎ ማለት “የወርቅ ሳንቲም”gold coin” ማለት ሲሆን “ዲርሀም” دِرْهَم‎ ማለት ደግሞ “የብር ሳንቲም”silver coin” ማለት ነው። ይህ በጥንት ጊዜ የሸቀጥ ገንዘብ”commodity money” ነው። “ዲናር” እና “ዲርሀም” የሚለኩት በሚስቃል ነው፥ “ሚስቃል” مِثْقَال የሚለው ቃል “ሰቀለ” ثَقَلَ ማለትም “ከበደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ክብደት” ማለት ነው።
1 ሚስቃል ወርቅ 4.25 ግራም ነው፥ 20 ሚስቃል ወርቅ ደግሞ 4,25x 20 = 85 ግራም ወርቅ ይሆናል ማለት ነው።
1 ሚስቃል ብር 2.975 ግራም ነው፥ 200 ሚስቃል ብር ደግሞ 2.975x 200= 595 ግራም ብር ይሆናል ማለት ነው።

በዘካህ ላይ የሚወጅበው ኒሷብ 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ነው።
አንድ ሙሥሊም ያስቀመጠው ካፒታል ዓመት ከሞላው እና ያም ካፒታል 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ያክል ከሆነ ዘካህ ማውጣት ግዴታው ነው።
ዘካቱል ማል የሚወጣበት አነስተኛ ዋጋ የብር ኒሷብ ስለሆነ አብላጫው ምሁራን የብር ኒሷብን መሠረት ባደረገ መልኩ ከዚያ እንዲወጣ ፈትዋ ሰተዋል፥ ስለዚህ አንድ ሰው ዓመት የተቀመጠ 89,250 ብር(ገንዘብ) እና ከዛ በላይ ካለው ዘካህ ማውጣት ግዴታ አለበት።

እንዴት? ካላችሁ የብር ኒሷብ ወደ ወረቀት ገንዘብ”Fiat money” ለመቀየር ብርን ዛሬ ባለው የወቅቱ ግብይት ለናሙና ያክል መሥራት ይቻላል። በኢትዮጵያ አንድ ግራም ብር"silver" አሁን ባለኝ መረጃ 150 ብር"ገንዘብ" ነው፥ ስናሰላው 150×595= 89,250 ብር(ገንዘብ) ይሆናል።
ለምሳሌ፦ እኔ 100 ሺህ ብር ቢኖረኝ ከ 100 ሺህ ብር ላይ 2.5 % ዘካህ ሲሰላ 2,500 ይወጅብብኛል፥ ስናሰላው 100,000×2.5፥100= 2,500 ይሆናል።
ዘካህን መስጠት አንርሳ፦
2፥110 ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም ስጡ፡፡ وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ

አምላካችን አሏህ ዘካን ከሚሰጡ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
2.1K views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 17:33:53 ኢፍጣር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

33፥35 "ጦመኛ ወንዶች እና ጦመኛ ሴቶችም፣ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶች እና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶች እና አውሺዎች ሴቶችም አላህ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል"፡፡ وَالصَّائِمِينَ وَالصَّائِمَاتِ وَالْحَافِظِينَ فُرُوجَهُمْ وَالْحَافِظَاتِ وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا

“ፊጥር” فِطْر የሚለው ቃል "ፈጦረ" فَطَرَ ማለትም "ገደፈ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ጦም መግደፊያ" ማለት ነው፥ የፊጥር ብዙ ቁጥር ደግሞ “ፉጡር” فُطُور ነው። ለምሳሌ፦ የረመዷን ጦም ማብቂያ በዓል እራሱ "ዒዱል ፊጥር" عِيدُ ٱلْفِطْر ይባላል፥ "ዘካቱል ፊጥር" زَكَاة الفِطْر ደግሞ ለመሣኪን በዒዱል ፊጥር ቀን ለማስፈጠሪያነት የሚውል ገንዘብ ነው። በተመሳሳይ “ኢፍጣር” إِفْطَار የሚለው ቃል "አፍጦረ" أَفْطَرَ ማለትም "አፈጠረ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ጦም መግደፍ" ማለት ነው፥ ጦመኛን ያስፈጠረ ጦመኛው ከሚያገኘውን ምንዳ ምንም ሳይቀነስ ጦመኛው ሊያገኘው የሚችለውን ምንዳ ያገኛል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 109
ዘይድ ኢብኑ ኻሊድ አል ጁሀኒይ እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጦመኛን ያስፈጠረ ጦመኛው ከሚያገኘውን ምንዳ ምንም ሳይቀነስ ጦመኛው ሊያገኘው የሚችለውን ምንዳ ያገኛል"። عَنْ زَيْدِ بْنِ خَالِدٍ الْجُهَنِيِّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ مَنْ فَطَّرَ صَائِمًا كَانَ لَهُ مِثْلُ أَجْرِهِمْ مِنْ غَيْرِ أَنْ يَنْقُصَ مِنْ أُجُورِهِمْ شَيْئًا ‏"‏ ‏.‏

አደባባይ ላይ እዩልኝ እና ስሙልኝ በማለት ከመበሻሸቅ፣ ከመነታረክ፣ እልህ ከመገባባት፣ ከመፎካከር ይልቅ ከወለጋ ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን በካምፕ ውስጥ ያሉትን የወሎ ሙሥሊሞችን ማስፈጠር አንርሳ! እነዚህ ተፈናቃዮች ዱንያህ ላይ ተስፋ ቆርጠው አኺራቸውን በመጠባበቅ ላይ በሞት እና በሕይወት መካከል ያሉ የሊላሂ ወንድሞቻችን እና እኅቶቻችን ናቸው። እውነት ለአሏህ ከተባለ እነዚህን ስደተኞች ባለን አቅም መጎብኘቱ እውነተኛ አጅር አለው። አሏህ ይቀበላችሁ!

አምላካችን አሏህ ጦመኛ ወንድ ባሪያውን "ሷኢም" صَّائِم ሲለው ጦመኛ ሴት ባሪያውን ደግሞ "ሷኢማህ" صَّائِمَة ይላታል፥ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል፦
33፥35 "ጦመኛ ወንዶች እና ጦመኛ ሴቶችም፣ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶች እና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶች እና አውሺዎች ሴቶችም አላህ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል"፡፡ وَالصَّائِمِينَ وَالصَّائِمَاتِ وَالْحَافِظِينَ فُرُوجَهُمْ وَالْحَافِظَاتِ وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا

አሏህ "ሷኢሚን" صَّآئِمِين እና "ሷኢማት" صَّآئِمَٰت ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
1.9K views14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 09:56:57 "ብጤ" ለሚለው የገባው ቃል "ኩፉው" كُفُو ሲሆን "አቻ" "እኩያ" "ወደር" ማለት ነው፥ለአሏህ አንድም "አቻ" "እኩያ" "ወደር" የለውም። "አንድም" ለሚለው ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን "ሸኽስ" شَخْص በሚል የመጣ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 67, ሐዲስ 153
ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ " "ከአላህ የበለጠ የሚቀና "አንድም" የለም"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ مَا مِنْ أَحَدٍ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ،
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 44
ዐብዱል ማሊክ እንደተናገረው፦ "ከአላህ የበለጠ የሚቀና "ማንነት" የለም። عَنْ عَبْدِ الْمَلِكِ ‏"‏ لاَ شَخْصَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ ‏"‌‏.‏

"አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን "ማንነት" ለሚለው የገባው ቃል "ሸኽስ" شَخْص ነው፥ ስለዚህ አሏህ በማንነቱ አንድ ነው። ባል በሚስቱ እንዲሁ ንጉሥ በመንግሥቱ እንደሚቀና የፈጠረን አንድ አምላክ በአምልኮቱ ይቀናል፦
ዘጸአት 20፥6 እኔ ያህዌህ አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና።

ገለቴ ከመንጨርጨር እና ከመንተክተክ ይልቅ መቅናት አውታዊ እንደሆነ ከራስህ መጽሐፍ ተረዳ! ስለዚህ አሏህ በአምልኮቱ መቅናቱ ላይ እርር እና ምርር አትበል። አሏህ፦ "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በአምልኮው እንዳናጋራ በአጽንዖት እና በአንክሮት ነግሮናል፦
18፥110 "በጌታውም አምልኮ አንድንም አያጋራ"። وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا

"አንድንም" ሲል በአሏህ አምልኮ "አንድንም ማንነት" ማጋራት እንደሌለብን ያሳያል፥ አምልኮ የአሏህ ሐቅ እና ገንዘብ ብቻ ነው።
ተወዳጁ ነቢያች"ﷺ" አንድ ማንነት ስለነበሩ በቁርኣን "አሐድ" በሐዲስ "ሸኽስ" شَخْص ተብለዋል፦
54፥24 «ከእኛ የኾነን "አንድን" ሰው እንከተለዋለን? እኛ ያን ጊዜ በስህተትና በዕብደት ውስጥ ነን» አሉ፡፡ فَقَالُوا أَبَشَرًا مِّنَّا وَاحِدًا نَّتَّبِعُهُ إِنَّا إِذًا لَّفِي ضَلَالٍ وَسُعُرٍ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 24
አነሥ እንደተረከው፦ "በእነርሱ ዘንድ ከአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" የበለጠ ተወዳጅ "ማንነት" አልነበረም"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ لَمْ يَكُنْ شَخْصٌ أَحَبَّ إِلَيْهِمْ مِنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم

መቼም ነቢያች"ﷺ" አንድ ማንነት ብቻ ነበሩ እንጂ ሥላሴ አልነበሩም። ሌላው ተሰምሮ ሊጤንበት የሚገባው ነጥብ "አለዚ" اَلَّذِي ኢሥሙል መውሱል ሲሆን ሙፍረድ ለሆነ ማንነት የምንጠቀምበት ነው፥ ከአንድ በላይ ለሆኑ ማንነቶች የምንጠቀምበት በሙሰና "አለዘይኒ" اَللَّذَيْنِ በጀምዕ "አለዚነ" اَلَّذِينَ ነው። አሏህ አንድ ማንነት ስለሆነ "አለዚ" اَلَّذِي ብቻ ተብሏል፦
7፥54 ጌታችሁ "ያ" ሰማያትን እና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ إِنَّ رَبَّكُمُ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ

"ያ" ለሚለው አንጻራዊ ተውላጠ ስም የገባው "አለዚ" اَلَّذِي እንደሆነ አስምርበት! ይህንን የሰዋስው ሙግት አፍጦና አፋጦ፤ አግጦና አንጋጦ ስታነቡ ቆሌ ተገፎ እና ቆሽት አሮ፦ "ሰማይ ተንዶ ሊናጫነኝ ነው፥ ምድር ተከፍቶ ሊውጠኝ ነው" ከምትሉ አውንታዊ መረዳት ይዛችሁ ልባችሁን ብትከፍቱ መልካም ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
1.5K viewsedited  06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 09:56:33 አሏህ አንድ ነው!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

12፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው»። قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ

"አሏህ አንድ ነው" ስንል ሚሽነሪዎች፦ "በምንድን ነው አንድ? በማንነት ወይስ በምንነት? ብለው ይጠይቃሉ፥ ምክንያቱም በእነርሱ እምነት "አምላክ በማንነት ሥስት በምንነት አንድ ነው" ተብሎ ስለሚታመን "አሏህ አንድ ምንነት እንጂ ስንት ማንነት እንዳለው አይታወቅም" የሚል ባቦሰጥ ንግግር ይናገራሉ።
"ማንነት" ማለት "ማን ነው" ብለን የምንጠይቅበት የምንነት መገለጫ"identity" ሲሆን "ምንነት" ማለት ደግሞ "ምንድን ነው" ብለን የምንጠይቅበት የማንነት መሠረት"being" ነው። እኔ በምንነቴ ሰው ነኝ፥ የፈጠረኝ አሏህ ግን በምንነቱ አምላክ ነው። እርሱም ምንነቱን የማያጋራ አንድ አምላክ ነው፦
2፥163 አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ እጅግ በጣም ርኅሩህ አዛኝ ነው፡፡ وَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۖ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الرَّحْمَـٰنُ الرَّحِيمُ

እዚህ አንቀጽ ላይ "አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "ዋሒድ" وَاحِد ሲሆን አምላካች አሏህ አንድ አምላክ እንደሆነ አስረግጦ ያሳያል። እኔ በማንነቴ አንድ ስሆን እራሴን የምገልጽበት "እከሌ" ለምሳሌ፦ "ወሒድ" እባላለው፥ ሁሉን የፈጠረ አንድ አምላክ በማንነቱ አንድ ሲሆን "አሏህ" ይባላል፦
20፥14 እኔ አላህ እኔ ነኝ፥ ከእኔ በቀር አምላክ የለምና አምልከኝ፡፡ ሶላትንም እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡ إِنَّنِي أَنَا اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدْنِي وَأَقِمِ الصَّلَاةَ لِذِكْرِي

"አና" أَنَا ማለት "እኔ" ማለት ሲሆን "አና" أَنَا የሚለው ደሚሩ አሽ-ሸኽስ ማንነትን ያሳያል፥ "እኔ" አንድ ነጠላ ማንነትን"one singular person" ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ስለዚህ "እኔ" የሚለውን መደብ ተውላጠ ስም"personal pronoun" አሏህ አንድ ማንነት እንደሆነ ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ ይህ አንድ ማንነት ምንነቱ አምላክ ስለሆነ "ከእኔ በቀር አምላክ የለም" በማለት ይናገራል። "አምልኩን" እያሉ የሚናገር አንድ "እኔነት" ነው፦
21፥92 "እኔም" ጌታችሁ ነኝና "አምልኩኝ"፡፡ وَأَنَا رَبُّكُمْ فَاعْبُدُونِ

"ሸኽስ" شَخْص ማለት "ማንነት"person" ማለት ሲሆን በነሕው ሕግ "ሸኽሱል ሙፍረድ" الشَخْص المُفْرَد ማለትም "ነጠላ ማንነት"singular person" ለመጠቀም በሙተከለም "አና" أَنَا ነው፥ ስለዚህ አሏህ "አና" ስላለ በማንነት አንድ ነው። "ሁወ" هُوَ በጋኢብ ለአንድ ነጠላ ማንነት የሚውል ደሚሩ አሽ ሸኽስ ከሆነ አሏህ ስለ ራሱ "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ "ሁወ" هُوَ ብሏል፦
12፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው»። قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ

እዚህ አንቀጽ ላይ "አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን ምንም መፈናፈኛ እንዳይኖር አርጎ ከርችሞታል፥ ምክንያቱም "አሐድ" አንድ ማንነትን ለማሳየት ብዙ ቦታ መጥቷል፦
72፥22 «እኔ ከአላህ ቅጣት አንድም አያድነኝም፡፡ ከእርሱም ሌላ መጠጊያን አላገኝም» በላቸው፡፡ قُلْ إِنِّي لَن يُجِيرَنِي مِنَ اللَّهِ أَحَدٌ وَلَنْ أَجِدَ مِن دُونِهِ مُلْتَحَدًا
72፥20 «እኔ የማመልከው ጌታዬን ብቻ ነው፡፡ በእርሱም አንድንም አላጋራም» በል፡፡ قُلْ إِنَّمَا أَدْعُو رَبِّي وَلَا أُشْرِكُ بِهِ أَحَدًا

"ከአላህ ቅጣት አንድም አያድነኝም" ሲል ከአሏህ ጋር የሚያድን አንድ ማንነት እንደሌለ የሚያሳይ ሲሆን "በእርሱም አንድንም አላጋራም" ሲል ከአሏህ ጋር አምልኮትን የሚጋራ አንድ ማንነት እንደሌለ ያሳያል። አሏህን በማንነት የሚመስል ማንም ማንነት የለም፦
112፥4 ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡ وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ
1.6K viewsedited  06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ