የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
194.85K
የሰርጥ መግለጫ
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን 251913134524
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
1
3 stars
1
2 stars
0
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 161
2022-11-17 11:38:50
ሎዛ የስነ ምግብ ማማከርና ህክምና ማዕከል
የላቀ እውቀት ባላቸው ሀኪሞችና የስነ ምግብ ባለሙያወች ሳንንሳዊና ተፈጥሯዊ በሆነ የምግብ ሥርዓት ጤናዎ እንዲስተካከል እንደርጋለን።
ይደውሉልን በ 0989300007 | 0993503136
በ Telegram: https://t.me/famwel21
20.2K views08:38
2022-11-17 11:38:50
http://t.me/dunamisRM ሱፐር ዱናሚስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር
በጥሬ እቃ አስመጪነት ላይ ለተሰማራቹ ባለሀብቶች በጅቡቲ በቀጥታ መጫን ለምትፈልጉ ሁሉ አለምአቀፍ እውቅና ካላቸው ድርጅቶች ጋር ያገናኞታል።
ለፋብሪካዎ ጥሬ እቃ ይፈልጋሉ?
1. የፕላስቲክ ጥሬ እቃ
2.የተለያዩ ኬሚካሎች
3.የኢንዱስትሪ ግብአቶች
- PET RESIN - PARAFFIN OIL
- PP RAFFIA - POLYOL & TDI
- HDPE INJ. - DOP
- HDPE BLOW - COPOLYMER
- LDPE - HDPE FILM
- SOAP NOODLES & OTHER INDUSTRIAL RAW MATERIALS
Call - +251911428276 , +251902454776 , +251703008276
Join Us: http://t.me/dunamisRM
22.0K views08:38
2022-11-16 15:12:05
ልማት ባንክ የሶስተኛ ደረጃ ህክምና ለሚሰጡ የጤና ተቋማት ብድር መስጠት ሊጀምር ነው
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁና በውጭ አገራት የሚሰጡ የሶስተኛ ደረጃ የህክምና አገልግሎቶችን በሀገር ውስጥ መስጠት ለሚችሉ የጤና ተቋማት ብድር መስጠት ሊጀምር መሆኑን አስታውቋል።
ሶስተኛ ደረጃ (ተርሸሪ ሌቭል) ሆስፒታል ዘመናዊ መሳሪያዎችን አካቶ የተሟላ አገልግሎትን ለታካሚዎች የሚሰጥ ሲሆን ከሁለተኛና አንደኛ ደረጃ ሆስፒታሎች በሪፈር የሚላኩ ታካሚዎችን ተቀብሎ አገልግሎት የሚሰጥ ጤና ተቋም ነው።
የባንኩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው ለኢዜአ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት ባንኩ ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁና በውጭ የሚደረጉ የህክምና አገልግሎቶችን በሀገር ውስጥ እንዲጀመር ለማስቻል አገልግሎቱን የሚሰጡ ተቋማትን ለመደገፍ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
በዘርፉ ድጋፍ ለማግኘት ጥያቄ ያቀረቡ መኖራቸውን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ ፕሮጀክቱን በቀጣዮቹ አራት ወራት ለማፅደቅ መታቀዱን አስረድተዋል።
@tikvahethmagazine
34.7K viewsedited 12:12
2022-11-16 15:02:55
በኦሮሚያ ክልል የወባ፣ የኩፍኝ እና የኮሌራ ወረርሽኝ መከሰቱን የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ገለጸ።
ወባ፣ ኩፍኝ እና ኮሌራ በሽታዎች በተለያዩ የኦሮሚያ ዞኖች በወረርሽኝ መልክ በመከሰታቸው ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ የኦሮሚያ ጤና ቢሮ አሳስቧል።
ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የፀረ ወባ ኬሚካል ርጭት፣ የአጎበር ስርጭት፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች፣ የመድሃኒት አቅርቦትና የፀረ ኮሌራ ክትባት ስራ መካሄዱን የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አበራ ቦቶሬ ለኢብኮ ገልጸዋል።
የተመድ የሠብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት (ኦቻ) ሪፖርት መሰረት በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሦስት ወረዳዎች በሚገኙ 25 ቀበሌዎች እንዲሁም በሶማሌ ክልል በ2 ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ 9 ቀበሌዎች ኮሌራ መከሰቱን ገልጿል።
እስከ ጥቅምት 15 ቀን ባለው መረጃ መሰረት 9 ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ እስከ ጥቅምት 21 ድረስ የተጠቂዎች ቁጥር በፍጥነት መጨመሩንና በእነዚህ አከባቢዎች 334 ተጠቂዎች መገኘታቸውንም ሪፖርቱ ያሳያል።
የመጀመሪያው የኮሌራ በሽታ በዚህ ዓመት በባሌ ዞን ነሃሴ 21 መገኘቱን የሚጠቁመው ሪፖርቱ የስደተኛ መጠለያ የሚገኝባቸውን ጨምሮ 114 ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ 459 ሺ ሰዎችም አስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ተብሏል።
@tikvahethmagazine
30.1K viewsedited 12:02
2022-11-16 13:57:53
ከሳተላይቶች ጋር በኅብረት የምትሠራ ሌላ ሳተላይት ለማምጠቅ መታቀዱ ተገለጸ
ለመሬት ምልከታ የሚያገለግሉ ሳተላይቶችን ካመጠቀ ኩባንያ ጋር ውል በመግባት የኢትዮጵያን ሁለተኛ ሳተላይት አምጥቆ፣ በኅብረ ሳተላይት (satellite constellation) በጋራ መረጃ ለመሰብሰብ ማቀዱን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
ኢንስቲትዩቱ ከሌሎች ሳተላይቶች ጋር በኅብረት የምትሠራ የመሬት ምልከታ ሳተላይት በተያዘው የ2015 በጀት ዓመት ለማምመጠቅ ዕቅድ እንደያዘና ጨረታ ለማውጣትም በዝግጅት ላይ እንደሆነ፣ ዋና ዳይሬክተሩ አቶ አብዲሳ ይልማ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
ሁለተኛዋን ሳተላይት ለማምጠቅ የኢኮኖሚ አዋጭነት ጥናት ሲደረግ መቆየቱን ያስረዱት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ጥናቱ አንድ ሳተላይት ከማምጠቅ ይልቅ በኅብረ ሳተላይት (satellite constellation) ውሰጥ መግባት ተመራጭ እንደሚሆን ማመላከቱን ገልጸዋል፡፡
ኅብረ ሳተላይት ለአንድ ዓላማ ተልከው ምድርን የሚዞሩ ሳተላይቶች ስብስብ ሲሆን፣ ከአንድ የምድር አካባቢ መረጃ ለማግኘት አንድ ሳተላይት ዞሮ እስከሚመለስ ለመጠበቅ ሳያስፈልግ ተተኪ ሆኖ ያንን አካባቢ ከሚዞር ሌላ ሳተላይት መረጃ መቀበል ይቻላል፡፡
ኢትዮጵያ ያላትን 1.1 ሚሊዮን ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት በአንድ ሳተላይት መሸፈን እንደማይቻል፤ "በአዲስ አበባ ላይ አንዴ ብታልፍ መልሳ በአዲስ አበባ ላይ ለማለፍ ሌላ 20 ወይም 30 ቀን ይፈጃል" ሲሉም አስረድተዋል።
ለኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነችው ETRSS-1 የመሬት ምልከታ ሳተላይት የመጠቀችው ከሦስት ዓመት በፊት መምጠቋ ይታወሳል። ሳተላይቷ የተገመተላት የቆይታ ጊዜ ሁለት ዓመት ተኩል ቢሆንም ከታቀደላት ጊዜ 5 ወራትን ጨምራ እስካሁን እያገለገለች ነው ተብሏል፡፡
[ ሪፖርተር ]
@tikvahethmagazine
28.6K views10:57
2022-11-16 13:29:56
ዛሬ ጠዋት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ 1.5 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ወደመ
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር በጨፌ ቀጠና በተለምዶ መስቀልኛ መንገድ አጠገብ ባሉ ሶስት ሱቆች ላይ ነው የእሳት አደጋው የደረሰው ።
አደጋው የተከሰተው ከጠዋቱ 1:30 አካባቢ ሲሆን በአደጋው 1.5 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት የወደመ ሲሆን አንድ የህንጻ መሳሪያ መሸጫ ሱቅ ሙሉ በሙሉ ሲወድም ሁለት የንግድ ሱቆች በከፊል ተጎድተዋል።
አደጋዉን ለመቆጣጠር አንድ ሰዓት የፈጀ ሲሆን እሳቱ ተዛምቶ የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ በማድረግ 10 ሚሊየን ብር የተገመተ ንብረት ማዳን ሲቻል በሰዉ ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩንና መንስኤዉ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ የብስራት ሬድዮ ዘገባ ያሳያል።
@tikvahethmagazine
28.7K viewsedited 10:29
2022-11-16 12:07:53
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ የኤች አይቪ የስርጭት መጠን 3 ከመቶ መድረሱ ተገልጿል። ነአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና የከተማው ጤና ቢሮ በጋራ ባስጠኑት ጥናት በመዲናዋ 48 ወረዳዎች ላይ የቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
የቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ ከሆነባቸው ክፍለ ከተሞች መካከል አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በቀዳሚነት የተቀመጠ ሲሆን፣ አቃቂ ቃሊቲ፣ አራዳ እንዲሁም ቦሌ ክፍለ ከተሞች ላይ ስርጭቱ እያየለ ይገኛል ሲል ጤና ቢሮው አስታውቋል፡፡
ሴተኛ አዳሪዎች በከተማዋ መበራከታቸው ለስርጭቱ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚወስድ የተነገረ ሲሆን በሴተኛ አዳሪዎች የስርጭት መጠኑ 23 ከመቶ እንደሆነም ነው የተገለጸው፡፡ ከሴተኛ አዳሪዎች በተጨማሪም የህግ ታራሚዎች 4 ከመቶ የስርጭት መጠን እንደሚሸፍኑ ተነግሯል፡፡
ዘገባው የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ነው
@tikvahethmagazine
29.9K viewsedited 09:07
2022-11-16 11:55:31
የገንዘብ ሚኒስቴር የኢትዮቴሌኮም ከፊል ሽያጭ ሂደትን በድጋሚ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡
የኢትዮቴሌኮምን 40 በመቶ ድርሻ ለመሸጥ ዓለም አቀፍ ጨረታ ከዛሬ ጀምሮ እንደሚወጣ የገንዘብ ሚንስቴር አስታወቀ።
መንግስት የኢትዮቴሌኮምን 40 በመቶ ድርሻ ወደ ግል ለማዛወር አውጥቶት የነበረው ዓለም አቀፍ ጨረታ በአለም አቀፍ የኢኮኖሚ መቀዛቀዝና በአገር አቀፍ ደረጃም ምቹ ሁኔታ ስላልነበረ መቋረጡን ተነገሯል።
ዓለም አቀፍ ኩባንያን ለማስገባት ከዛሬ ጀምሮ ጨረታው ለቀጣይ ሶስት ሳምንታት እስከ ዲሴምበር 19 ቀን 2022 ክፍት ተደርጓል።
አሁን በተፈጠረው ስምምነት መሰረትና አለም አቀፋዊ ሁኔታውን ግምት ውስጥ በማስገባት ከሳፋሪኮም ቀጥሎ አንድ ተጨማሪ ኩባንያ ለማስገባት ጨረታ መውጣቱም የተገለጸ ሲሆን ለዚህም ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ አራት ሳምንታት ውይይት እንደሚኖር ታውቋል፡፡ (EPA, Captal)
@tikvahethmagazine
28.0K viewsedited 08:55
2022-11-16 11:55:22
ሎዛ የስነ ምግብ ማማከርና ህክምና ማዕከል
የላቀ እውቀት ባላቸው ሀኪሞችና የስነ ምግብ ባለሙያወች ሳንንሳዊና ተፈጥሯዊ በሆነ የምግብ ሥርዓት ጤናዎ እንዲስተካከል እንደርጋለን።
ይደውሉልን በ 0989300007 | 0993503136
በ Telegram: https://t.me/famwel21
26.2K viewsedited 08:55
2022-11-16 11:55:10
http://t.me/dunamisRM ሱፐር ዱናሚስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር
በጥሬ እቃ አስመጪነት ላይ ለተሰማራቹ ባለሀብቶች በጅቡቲ በቀጥታ መጫን ለምትፈልጉ ሁሉ አለምአቀፍ እውቅና ካላቸው ድርጅቶች ጋር ያገናኞታል።
ለፋብሪካዎ ጥሬ እቃ ይፈልጋሉ?
1. የፕላስቲክ ጥሬ እቃ
2.የተለያዩ ኬሚካሎች
3.የኢንዱስትሪ ግብአቶች
- PET RESIN - PARAFFIN OIL
- PP RAFFIA - POLYOL & TDI
- HDPE INJ. - DOP
- HDPE BLOW - COPOLYMER
- LDPE - HDPE FILM
- SOAP NOODLES & OTHER INDUSTRIAL RAW MATERIALS
Call - +251911428276 , +251902454776 , +251703008276
Join Us: http://t.me/dunamisRM
28.9K views08:55