Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Safaricomethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.61K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 156

2022-12-29 12:23:45
በከባድ ዝናብ ምክንያት በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ

በጎፋ ዞን በቶ ከተማ አስተዳደር ትናንት አመሻሹን የጣለው ከባድ ዝናብ በ3ቱም ቀጠናዎች በመኖሪያ ቤት ፣ በንብረት እና በሰብል ላይ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱ ተገልጿል።

ጉዳቱ በባላ ቀጠና እና መሀል ከተማ አጠቃላይ በ 95 ቤቶች እና ቤተሰብ ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 19ኙ ሙሉ በሙሉ መኖሪያ ቤታቸው ላይ በደረሰው ጉዳት ተፈናቅለዋል ሲል የዞኑ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ገልጿል።

ጉዳት የደረሰባቸው አንድ ህፃን እና አንድ አዛውንት በህክምና ማዕከል እየተረዱ መሆኑንና ዝናቡ በእንስሳትም ላይ ጉዳት ማስከተሉንና የአካባቢው ህብረተሰብ እና የከተማዋ አመራሮች በቅንጅት የደረሰውን ጉዳት ማጣራት ላይ መሆናቸውን ከዞኑ ኮሚዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

@tikvahethmagazine
16.9K views09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 12:20:33
ባለፉት 3 ዓመታት ከአንድ ሺህ በላይ አርሶ አደሮች የቡና ላኪነት ፈቃድ ማግኘታቸውን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

የቡና ላኪነት ፈቃድ ከወሰዱት አርሶ አደሮች መካከል ከ100 በላይ የሚሆኑ ቡናቸውን በቀጥታ ለውጭ ገበያ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል፡፡

ባለፈው በጀት ዓመት 302 ሺህ ቶን ቡና ለውጭ ገበያ በመላክ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር የተገኘ ሲሆን በዘንድሮ በጀት ዓመት 360 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ በመላክ 2 ቢሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት ዕቅድ መያዙ ተበግሯል።

ባለስልጣኑ የዓለም የቡና ገበያ ተለዋዋጭነትን መሰረት በማድረግ ተጨማሪ የገበያ መዳረሻዎችን የማፈላለጉን ስራ በትኩረት እያከናወነ መሆኑን እንደ ኤዥያ ባሉ አካባቢዎች አዳዲስ የገበያ መዳረሻዎችን ለማስፋት እንቅስቃሴ መጀመሩን የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡

@tikvahethmagazine
14.2K viewsedited  09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 12:19:55
ነፃ የሽያጭ ስልጠና ላይ ይሳተፉ!

በሪልስቴት ሽያጭ ሙያ ላይ ተሰማርተው ገቢዎን ዕጥፍ ማድረግ ይፈልጋሉ? የሽያጭ ክፍል ኃላፊስ ሆነው የተሻለ ደመወዝ ማግኘት እና የስራ ደረጃዎትን ከፍ ማድረግ ይፈልጋሉ? ቢዝነስዎትንስ በዲጂታል ማርኬቲንግ አስተዋውቀው የሽያጭ መጠንዎን ማብዛት ይሻሉ?

ለጥያቄዎቹ መልስዎት አዎ ከሆነ፣ እኛ መልኅቅ ማርኬቲንግ እና ሊደርሺፕ ኢንስቲትዩት ለእርስዎ የሚሆን ነፃ የሽያጭ ስልጣን አዘጋጅተንልዎታል። 0967280828 ወይም 0115572357 በመደወል ይመዝገቡ!

ታህሳስ 20፣ 2015 ከ11:30 ጀምሮ

ጊዮን ሆቴል
13.1K views09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 12:19:33
https://t.me/Amirshifon1
availabe now
ከ ነፃ ዴሊቨሪ አዲስአበባ ዉስጥ ለሆናቹ
ይደዉሉልን 0933471055
                0979224310
በብዛት ለምትወስዱ ሽፎን ቤቶች ቅናሽ አለን
አድራሻችን
መርካቶ ሚሊተሪ ተራ አዲሱ ህንፃ F1-128C
telegram channal
https://t.me/Amirshifon1
13.0K views09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 10:00:16
ሁለተኛው ዙር የትምህርት መፅሀፍት ማሰባሰብ ዘመቻ ዛሬ ይጀመራል።

በዚህ ዙር በጦርነት የተጎዱ ትምህርት ቤቶች ከሚያስፈልጋቸው ቁሳቁስ አንፃር መማሪያ መፅሀፍ ብቻ ሳይሆን ፦

+ ነጭ ወረቀት
+ ያገለገለ ፕሪንተር
+ የፕሪንተር ቀለም
+ ማንኛውም አይነት ያገለገለ ኮምፒዩተር መስጠት ይቻላል።

ውድ ቤተሰቦቻችን በመጀመሪያው ዙር በጥቂት ቀናት ዘመቻ 8 ሺህ ገደማ መፅሀፍ መሰባሰቡ አይዘነጋም አሁን በትንሹ 30 ሺህ መፅሀፍ ለማግኘት ታቅዷል።

መስጠት የሚቻለው መፅሀፍ ፦

- ከ1-8 #አጋዥ_መፅሀፍ_ብቻ
- ከ9-12 ማኛውም መደበኛ (ቴክስት) እና አጋዥ መፅሀፍ

በተጨማሪ ፦ ከከተማ ወጣ ብሎ ለሚገኝ የህዝብ ቤተመፅሀፍ ማንኛውም አይነት አሉታዊ መልዕክት የማያስተላልፍ ልብወለድ መፅሀፍ መለግስ ይቻላል።

#አዲስ_አበባ ስልክ ፦ 0919743630

በቅርብ ቀናት በሀዋሳ ተመሳሳይ ዘመቻ ይኖራል።

ማሳሰቢያ ፦ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ የገንዘብ ድጋፍ የሚሰበሰብ ባለመሆኑ ከላይ የተዘረዘሩትን ቁሳቁሶች #የመግዛት_አቅም ያላችሁ ቁሳቁሶቹን ገዝታችሁ ማበርከት ትችላላችሁ።

የማሰባሰብ ስራው የሚያበቃበት ቀን ከየካቲት 30 በፊት።

@tikvahethiopia
18.1K views07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 17:15:34
#OmoBank

ኦሞ ባንክ በ2014 በጀት ዓመት 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል። ባንኩ አሁን ያለውን ሐብት ወደ 12 ቢሊየን ብር ያደረሰ ሲሆን በበጀት ዓመቱም 3 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ብድር ማሰራጨት መቻሉ ተመላክቷል፡፡

ባንኩ ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማሳደግ በደቡብ ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦችና በሲዳማ ክልል ቅርጫፎችን በመክፈት ሂደት ላይ ነው ተብሏል፡፡

ባንኩ ነሐሴ 1989 ዓ.ም በ500 ሺህ ብር ካፒታል እና በ4 ቅርንጫፎች የተመሰረተ ሲሆን ከዚህ ቀድም ኦሞ ማክሮ ፋይናንስ ተቋም በመባል የሚታወቅ ሲሆን በቅርቡ ወደ ባንክ ማደጉ የሚታወስ ነው፡፡

@tikvahethmagazine
23.8K viewsedited  14:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 15:33:01
የጓደኛዉን መኖሪያ ቤት ለመሸጥ በማሰብ በጓደኛዉ ስም መታወቂያ አጭበርብሮ ያስወጠዉ ግለሰብ...

በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ ተከሳሽ አቡበክር ሱጋቶ እና የቅርብ ጓደኛዉ ቶፊቅ ከድር አብረዉ በጓደኝነት እየኖሩ ቆይተዉ ተከሳሽ መኖሪያ ቤት ስለሌለዉ በቤት ኪራይ መቸገሩን ያስተዋለዉ ጓደኛዉ ከቤተሰቡ ጋር በመኖሪያ ቤቱ በተወሰኑ ክፍሎች እንዲኖር ይፈቅድለታል፡፡

ከዚያም ለግዜዉ ባልታወቀ ሁኔታ ጓደኛዉ ቶፊቅ ከድር ያሲን የደረሰበት ይጠፋል፤ ተከሳሽም ይህን አጋጣሚ እንደ መልካም እድል በመዉሰድ የጓደኛዉን ቶፊቅ ከድር ያሲንን መኖሪያ ቤት ለመሸጥ በከተማዉ ከሚገኙ የቤት ደላሎች አንድ ሚሊዮን ብር ይስማማል፡፡

በመቀጠል ግለሰቡ ወራቤ ከተማ አስተዳደር 02 ቀበሌ ጽ/ቤት በመሄድ ራሱን ቶፊቅ ከድር ያሲን እንደሆነ በመቅረብ አጭበርብሮ የቀበሌ መታወቂያ አስወጥቶ ድርድር ላይ ሳለ የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሙስና እና ሙስና ነክ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክትሬት ጥቆማ ይደርሰዋል፡፡

ከዞኑ ዓቃቤ ህግ የወንጀል ክስ የቀረበለት የስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤትም በመዝገብ ቁጥር 20153 ሲያከራክር ቆይቶ በቀን 14/04/2015 የሙስና ወንጀል ችሎት ተከሳሽን በከባድ ማታለል ወንጀል ጥፋተኛ ብታል፡፡

በዚህም ተከሳሽ የአራት ዓመት ከአምስት ወር ጽኑ እስራት እና አንድ ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ መወሰኑን የዞኑን ፍትህ መምሪያ ዋቢ አድርጎ የስልጢ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ዘግቧል፡፡

@tikvahethmagazine
26.0K viewsedited  12:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 14:05:08
እየተባባሰ የመጣው የአሰሪና ሰራተኛ አለመግባባት…

በሀገራችን በአሰሪዎችና በሰራተኞቻቸው በሚፈጠር አለመግባባትና ሌሎች ምክንያቶች አሰቃቂ ወንጀሎች ሲፈጸሙ ይስተዋላል ለአብነትም ከወራት በፊት አንዲት ሰራተኛ ሁለት ህጻንትን በአሰቃቂ ሁኔታ ገላ ፍርድ ቤትም የሞት ቅጣት እንደወሰነባት መገለጹ ይታወሳል።

በተጨማሪም የቤት ሰራተኛቸውን ገድለው በሳጥን ለመቅበር ጥረት ሲያደርጉ በአካባቢው ህብረተሰብ ትብብር በቁጥጥር ስር ውለው በ25 ዓመት ጽኑ እስራት የተቀጡት አሰሪዎች ደግሞ ሌላው በሚዲያው ቀረበ ማሳያ ነው፡፡

የፍትህ ሚንስቴር ዛሬ ባወጣው መረጃ ደግሞ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስኮ አዲስ ሰፈር ሊዝ መንደር አበቡ ሙላቴ የተባለችው ግለሰብ ጥቅምት 18 ቀን 2015 ዓ.ም የወር ደመወዝ አልተከፈለኝም በሚል ቂም ተነሳስታ አሰሪዋን መግደሏን ይገልጻል።

ጉዳዩን የተመለከተው ፍርድ ቤትም በዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንድትቀጣ እንዲሁም ማህበራዊ መብቶቹ ለዘወትር እንዲሻሩ መወሰኑን የፍትህ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በስራ አጋጣሚ ሰዎች በመካከላቸው በሚያስሩት ውል መሰረት አንዱ አሰሪ ሌላው ደግሞ ሰራተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ አሰሪዎች በሰራተኞች መብት እና ደህንነት ላይ አደጋ የሚጥሉ ድርጊቶችን የመፈጸም ስልጣን የላቸውም።

የቤት ሰራተኞችም ደግሞ በሚንከባከቧቸው ህጻናት እና በሚጠብቁት ንብረት ላይ በሚያስከትሉት ማንኛውም ጉዳት ሀላፊነት እና ተጠያቂነት እንዳለባቸው ተጠቅሷል።

ይህ ባልሆነበት ሁኔታ የወንጀል ህጉ እንደ ወንጀሉ ክብደት ከቀላል እስራት እስከ ሞት ሊያስቀጣ የሚችል የወንጀል ተጠያቂነትን ሊያስከትል እንደሚችል በማወቅ ተገቢው ጥንቃቄ መደረግ እንደሚኖርበት ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ፍትህ ሚንስቴር ከሰሞኑ ያወጣው መግለጫ ያመላክታል፡፡

@tikvahethmagazine
25.3K viewsedited  11:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 12:44:17
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን በ1 ሳምንት ብቻ ስድስት የብረት ማማዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን በሁለት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ዝርፊያ እንዲሁም ሆን ተብሎ አገልግሎት ለማቋረጥ በሚመስል መልኩ ጉዳት መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።

ጉዳት የደረሰባቸው የትኞቹ መስመሮች ላይ ነው?

1. ከቆቃ - አዋሽ 2 - ወንጂ መስመር

- ድርጊቱ የተፈጸመው ታህሳስ 15 ቀን 2015 ዓ.ም ሲሆን ስርቆት ከተፈጸመባቸው ምሶሶዎች ከእያንዳንዳቸው ከ60-100 የሚደርሱ ብረቶች ተሰርቀዋል።

- የወደቁትን ምስሶዎች መልሶ ለማቆም ለመሰረት ሥራው ብቻ  ለእያንዳንዱ አምስት መቶ ሺህ ብር ያስፈልጋል።

2. ከአዋሽ - መልካሳ - ወለንጪቲ መስመር

- ይህ መስመር ለኢትዮ -ጂቡቲ የባቡር መስመር ኃይል እንዲያቀርብ የተዘረጋ መስመር ነው።

ድርጊቱ የተፈጸመው ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ነው።

- በሁለት የብረት ምሶሶዎች ላይ ልዩ ተልዕኮ ያለው በሚመስል መልኩ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

- የብረት ምሶሶዎችን ከመጣልና መስመሩ አገልግሎት እንዳይሰጥ ከማድረግ ውጪ ምንም ዓይነት የሥርቆት ወንጀል አለመፈፀሙ ተገልጿል።

- በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ማማዎቹ ላይ በተፈፀመው ዝርፊያ ወንጂና አካባቢው ኃይል ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም አካባቢዎቹን በጊዜያዊነት ከቆቃ ኃይል እንዲያገኝ ተደርገዋል፡፡

@tikvahethmagazine
25.2K viewsedited  09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-27 12:44:02
ነፃ የሽያጭ ስልጠና ላይ ይሳተፉ!

በሪልስቴት ሽያጭ ሙያ ላይ ተሰማርተው ገቢዎን ዕጥፍ ማድረግ ይፈልጋሉ? የሽያጭ ክፍል ኃላፊስ ሆነው የተሻለ ደመወዝ ማግኘት እና የስራ ደረጃዎትን ከፍ ማድረግ ይፈልጋሉ? ቢዝነስዎትንስ በዲጂታል ማርኬቲንግ አስተዋውቀው የሽያጭ መጠንዎን ማብዛት ይሻሉ?

ለጥያቄዎቹ መልስዎት አዎ ከሆነ፣ እኛ መልኅቅ ማርኬቲንግ እና ሊደርሺፕ ኢንስቲትዩት ለእርስዎ የሚሆን ነፃ የሽያጭ ስልጣን አዘጋጅተንልዎታል። 0967280828 ወይም 0115572357 በመደወል ይመዝገቡ!

ታህሳስ 20፣ 2015 ከ11:30 ጀምሮ

ጊዮን ሆቴል
21.4K views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ