Get Mystery Box with random crypto!

ሁለተኛው ዙር የትምህርት መፅሀፍት ማሰባሰብ ዘመቻ ዛሬ ይጀመራል። በዚህ ዙር በጦርነት የተጎዱ ት | TIKVAH-MAGAZINE

ሁለተኛው ዙር የትምህርት መፅሀፍት ማሰባሰብ ዘመቻ ዛሬ ይጀመራል።

በዚህ ዙር በጦርነት የተጎዱ ትምህርት ቤቶች ከሚያስፈልጋቸው ቁሳቁስ አንፃር መማሪያ መፅሀፍ ብቻ ሳይሆን ፦

+ ነጭ ወረቀት
+ ያገለገለ ፕሪንተር
+ የፕሪንተር ቀለም
+ ማንኛውም አይነት ያገለገለ ኮምፒዩተር መስጠት ይቻላል።

ውድ ቤተሰቦቻችን በመጀመሪያው ዙር በጥቂት ቀናት ዘመቻ 8 ሺህ ገደማ መፅሀፍ መሰባሰቡ አይዘነጋም አሁን በትንሹ 30 ሺህ መፅሀፍ ለማግኘት ታቅዷል።

መስጠት የሚቻለው መፅሀፍ ፦

- ከ1-8 #አጋዥ_መፅሀፍ_ብቻ
- ከ9-12 ማኛውም መደበኛ (ቴክስት) እና አጋዥ መፅሀፍ

በተጨማሪ ፦ ከከተማ ወጣ ብሎ ለሚገኝ የህዝብ ቤተመፅሀፍ ማንኛውም አይነት አሉታዊ መልዕክት የማያስተላልፍ ልብወለድ መፅሀፍ መለግስ ይቻላል።

#አዲስ_አበባ ስልክ ፦ 0919743630

በቅርብ ቀናት በሀዋሳ ተመሳሳይ ዘመቻ ይኖራል።

ማሳሰቢያ ፦ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ የገንዘብ ድጋፍ የሚሰበሰብ ባለመሆኑ ከላይ የተዘረዘሩትን ቁሳቁሶች #የመግዛት_አቅም ያላችሁ ቁሳቁሶቹን ገዝታችሁ ማበርከት ትችላላችሁ።

የማሰባሰብ ስራው የሚያበቃበት ቀን ከየካቲት 30 በፊት።

@tikvahethiopia