Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-MAGAZINE

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethmagazine — TIKVAH-MAGAZINE
ርዕሶች ከሰርጥ:
Freeseminar
Cloudbridge
Traininginstitute
Cryptocurrency
Аирдроп
Tikvahtechteam
Techdailly
Attention
Cbdc
Cryptocurrencies
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethmagazine
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 196.76K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 256

2022-05-28 13:18:58
በደጀን ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት አለፈ።

በምስራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ከተማ አስተዳደር ዳሸን ስሚንቶ ፋብሪካ አካባቢ ግንቦት 19 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ አምስት ሰዓት አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአምስት ሰዎች ህይወት አልፏል።

አደጋው የተከሰተው የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 _A02900 ኢት ዋልያ የህዝብ ማመላለሻ ባስ ከደብረታቦር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በተቃራኒ አቅጣጫ ይጓዝ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3_ 09813 የህዝብ ሚኒባስ ጋር ፊት ለፊት በመጋጨቱ ነው።

በዚህም አንድ እግረኛን ሴት ጨምሮ ከባሱ አንድ ወንድ ህጻን፣ ከሚኒባሱ አሽከርካሪውን ጨምሮ 3 ወንድ በድምሩ በ5 ሰው የሞት አደጋ ተከስቷል።

ከአደጋው በኋላ 9 ሰዎች ወደ ደብረ ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል ሪፈር የተባሉ ሲሆን ሦስት ሰዎች ደግሞ በደጀን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ክትትል እየተደረገላቸው ነው ተብሏል።

መረጃው የምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
21.0K viewsedited  10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 13:18:39
ውብ በሆነ መልክ በመረጡት ፎቶ እና ጥቅስ በእንጨት እና ቆዳ ላይ በተለያየ ሳይዝ ለማሰራት ከፈለጉ በዚ 0927840730 ይዘዙ።
ዋጋ እና ለበለጠ መረጃ...
#share
#like
#join
@kiyaengraving
20.7K views10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 13:18:27
ብዙዎች ወስነዋል፣
ስኬታቸውን እያጣጣሙ ነው፣

አንተስ?
ዛሬውኑ ወስን፣ ልናግዝህ ተዘጋጅተናል...

ብልጥ ልጅ ያንተ አይነት ስኬታማ ኢትዮጲያዊያን ስኬታቸውን የሚያጣጥሙባቸውን በዱባይ የሚገኙ መኖሪያ ቤቶች ከተለያዩ የብድር አማራጮች ጋር ይዞ ቀርቧል!

መልክትህን ለመላክ:
ዌብ ሳይታችንን ጎብኝ: https://www.biltlij.com/
በቴሌግራም ለመነጋጋር: https://t.me/bilt_lij
በዋትስአፕ ለመነጋገር: https://wa.link/y2j9af
ወይም ለመደወል፡ +97152989 8575

ወደ ፌስቡክ አካውንታችን ለመሄድ፡ https://www.facebook.com/biltlij
የኢንስታግራም አካውንታችን፡ https://www.instagram.com/bilt.lij/
የቲክቶች ቻናላችንን ለማግኘት፡ https://www.tiktok.com/@bilt_lij
23.7K views10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 23:50:08 #የዛሬ (ግንቦት 19/2014)

እናት የፓርቲ 4 አመራሮቹ የገቡበትን ማወቅ እንዳልቻለ ገልጿል። ፓርቲው በአማራ ክልል መንግስት እየወሰደ ያለውን የሰሞኑን እርምጃ "አፈና" ሲል ገልጾ በዚህ ሂደት አመራሮቹ እንደታፈኑበት ገልጿል።

ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) ከፍተኛ አመራሩ አቶ ስንታየሁ ቸኮል በባህር ዳር ከተማ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል። ፓርቲው አመራሩ በአንደኛ ፖሊስ ጣቢያ መታሰሩን ነው ያመለከተው።

የ 'ፍትህ መጽሔት' ማኔጂግ ዳሪክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ " የሀገር መከላከያ ሰራዊትን በህዝብ ዘንድ አመኔታ ለማሳጣትና ሁከትና ብጥብጥ በማስነሳት ወንጀል " መጠርጠሩን መርማሪ ፖሊስ ዛሬ ለፍ/ቤት ገልጿል። የጋዜጠኛ ተመስገን ጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ በበኩሉ መከላከያን መተቸት እምነት ማሳጣት አለመሆኑን ጠቅሶ ተከራክሯል። ጉዳዩን የተከታተለው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎች የፖሊስ የምርመራ መዝገብ እንዲቀርብ በማዘዝ መርምሮ ትዛዝ ለመስጠት ለፊታችን ሰኞ ቀጥሯል።

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ላይ የ10 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል። ጋዜጠኛ ያየሰው የተጠረጠረው " ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል " መሆኑን መርማሪ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ገልጿል።

''እስካሁን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ ስም ብዙ ነገሮች ተችለዋል በአሁን ሰዓት ግን የለየለት የሽብር ስራ ፣ የሽብር ፈጠራ ፣ ሀገርን የማፍረስ ስራ ፣ ህግ የሌለ እስከማስመሰል ፣ የፍትህ ተቋማት እርምጃ መውሰድ አይችሉም የሚያስብል ደረጃ ላይ ደርሶ ሀገርን የማፍረስ ተልዕኮ ላይ እየሰሩ ያሉት አካላት ላይ የህግ የበላይነት ለማስከበር ከምን ጊዜውም በላይ የፌዴራል ፖሊስ ከሌሎች የፍትህ ተቋማት ጋር በመሆን የምርመራ ስራን እየሰራ ይገኛል።'' አቶ ሙሊሳ አብዲሳ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የኦፕሬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ

"የሚዲያ ባለሙያዎች መታሰራቸው ከመገናኛ ብዙሃን ህጉ ጋር የሚጻረርና መዘዙ ከመገናኛ ብዙሃን እና ሃሳብን ከመግለጽ የዘለለ በመሆኑ አሳሳቢ ነው" ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር

ከጥቂት ወራት በፊት ታስሮ ከእስር የተፈታው የቀድሞ የአውሎ ሚዲያ ባልደረባ አሁን ላይ " አልፋ ቲቪ " የተሰኘ የማህበራዊ ሚዲያ መስራች እና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር መዋሉን ጠበቃ ታደለ ገብረመድህንን ዋቢ አድርጎ አዲስ ስታንዳር አስነብቧል። የጋዜጠኛውን መታሰር ባለቤቱ ሄለን አባተ አረጋግጠዋል።

የፊንፊኔ ኢንተግሬትድ ብሮድካስቲንግ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኛ ሰቦንቱ አህመድ ትላንት በአዲስ አበባ ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን (በለቡ ፖሊስ ጣቢያ ነበረች) ዛሬ ወደ ቢሾፍቱ መወሰዷን የጣቢያው ዋና ዳይሬክተር ለሚ ታዬ ተናግረዋል።

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ እና የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሀመድ ወደ በሰኔ እና ሃምሌ ወር 2022 ወደ ሰሜን አሜሪካ እና አውሮፓ እንደሚጓዙ ታውቋል።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረችው ፅጌሬዳ ግርማይን በመግደል የተከሰሰው ተማሪ በ17 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ፍርድ ቤት ወሰነ። ፍርድ ቤቱ ዛሬ ግንቦት 19/2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹን በወንጀል ህግ ቁጥር 5391-ሀ ጥፋተኛ አድርጎታል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
4.6K viewsedited  20:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 23:20:08
#ትኩረት

በአንዳንድ አከባቢዎች ከሰሞኑ እየተስተዋለ ያለው ዝናብ መጠነኛ ጉዳቶችን እያደረሰ ይገኛል። መጪው የክረምት ወቅት በመሆኑ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በመስራትና የጥንቃቄ መልዕክቶችን በማድረስ የሚያስከትለውን ቀውስ መቀነስ ያሻል። በተለይ በደቡባዊው የሀገሪቱ ክፍል ከወዲሁ የጎርፍ አደጋዎች እየተስተዋሉ እንደሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ፎቶ:- ጋሞ ዞን ጨንቻ ዙሪያ ወረዳ፣ ስልጤ ዞን ሳንኩራ ወረዳ፣ ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
6.7K viewsedited  20:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 18:39:08
#UPDATE: ዜጎችን ከሳኡዲ አረቢያ የመመለስ ስራ ማከናወን ከተጀመረ ጀምሮ እስካሁን ቁጥራቸው ከ 29,122 በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉ ተገልጿል። በዛሬው ዕለትም በሦስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳኡዲ አረቢያ የመመለስ ስራ በአጠቃላይ ቁጥራቸው 1ሺህ 166 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ ተችሏል።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
18.6K viewsedited  15:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 18:38:53
የስራ ማግኛ ኦንላይን ፕላትፎርም /ሊንኮችህ/ ዝርዝር ለማግኘት

Join our telegram

https://t.me/+Zhm6yWqPh7U0N2E0
17.9K views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 17:02:09
በአርባምንጭ ከተማ አንድ እናት ሦስት ልጆችን በሰላም ተገላገለች።

በአርባምንጭ ድልፋና የመጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ክትትል ሲደረግላት የቆየች አንዲት እናት የሦስት ልጆችን በሰላም መገላገሏ ተገልጿል።

የሆስፒታሉ ዋና ሥራአስኪያጅ ዶ/ር ወንድሙ ጨርፋ እናት ድንገተኛ በተፈጠረ የምጥ መፋጠን ምክንያት የአንድ ወንድና የሁለት ሴት ልጆችን አቅራቢያቸዉ በሚገኘው ወዜ ጤና ጣቢያ መገለገቸውን ጠቁመዋል።

አሁን ላይ ለሕፃናቱ ተጨማሪ ክትትል ሲባል ወደ አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል መላኳንም ነው ዶ/ር ወንድሙ የገለጹት።

እናት ወ/ሮ ነፃነት ኩማ በአርባምንጭ ከተማ ልማት ቀበሌ የወዜ ቀጠና ነዋሪ ስትሆን ሌሎች 3 ልጆች እንዷላትና ከእነዚህ ጋር የ6 ልጆች እናት መሆንዋን ተናግራለች።

በተፈጥሮ ወሊድ (በምጥ) የሦስት ልጆች እናት መሆኗ ያስደሰታት እናት ወ/ሮ ነፃነት በተደረገላት የጤና ክትትልና ድጋፍ ምስጋናዋን አቅርባለች ሲል መረጃውን ያጋራው አርባምንጭ ከተማ ኮሚኒኬሽን ነው።

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
19.7K viewsedited  14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 16:57:33
በሀሰተኛ ገንዘብ ነዳጅ ቀድቶ ለማምለጥ የሞከረው አሽከርካሪ ህይወቱ አለፈ።

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው ሚካኤል አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ግንቦት 18 ቀን 2014 ዓ/ም ከሌሊቱ 6፡30 ሰዓት ገደማ በሀሰተኛ ገንዘብ ነዳጅ ቀድቶ ለማምለጥ የሞከረው አሽከርካሪ ከቆመ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ህይወቱ ማለፉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡

የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 1- 30262 አ.አ የሆነ ተሽከርካሪ ከጀሞ 1 አቅጣጫ ወደ ሚካኤል አደባባይ እየተጓዘ 67 ማዞሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ ነዳጅ ማደያ ውስጥ ነዳጅ ሊቀዳ መግባቱን በአዲስ አበባ ፖሊስ የትራፊክ አደጋ ምርመራ ቲም ሃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ስጦታው ወልዴ ገልፀዋል፡፡

አሽከርካሪው ነዳጅ ከቀዳ በኋላ አምስት ባለ 100 መቶ ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ለነዳጅ ማደያው ሰራተኛ ሰጥቶ በሚሄድበት ወቅት ነዳጅ ቀጂው የብሮቹን ትክክለኛነት በመጠራጠሩ ሊያስቆመው መሞከሩን ምክትል ኢንስፔክተር ስጦታው ጠቅሰዋል።

አሽከርካሪው ግን በፍጥነት በማሽከርከር ለማምለጥ ጥረት ሲያደርግ መንገድ ዳር ቆሞ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3A- 60203 አ.አ ከሆነ አይሱዙ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ህይወቱ ማለፉን ተናግረዋል፡፡

በወቅቱ አብረውት ተሳፍረው የነበሩ 2 ግለሰቦች ላይም ከባድ የአካል ጉዳት በመድረሱ ተጎጂዎቹ በህክምና ላይ እንደሚገኙ ምክትል ኢንስፔክተር ስጦታው ወልዴ አስረድተዋል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
18.4K viewsedited  13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-27 13:35:34
የደሴ ከተማ መናኸሪያ በደሴ ከተማ እንዲተዳደር ተወሰነ፡፡

በደቡብ ወሎ ዞን ትራንስፖርት መምሪያ ይተዳደር የነበረውን የደሴ ከተማ መናኸሪያ ለማሻሻል ለበርካታ ዓመታት የባለቤትነት ጥያቄ ሲያስነሳ የቆየው የደሴ ከተማ መናኸሪያ በደሴ ከተማ አስተዳደር እንዲመራ ውሳኔ ተላልፏል፡፡

''የህዝብ ጥያቄን በአመራር መገፋፋት ማስተጓጎል አይቻልም'' ሲሉ የደሴ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሣሙኤል ሞላልኝ ውሳኔው ይፋ በሆነበት ዕለት ተናግረዋል።

መናኸሪያው በከተማዋ ማሀል የሚገኝ ነገር ግን ጥራት የሌለውና የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ መቆየቱንም ጠቁመው የመናኸሪያው ጥገናና ማሻሻል በዚህ አመት ይጀመራል ብለዋል፡፡

@tikvahethmagazine @tikvahmagbot
24.1K viewsedited  10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ