Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Silver
Platinum
Golden
Cloudbridge
Traininginstitute
Samitech
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.23K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 159

2022-12-14 14:33:31
አብዱ የሻወር ውሃ ማሞቂያ ሽያጭና ጥገና
ጤና ይስጥልን ቤተሰቦች
.. የተለያዩ የሻወር ውሃ ማሞቂያዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ይዘን ቀርበናል
.... sterling, lorenzeti, atmor, milano, arston, florence.. እንዲሁም ሌሎችን .....
በብቁ ባለሙያዎቻችን ያሉበት ድረስ በመምጣት እንገጥማለን እንዲሁም የተበላሸ ካሎት እናስተካክላለን
ለበለጠ መረጃ 0921461805/0941074778
telegram link https://t.me/abduawe
21.5K views11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 21:04:21
"ኮካ ኮላ በኢትዮጵያ የገንዘብን ሽልማት የሚሸልም ውድድር ወይም ሎተሪ የለውም።" ድርጅቱ

ከኮካ ኮላ የገንዘብ ሽልማት እንዳገኙ በማስመሰል ሰዎች ሽልማቱን ያሸነፉ መሆኑን የሚገልፁ የማጭበርበሪያ መልዕክቶችን በተለያዩ መንገዶች አማካኝነት የሚያሰራጩ ግለሰቦች በመኖራቸው ደንበኞቹ እንዲጠነቀቁ ካንፖኒው በላከልን መልዕክት ገልጾልናል።

"ኮካ ኮላ በኢትዮጵያ የገንዘብን ሽልማት የሚሸልም ውድድር ወይም ሎተሪ የለውም።" ያለው ድርጅቱ ሽልማት የሚያስገኙ ፕሮግራሞች ሲኖሩትም በግልፅ ለህዝብ በማሳወቅና ባሉት የማኅበራዊና የሚዲያ ማስታወቂያዎች እንደሚያስነግር አስታውቋል።

@tikvahethmagazine
19.8K viewsedited  18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 20:38:14
#እንድታውቁት

ከኮዬ ፈጬ አደባባይ እስከ ሃጫሉ ሁንዴሳ አደባባይ ያለው መንገድ በውሃ መስመር ዝርጋታ ምክንያት ከነገ ታህሳስ 5/2015 ዓ.ም ጀምሮ ስራው እስኪጠናቀቅ ድረስ በከፊል የሚዘጋ ይሆናል።

በዚሁ መሰረት በመጀመሪያው ዙሪ ከኮዬ ፈጬ አደባባይ ወደ ሃጫሉ ሁንዴሳ የሚወስደው መንገድ ዝግ ይሆንና በተቃራኒ ያለው መንገድ ወደ ሁለቱም አቅጣጫ አሽከርካሪዎች የሚጠቀሙበት ሲሆን የውሃ መስመር ዝርጋታው ሲጠናቀቅ በተቃራኒው ከሃጫሉ ሁንዴሳ ወደ ኮዬ ፈጬ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ዝግ ሆኖ በተመሳሳይ ሁኔታ የባለአንድ አቅጣጫ መንገዱን ወደ ሁለቱም አቅጣጫ የሚጠቀሙበት ይሆናል።

ስለሆነም የትራፊክ ፍሰቱ እንዳይጨናነቅ እና ደህንነቱም የተረጋገጠ እንዲሆን አሽከርካሪዎች በጥንቃቄ መንገዱን እንድትጠቀሙ፣ በአካባቢው ላይ በስራ ላይ ለሚሆኑ ባለሙያዎች ጥንቃቄ በማድረግና በሚሰጡት አቅጣጫ መሰረት በመንቀሳቀስ የበኩላችሁን ኃላፊነት እንድትወጡ ሲል የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስታውቋል።

@tikvahethmagazine
23.2K viewsedited  17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 10:49:32 ለወላጆች እና ተማሪዎች ...

በአዲስ አበባ ከተማ ካሉ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ጋር በተያያዘ ባለፈው ዓመት የነበረው ሁኔታ ዘንድሮ በተለይም ከሰሞኑን ተባብሶ ነበር።

ይኸውም ችግር በተለያዩ ወገኖች እና በመንግስት አካላት የተለያየ ማባራሪያ እየተሰጠበት ነው።

አንዳንድ ነዋሪዎች ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፣ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ያሉ ግለሰቦች፣ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚፅፉ ግለሰቦች ፤ የከተማው አስተዳደር ምንም በማያውቁ ተማሪዎች ላይ ያለፍላጎታቸው ጫና በማድረግ የኦሮሚያ ክልል መዝሙር እንዲዘምሩ፣ ባንዲራም እንዲሰቀል እና  የበላይነትን ለማስፈን እየሰራ ነው ፤ በአዲስ አበባ የሁሉም መቀመጫ ከሆነች ለምን የሌላው ቋንቋ አይሰጥም ? የሌላው ባንዲራ አይሰቀልም ? መንግስት በተለይም የኦሮሚያ ብልፅግና ሆን ብሎ አቅዶ የሚሰራው ስራ ዛሬ በግልፅ ካልተቃወምን ነገ መዘዙ አደገኛ ነው የሚል ሀሳብ ይሰነዝራሉ። ለሚፈጠረው ቀውስ ሁሉ መንግስትን ተጠያቂ በማድረግም ከድርጊቱ እንዲታቀብ ተማሪዎችን እንዲዘምሩ እና የክልል ባንዲራ ያለፍላጎት እንዲሰቀል ማስገደድ ማቆም አለበት ይላሉ።

በሌላ በኩል ፤ የከተማው አስተዳደር ፣ አስተዳደሩንም የሚደግፉ አንዳንድ አካላት ይኸው በአ/አ ትምህርት ቤቶች በአፋን ኦሮሞ የማስተማር ስራ አዲስ እንዳልሆነ ፣ በኢህአዴግ ጊዜ እንደጀመረ ፣ በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ተጀምሮ ፍላጎት በመጨመሩ መስፋፋቱ ፣ ባንዲራው እና መዝሙሩም የአ/አ ከተማ አስተዳደር የራሱ የአፋን ኦሮሞ ማስተማሪያ ስርዓተ ትምህርት ስለሌለው ከኦሮሚያ ክልል እንደተዋሰና እሱኑ እያስፈፀመ እንደሆነ፣ አሁን ለመፅደቅ በሂደት ላይ ባለ ስርዓተ ትምህርት ውስጥ ሌሎችም ቋንቋዎች እንዲሰጡ እየተሰራ መሆኑን ይገልጻሉ። ይህ እየታወቀ፣ በቀጣይም ሌሎች ቋንቋዎችን ፣ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ ለማድረግ ስራ እየተሰራ እንዳለ እየታወቀ ሆን ብሎ አጀንዳ በመፍጠር ከተማውን ለመበጥበጥ፣ በግጭት ገንዘብ ለማግኘት የሚፈልጉ አካላት ተማሪዎችን እያነሳሱ ፣ በብሄር እየከፋፈሉ ፣ እንደሆነ በዚህም ጉዳት እየደረሰ እንደሚገኝ ይገልጻሉ።

ይህ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከታችሁ የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች (ስለጉዳዩ በቂ ግንዛቤ ያላችሁ) ሁኔታውን እንዴት ነው እየተከታተላችሁ ያላችሁት ? እናተ በጉዳዩ ላይ ቀጥታ ባለቤት እንደመሆናችሁ  ምንድነው የምታውቁትና የተፈጠረው ?

የመንግስት አካላትን ፤ ከዛ በተቃራኒ ደግሞ የመንግስት ተቃዋሚ ኃይሎችን ሃሳብ በስፋት ተሰምቷል ሚዲያዎችንም ተቆጣጥሯል ወላጆች ምን ይላሉ ? ተማሪዎችስ ?

እባክዎትን እዚህ መልዕክት ማስቀመጫ ላይ ፤ የጉዳዩ ቀጥተኛ ባለቤት ካልሆናችሁ (የተማሪ ወላጅ ወይም ተማሪ) መልዕክት ባትልኩ ስንል በትህትና እንጠይቃለን።

@tikvahethiopia
33.7K views07:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 10:40:18
ባለፈው ሳምንት በኦሮሚያ ክልል በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ13 ሰዎች ህይወት አለፈ።

በኦሮሚያ ክልል ከህዳር 26 እስከ ጥቅምት 02  ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናቶች በተለያዩ አካባቢዎች በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች የ13 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ፤ በ9ሰዎች ላይ ከባድ እና በ6ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡

በንብረት ላይ የደረሰዉ ዉድመት በገንዘብ ሲተመን ከ300ሺ ብር በላይ እንደሚገመት የተነገረ ሲሆን አብዛኛዎቹ የሞት አደጋዎች የደረሱት በጭነት ተሽከርካሪ፣ በህዝብ ማመላለሻ እንዲሁም በሶስት እግር (ባጃጅ) ተሸርከርካሪዎች የተከሰቱ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

የአደጋዎቹ ሁኔታ ካለፈው ሳምንት ጋር ሲነፃፀር የቀነሰ ሲሆን ፤ የአደጋ መንስኤ ተብሎ የተመዘገበዉ ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት፣ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር ፣የተሽከርካሪ የቴክኒክ ችግር፣ርቀትን ጠብቆ አለማሽርከር መሆኑን ከብስራት ሬዲዮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

@tikvahethmagazine
29.7K viewsedited  07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 10:40:11
እንኳን ደስ አሎት ለGamezoneኦች ኦሪጂናል 100% SONY - PS4 JOYSTICK በተመጣጣ ዋጋ አቅርበንሎታል።
በፈለጉት የከለር ምርጫ

➩ ከአዲስ አበባ ውጪ ያላቹ በታማኝነት ያላቹበት ድረስ በ 1 ቀን ውስጥ ያዘዙንን እንልክሎታለን (ከዚህ በፊት በታማኝነት የላክናቸውን እቃዎች የቴሌግራም አካውንታችን ላይ በማየት ማስላክ  ይችላሉ)

PRICE = 4800 ETB ✶FIXED!!✶
LIMITED STOCK AVAILABLE
════════════════════
እንዲሁም Playsation 4 & 3 በተመጣጣኝ ዋጋ አለን
0944311523]
InBox Us On Telegram
@mamelaaaa |
✃┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
Join below
https://t.me/mame321a
28.0K views07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-13 10:40:02
አብዱ የሻወር ውሃ ማሞቂያ ሽያጭና ጥገና
ጤና ይስጥልን ቤተሰቦች
.. የተለያዩ የሻወር ውሃ ማሞቂያዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ይዘን ቀርበናል
.... sterling, lorenzeti, atmor, milano, arston, florence.. እንዲሁም ሌሎችን .....
በብቁ ባለሙያዎቻችን ያሉበት ድረስ በመምጣት እንገጥማለን እንዲሁም የተበላሸ ካሎት እናስተካክላለን
ለበለጠ መረጃ 0921461805/0941074778
telegram link https://t.me/abduawe
27.4K views07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 17:36:19
የ“ኤርፖርት ሲቲ” ግንባታ በተያዘው በጀት ዓመት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ።

ከሦስት ዓመት በፊት ይፋ የተደረገው የ”ኤርፖርት ሲቲ” ግንባታ በተያዘው በጀት ዓመት ለመጀመር የሚያስችለውን ሥራ እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።

በኦሮሚያ ክልል ከቢሾፍቱ ከተማ ጥቂት ወጣ ባለ ሥፍራ ላይ እንደሚገነባ የተገለጸው ይህ ፕሮጀክት፤ ዘመናዊ ሆቴሎች፣ ከቀረጥ ነጻ የግብይት ሥፍራና የካርጎ ሎጂስቲክ ማዕከል ይኖረዋል ነው የተባለው።

የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ ሲጠናቀቅ በዓመት 100 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል።

በቀጣይም የፕሮጀክቱን ዲዛይን ለሚሰሩ ኩባንያዎች ጨረታ እንደሚወጣ ጠቅሰው በተያዘው ዓመት ሁሉንም የዝግጅት ሥራዎችን በማጠናቀቅ ወደ ግንባታ ለመግባት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 5 ቢሊዮን ዶላር በጀት የተያዘለት ሲሆን፤ በአምስት ዓመታት ውስጥ ተገንብቶ እንደሚጠናቀቅም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ እንደ አስፈላጊነቱ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ ሊገነባ እንደሚችልም ጠቁመዋል። (ENA)

@tikvahethmagazine
20.2K viewsedited  14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 17:17:52
የዛምቢያ ፖሊስ የ27 ኢትዮጵያውያን አስከሬን በዛምቢያ ዋና ከተማ እሁድ እለት መገኘቱን አረጋግጧል።

የፖሊስ ምርመራ እንደሚያመለክተው ከ20 እስከ 38 ዓመት የሆናቸው ወንዶች ንግዌሬ በተባለ አካባቢ ባልታወቁ ሰዎች አስክሬናቸው ተጥሎ መገኘቱ ተናግሯል።

ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጎች እንደሆኑ እንደሚታመን የተነገረ ሲሆን አንድ ግለሰብ በህይወት እያለ በፍጥነት ወደ ሆስፒታል ለህክምና መወሰዱ ተገልጿል።

27ቱ አስከሬኖች ለምርመራ ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸውን ተነግሯል። ፖሊስ እንዲሁም ሌሎች የጸጥታ አካላት ምርመራ ላይ መሆናቸውም ነው የዜና አውታሮች የዘገቡት።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ በደረሰው አደጋ የተሰማውን ሀዘን ገልጾ የተሰራጨውን ዘገባ እንደሚያጣራ አሳውቋል።

ግለሰቦቹ በህገወጥ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ ሲሉ ህይወታቸውን ማጣታቸው መዘገቡን የጠቆመው ሚንስቴሩ አደጋውን ለማጣራት ባለሙያዎችን ወደ አካባቢው በማሰማራት ከዛምቢያ መንግስት ጋር እንደሚሰራም አረጋግጧል፡፡

ቀደም ሲል በተመሳሳይ ሁኔታ ማላዊ ውስጥ ህይወታቸው ያለፉ ወገኖችን ሁኔታ ለመመርመር በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተመራ ቡድን በአገሪቱ እንደሚገኝም አስታውሷል፡፡

@tikvahethmagazine
19.6K viewsedited  14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-12 13:52:18
#ጥንቃቄ

የአንድ ብሩን ሳንቲም በሺዎች በሚቆጠር ገንዘብ እንገዛለን ከሚሉ አጭበርባሪዎች ኅብረተሰቡ ራሱን እንዲጠብቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳስቧል።

ከሰሞኑ በተለያዩ ማኅበራዊ ድረገፆች አራት የግዕዝ ፊደላት ያሉትን የአንድ ብር ሳንቲም በ2 ሺህ ብር እና ከዚያም በላይ እንገዛለን የሚሉ ከእውነት የራቁ ሀሰተኛ ማስታወቂያዎች በስፋት ተስተውለዋል።

ማስታወቂያዎቹ ኅብረተሰቡን ለማጭበርበር እየተነገሩ ያሉ እና ከእውነት የራቁ መሆናቸውን ያሳወቀው ብሔራዊ ባንኩ፣ ኅብረተሰቡ ራሱን ከአጭበርባሪዎች ሊጠብቅ እንደሚገባ ገልጿል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ በበኩሉ፣ ድርጊቱ በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑን አሳውቆ በዚህ ማጭበርበር ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ግለሰቦች ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ አስጠንቅቋል፡፡(EBC)

@tikvahethmagazine
26.3K viewsedited  10:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ