Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Update
Silver
Platinum
Golden
Cloudbridge
Traininginstitute
Samitech
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.23K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 158

2022-12-16 10:32:46
በኤሌክትሪክ መኪና የቴክኖሎጂ ትራንስፖርት አገልግሎት ለመስራት ዝግጁ ኖት?

በቀን ከ 2,000 ብር በወር ከ 60,000 ብር በላይ ገቢ ያግኙ፤
ከ 10% ጀምሮ ቅድመ ክፍያን በመክፈል የኤሌክትሪክ መኪኖችን የማግኛ እድል፤
በ 60 ብር የኤሌክትሪክ ቻርጅ ከ 300 ኪሎ ሜትር በላይ ይጠቀሙ፤
አገልግሎቱን በግልዎ አሊያም ከሰለጠኑ ሹፌሮቻችን ጋር መስጠት ይችላሉ፤
ቀሪ ክፍያዎን ዋስትና በማቅረብ ከእኛ ጋር በመስራት የሚከፍሉት፤

ከስማርት ጋር ይስሩ ፤ ከጊዜ ጋር ይበልጽጉ!

ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቤተሰብ ይሁኑ!
https://t.me/SmartHibret

በኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/smarthibret/

በፌስቡክ ገጻችን ይከታተሉን!
https://www.facebook.com/profile.php?id=100087358936762
#ስማርትህብረት
23.5K views07:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-15 15:29:27
ከሰሞኑ በስፋት የተከሰተው ጉንፋን መሳይ የበሽታ ምልክት ኮቪድ 19 የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው ተባለ

ከሰሞኑ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጉንፋን መሳይ የበሽታ ምልክት በስፋት መከሰቱንና ይህም የመተንፈሻ አካላትን የሚያጠቃ ጉንፋን መሳይ የበሽታ ምልክት ኮቪድ 19 የመሆን እድሉ ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡

ጉንፋን መሰሉን የበሽታ ምልክት ሁሉ ኮቪድ19 ነው ማለት ባይቻልም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቱ የኮቪድ 19 ስርጭት እየጨመረ መጥቷል፤ የበሽታ ምልክቱ ኮቪድ-19 የመሆን እድሉ ከፍተኛ ስለሆነ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል፡፡

በተለይ ባለፉት አምስት ተከታታይ ሳምንታት በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ስርጭት የመጨመር አዝማሚያ ማሳየቱን ሲሆን ከ1 በመቶ በታች ወርዶ የነበረው የስርጭት ምጣኔው አሁን ላይ ግን ወደ 4 ነጥብ 5 በመቶ ማሻቀቡን ተነገሯል፡፡

ለአብነትም ባለፉት ሰባት ቀናት ለ11 ሺሕ 920 ሰዎች ምርመራ ተደርጎ በ662ቱ ላይ ኮቪድ-19 መገኘቱ የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ ከመያዙ በፊት ለመከላከል የሚያስችሉ ዘዴዎችን መጠቀምና ምልክቱ ሲታይም ፈጥኖ መመርመር እንደሚገባው ተጠቁሟል።(ዋልታ)

@tikvahethmagazine
34.6K viewsedited  12:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-15 15:28:42
በኢትዮጵያ 68% የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች እና 51% የሶስተኛ ክፍል ተማሪዎች ማንበብ እንደማይችሉ ተነገረ

በኢትዮጲያ በተለያዩ የአንደኛ ደረጃ 168 ትምህርትቤቶች በሚገኙ በ 9,000 ተማሪዎች በተጠናዉ ጥናት መሰረት 2ኛ ክፍል ተማሪዎች 68% እና 3ኛ ክፍል ተማሪዎች 51% ያህሉ ማንበብና መጻፍ እንደማይችሉ ተገልጿል።

የተማሪዎችን የትምህርት ዉጤት ለማሻሻል የትምህርት ስርአቱ የተናበበ እና የተቀናጀ ትግበራ አስፈላጊ እንደሆነ በጥናቱ ላይ የተመላከተ ሲሆን የትምህርት ስርአቱ ትኩረት ተሰቶበት ሊሰራ እንደሚገባም ተጠቁሟል።

በተጨማሪም በቅድመ መደበኛ ተማሪዎች ላይ እና ከ 1- 4 ተማሪዎች መሰረታዊ ክሎት ማለትም ማንበብ እና መፃፍ፣ ሂሳብ ማስላት እና የተረጋጋ ስነልቦና እና መልካም ማህበራዊ መስተጋብር እንዲኖራቸው መሰራት አለበት ተብሏል፡፡

በዛሬው እለት ''Rise Ethiopia'' ፕሮግራም በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ አዘጋጅነት በ ሂልተን ሆቴል አየተካሄደ ሲሆን መሰል ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት በ ትምህርት ዙርያ ያሉ ችግሮችን መቅረፍ እንደሚቻል በፕሮግራሙ ላይ መገለጹን ከዩንቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

@tikvahethmagazine
30.3K viewsedited  12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-15 10:57:50
#ንብኢንተርናሽናልባንክ

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በ2021/22 የበጀት ዓመት 1.76 ቢሊዮን ብር ትርፍ አስመዝግቧል። ይህም የትርፍ መጠን ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር 139.3 ሚሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ተገልጿል።

ከእዚህ በተጨማሪ በአሁን ሰዓት የባንኩ አጠቃላይ ሀብት 61.49 ቢሊዮን ብር መድረሱ የተጠቆመ ሲሆን ይህ የሀብት መጠን ባለፈው በጀት ዓመት ከተመዘገበው የሀብት መጠን 7.3 ቢሊዮን ወይም 13.45 ጭማሪ ማሳየቱ ተጠቁሟል።

ከ23 ዓመታት በፊት በ7 መቶ 17  መስራች አባላት የተቋቋመው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማህበር በአሁን ሰዓት 7578 ሰራተኞችን ይዞ በ410 ቅርንጫፎች በመላ ሀገሪቱ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ ተነግሯል።

@tikvahethmagazine
30.9K viewsedited  07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-15 10:57:34
በ58 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የዳቦ ፋብሪካ ተመረቀ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ በግል ባለሃብት የተገነባው ከረዩ ዳቦ ፋብሪካ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ሌሎች የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተመርቋል፡፡

ፋብሪካው አሁን ላይ በቀን 250 ሺህ ዳቦ በማምረት ስራውን የጀመረ ሲሆን÷ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባ በቀን 1 ሚሊየን ዳቦ ያመርታል ተብሎ ይጠበቃል ።

ለከረዩ ዳቦ ማምረቻ እና ማከፋፈያ መንግስት  የዱቄት  አቅርቦት ስራ  የሚሰራ መሆኑ  የተነገረ ሲሆን የንግድ ቢሮ በሚያወጣው ቅናሽ የዳቦ መሸጫ ተመን እንደሚያከፋፍልም ተገልጿል፡፡

አሁን ላይ ለ30 ሰዎች የስራ ዕድል የፈጠረው ፋብሪካው ÷በቀጣይ 150 የሚጠጉ ሰራተኞች እንደሚኖሩት ከፋና ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

@tikvahethmagazine
28.3K viewsedited  07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-15 10:57:08
እንኳን ደስ አሎት ለGamezoneኦች ኦሪጂናል 100% SONY - PS4 JOYSTICK በተመጣጣ ዋጋ አቅርበንሎታል።
በፈለጉት የከለር ምርጫ

➩ ከአዲስ አበባ ውጪ ያላቹ በታማኝነት ያላቹበት ድረስ በ 1 ቀን ውስጥ ያዘዙንን እንልክሎታለን (ከዚህ በፊት በታማኝነት የላክናቸውን እቃዎች የቴሌግራም አካውንታችን ላይ በማየት ማስላክ  ይችላሉ)

PRICE = 4800 ETB ✶FIXED!!✶
LIMITED STOCK AVAILABLE
════════════════════
እንዲሁም Playsation 4 & 3 በተመጣጣኝ ዋጋ አለን
0944311523]
InBox Us On Telegram
@mamelaaaa |
✃┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
Join below
https://t.me/mame321a
26.4K views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 18:17:37
የ10 ልጆችና ነብሰጡር የሆነች ባለቤቱን በጥይት መቶ የገደለ ግለሰብ...

በደቡብ ክልል ቡርጂ ልዩ ወረዳ ነዋሪ የሆነዉ ተጠርጣሪ የ22 ዓመት የትዳር አጋሩና የ10 ልጆች እናት የሆነችዉ ነብሰጡር ባለቤቱን በአንድ ጥይት ደረቷን መቶ የግድያ ወንጀል እንደፈፀመ ከአካባቢዉ ህብረተሰቡ ለፖሊስ በደረሰ ጥቆማ መነሻ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ያውለዋል።

ተጠርጣሪዉ በቅርቡ መሬት ሸጦ ክላሽንኮቭ ጠብመንጃ መግዛቱና በተደጋጋሚ ጠጥቶ እየሰከረ ወደቤት መመለሱ ያላስደሰታት ባለቤቱ ድርጊቱን በመቃወሟ ምክንያት ባልና ሚስቱ ይጨቃጨቁ እንደነበር ፖሊስ በአካባቢያዊ ማስረጃ ማረጋገጡ ተነግሯል።

ተጠርጣሪዉ ህዳር 30/2015 ዓ.ም በመጠጥ ሲዝናና አምሽቶ ምሽት 2:00 ሰዓት ላይ ወደ ቤት በመመለስ ከብቶችን ስታግድ የዋለች የትዳር አጋሩን በጥይት ለህልፈት የዳረገበት ምክንያት መሳሪያዉ ባርቆብኝ ነዉ በማለት አስረድቷል።

ይሁን እንጂ ከተጠረጠረበት ወንጀል ለመሸሽ የቀረበ ምክንያት ነዉ ሲል ፖሊስ የግለሰቡን ሀሳብ ዉድቅ የሚያደርግ ተጨባጭ መረጃ እንዳለዉ ገልፆ ወንጀሉ ሆን ብሎ እንደፈፀመዉ አረጋግጫለሁ ማለቱን ደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

@tikvahethmagazine
19.3K viewsedited  15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 14:38:39
ከ11 ሺህ በላይ ሰራተኞችን ለመቅጠር በወጣው ማስታወቂያ ከ130 ሺህ በላይ አመልካቾች ለፈተና ቀረቡ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ11 ሺህ በላይ ሰራተኞችን ለመቅጠር ከ130 ሺህ በላይ አመልካቾች የጽሑፍ ፈተና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አማካኝነት ላለፉት አራት ተከታታይ እሑዶች መስጠቱን አስታውቋል።

ፈተናው በአዲስ አበባ የኒቨርሲቲ የንግድ ክፍል የተሰጠ ሲሆን ዩኒቨርስቲው ፈተናውን ከማዘጋጀት ጀምሮ እስከ ውጤት ድረስ በጥንቃቄ ማከናወኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የፈተናውን ሒደት አስመልከቶ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በዛሬው ዕለት በሰጡት የጋራ መግለጫ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ፈተናው ወጥቷል ተብሎ ሲሰራጭ የነበረው መረጃ ፈጽሞ ከእውነት የራቀ ነው ሲሉ አንስተዋል። (FBC)

@tikvahethmagazine
26.1K viewsedited  11:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 14:33:42
ከጅብሰም ጋር ተጭኖ ወደ ኬኒያ ሊሻገር የነበረ አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ስር ዋለ

በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- አ.አ06344 በሆነ ኤፍኤስአር የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ከጅብሰም ጋር ተቀላቅሎ የተጫነ 6,150 ኪ.ግ ካናቢስ የተሰኘዉ እፅ በቁጥጥር ስር መዋሉ የዞኑ ፖሊስ አስታዉቋል።

አደንዛዥ እጹን የጫነዉ ተሽከርካሪ በኤርቦሬ መስመር በጉዞ ላይ ሳለ በበናፀማይ ወረዳ ወይጦ ወይም ብራይሌ ተብሎ በሚጠራዉ የገጠር ከተማ እንደደረሰ ታህሳስ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ለሊት 8:00 ሰዓት ላይ የደቡብ ልዩ ኃይል አባላት ባደረጉት ክትትል በቁጥጥር ስር መዋሉ ታውቋል።

ሾፌሩ ንብረቱን ከጫነዉ ግለሰብ ጋር ያመለጡ ሲሆን የተሽከርካሪዉ ረዳትና ተሽከርካሪዉን ከነጭነቱ በቁጥጥር ስር አዉሎ ፖሊስ ምርመራ ማጣራት መጀመሩ ታውቋል።

እፁ ከምስራቅ አርሲ ዞን ሻሸመኔ አካባቢ የተጫነ መሆኑን ፖሊስ በምርመራ ማረጋገጡን ከደቡብ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።

@tikvahethmagazine
24.1K viewsedited  11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-14 14:33:31
እንኳን ደስ አሎት ለGamezoneኦች ኦሪጂናል 100% SONY - PS4 JOYSTICK በተመጣጣ ዋጋ አቅርበንሎታል።
በፈለጉት የከለር ምርጫ

➩ ከአዲስ አበባ ውጪ ያላቹ በታማኝነት ያላቹበት ድረስ በ 1 ቀን ውስጥ ያዘዙንን እንልክሎታለን (ከዚህ በፊት በታማኝነት የላክናቸውን እቃዎች የቴሌግራም አካውንታችን ላይ በማየት ማስላክ  ይችላሉ)

PRICE = 4800 ETB ✶FIXED!!✶
LIMITED STOCK AVAILABLE
════════════════════
እንዲሁም Playsation 4 & 3 በተመጣጣኝ ዋጋ አለን
0944311523]
InBox Us On Telegram
@mamelaaaa |
✃┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈┈
Join below
https://t.me/mame321a
21.0K views11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ