Get Mystery Box with random crypto!

'ከ-ሚፈጥረው' የሚለውን ይሰመርበት! 'የኽሉቁ' يَخْلُقُ የሚለው ፊዕሉል ሙዷሪዕ 'የተኺዘ' | ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

"ከ-ሚፈጥረው" የሚለውን ይሰመርበት! "የኽሉቁ" يَخْلُقُ የሚለው ፊዕሉል ሙዷሪዕ "የተኺዘ" يَتَّخِذَ ከሚለው ጋር መምጣቱ በራሱ "መያዝ" ልክ እንደ መውለድ የባሕርይ ጉዳይ ሳይሆን ሳይወልዱ ወደ ራስ በማስጠጋት ከሚፈጥረው ፍጡራን መያዝ ነው፥ ጥራት ይገባው! እርሱ አሸናፊው አንዱ አሏህ ነው፡፡ በሌላ አንቀጽ ደግሞ "ከ-እኛ ዘንድ" በማለት እርሱ ዘንድ "ከ-ተፈጠሩ ፍጥረታት" መያዝ ቢፈልግ ልጅ መያዝ ይችል ነበር፥ ነገር ግን ጥራት ይገባው! ይህ ለእርሱ ተገቢ አይደለም፦
21፥17 መጫወቻን "ልንይዝ" ብንፈልግ ኖሮ "ከ-እኛ ዘንድ" በያዝነው ነበር፡፡ ግን ሠሪዎች አይደለንም፡፡ لَوْ أَرَدْنَا أَن نَّتَّخِذَ لَهْوًا لَّاتَّخَذْنَاهُ مِن لَّدُنَّا إِن كُنَّا فَاعِلِينَ

እዚህ አንቀጽ "መጫወቻ" ለሚለው የገባው ቃል "ለህው" لَهْو ሲሆን "መደሰቻ" "መጠቀሚያ" "የዓይን ማረፊያ እና መርጊያ" ማለት ነው፥ ልጅ ለወላጅ ሆነ ለአሳዳጊ መደሰቻ ነው።
21፥17 ላይ በመጀመሪያ መደብ ያለውን ሐረግ የሚፈታልን 39፥4 ላይ በሦስተኛ መደብ ያለው ሐረግ ነው፥ በመጀመሪያ መደብ "አረድና" أَرَدْنَا ብሎ በሦስተኛ መደብ "አራደ" أَرَادَ ይለናል። "ከእኛ ዘንድ" የሚለውን "ከ-ሚፈጥረው" በማለት ይፈታልናል፥ "ከእኛ ዘንድ" የሚለውን ሚሽነሪዎች "ከእኛ ውስጥ" በማለት የአሏህ እኛነትን ብዙ አካላት እንደሆነ ለማመልከት ያጭበረብሩበታል። ነገር ግን "ዘንድ" እና "ውስጥ" የሚባሉትን መስተዋድድ በቅጡ ካለመረዳት የመጣ የተሳከረ፣ የደፈረሰ፣ የተንሸዋረረ ምልከታ ነው፦
19፥5 «እኔም ከበኋላዬ ዘመዶቼን በእርግጥ ፈራሁ፡፡ ሚስቴም መካን ነበረች ስለዚህ "ከ-አንተ ዘንድ" ለእኔ ልጅን ስጠኝ፡፡ وَإِنِّي خِفْتُ الْمَوَالِيَ مِن وَرَائِي وَكَانَتِ امْرَأَتِي عَاقِرًا فَهَبْ لِي مِن لَّدُنكَ وَلِيًّا

ዘከሪያ፦ "ከ-አንተ ዘንድ" ሲል "ከ-አንተ ውስጥ" ማለቱ አልነበረም፥ ቅሉ ግን ልጅ ከአሏህ ዘንድ የሚሰጥ ነው። አሏህ ልክ እንደ ፈርዖን ሚስት እና እንደ ያም ከምስር እንደ ገዛው ሰው መጫወቻ ልጅ መያዝ ቢፈልግ ኖሮ ከሚፈጥረው መያዝ ይችል ነበር፥ ነገር ግን ይህ ለእርሱ ተገቢ እንዳልሆነ እራሱ ተናግሯል። "መጫወቻን ልንይዝ ብንፈልግ ኖሮ ከእኛ ዘንድ በያዝነው ነበር" ሲል ዐውደ ንባቡ ላይ ከፈጠራቸው እርሱ ዘንድ ያሉትም መላእክት ያመለክታል፥ ቁረይሾችም "አልረሕማንም ከመላእክት ልጅን ያዘ" ብለዋልና፦
21፥19 በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉም የእርሱ ነው፡፡ "እርሱ ዘንድ" ያሉትም መላእክት" እርሱን ከማምለክ አይኮሩም፡፡ አይሰለቹምም፡፡ وَلَهُ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ وَمَنْ عِندَهُ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِ وَلَا يَسْتَحْسِرُونَ
21፥26 «አልረሕማንም ከመላእክት ልጅን ያዘ» አሉ፡፡ ጥራት ተገባው፡፡ አይደለም መላእክት የተከበሩ ባሮች ናቸው፡፡ وَقَالُوا اتَّخَذَ الرَّحْمَـٰنُ وَلَدًا ۗ سُبْحَانَهُ ۚ بَلْ عِبَادٌ مُّكْرَمُونَ

"እርሱ ዘንድ" "አንተ ዘንድ" "እኛ ዘንድ" የሚለው እርሱ ዘንድ ያሉትን ፍጡራን ለማመልከት የመጣ ነው፥ ጥቅሉ ግን በአሏህ ባሕርይ መውለድ የሚባል ባሕርይ ካለመኖር ባሻገር ሳይወልድ እንደ ማደጎ ከሚፈጥረው መጫወት ልጅ መያዝ አይፈልግም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም