Get Mystery Box with random crypto!

ሰሌዳ | Seleda

የቴሌግራም ቻናል አርማ seledadotio — ሰሌዳ | Seleda
የቴሌግራም ቻናል አርማ seledadotio — ሰሌዳ | Seleda
የሰርጥ አድራሻ: @seledadotio
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 50.47K
የሰርጥ መግለጫ

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
@seleda_support ለማንኛውም አይነት ጥያቄ

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-07-03 18:31:30
"ትልቅሰው ሪል እስቴት "
በመሃል ካዛንችስ እንደራሴ እጅግ ዘመናዊ  አፓርትመንቶችን እስከ ሰኔ 30 በማስተዋቂያ ዋጋ መሸጥ ጀምረናል ።
ትልቅ ሰው ሪል እስቴት
    የኔክሰስ ሆቴል
    የግራንድ ሆቴል
    የኢግል ፓክ ኢምፓርት ኤክስፓርት እና
    የስካይ ፔትሮሊየም እህት ኩባንያ ነው
ባለ 2 መኝታ
ባለ 3 መኝታ
የሚገርም ማራኪ እይታ ያላቸው !!!
ከአማራጭ አከፋፈል ጋር
100% በ1 አመት በ4ዙር
50/50 በባንክ

ለበለጠ መረጃ
@setu1988
0936606665
3.8K views15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 16:51:40
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 10ኛ ድሪም ላይነር አውሮፕላኑን መረከቡን አስታወቀ።

አየር መንገዱ በድረ ገጹ እንዳመለከተው Boeing 787-9 ድሪም ላይነር አውሮፕላኑ ከቦይንግ ኩባንያ ተረክቦ የዛሬ 3 ቀን አዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ደርሷል።

አዲሱ ድሪምላይነር አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን ወደ ዱባይ ማድረጉንም አየር መንገዱ አሳውቋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት ክፍሉ ለቻይና ብድር በመያዣነት ሊተላለፍ ነው የሚል ትችት በስፋት ቀርቦበት የነበረ ሲሆን አየርመንገዱ ግን ውንጀላውን "የሐሰት ወሬ" ሲል አስተባብሏል።
4.6K views13:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 16:05:11
ኢትዮጵያ ያለችበት ወቅታዊ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ የሰራተኞችን ጥያቄ ከመመለስ የሚያግድ እንዳልሆነ ኢሰማኮ አስታወቀ፡፡

ተቀጥረዉ በሚሰሩ ሰራተኞች በርካታ ኢኮኖሚያዊ ጫናዎች አሉባቸው በሚል በመንግስት በኩል ማስተካከያዎች እዲደረጉ  ጥያቄ ያቀረበው የሰራተኞች ማህበራት ኮንፌደሬሽን ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት የኢኮኖሚ ሁኔታ የሰራተኞችን ጥያቄ ከመመለስ የሚያግድ እዳልሆነ ለመናኸሪያ ሬድዮ አስታውቋል፡፡

ገንዘብ ሚኒስቴር ለ2016 የበጀት ዓመት ረቂቅ በጀቱን ይፋ ሲያደርግ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ቅጥርን ማስቀረት ጨምሮ ወጪ የሚቀንሱ እርምጃዎችን እንደሚወስድ ማስታወቁን ተከትሎ፤ በኮንፌደሬሽኑ የቀረቡ ጥያቄዎች የሚመለሱበት መንገድ ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል ወይ በሚል መናኸሪያ ሬዲዮ ለኮንፌደሬሽኑ ጥያቄ አቅርቧል፡፡ የኮንፌደሬሽኑ ፕሬዘዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ በዚህ ምክንያት መልስ ላያገኝ የማይችል ጥያቄ እንደሌለ ገልጸዋል፡፡

አቶ ካሳሁን አክለውም ከሰራተኞች የሚቆረጠው የገቢ ግብር እንዲቀነስ መጠየቁ መንግስት የሚያገኘው ገቢ ላይ በቀጥታ ተጽዕኖ ቢያሳድርም ጉድለቱን በሌሎች መንገዶች መሙላት ይችላል ብለዉ በዚህም የሰራተኞችን ጥያቄ ለመመለስ የበጀት ጉዳይ ምክንያት ሆኖ መቅረብ እንደሌለበት ጠቁመዋል፡፡
4.8K views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 15:42:54
ጣሊያናውያን በኑሮ ውድነት ሳቢያ ምግብ ለመቀነስ ተገደዋል ተባለ

ጣሊያናውያን ከፍተኛ ከሆነ የዋጋ ንረት የተነሳ የምግብ ፍጆታቸውን ለመቀነስ መገደዳቸውን አዲስ የወጣ ሪፖርት አመላክቷል።

የጣሊያን ኢንዱስትሪ ኮንፌዴሬሽን (ኮንፊንዱስትሪያ) ባወጣው ሪፖርት መሰረት እየጨመረ ያለው የዋጋ ንረት ጣሊያናውያን ቤተሰቦች ለምግብ የሚያወጡትን ወጪ እንዲቀንሱ እያደረጋቸው ነው ማለቱን አልአይን ፅፏል።

ሪፖርቱ የጣሊያናውያን ቤተሰቦች የምግብ ፍጆታ ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ መምጣቱን ያመላከተ ሲሆን፤ በፈረንጆቹ 2022 አራተኛ ሩብ ዓመት ላይ ብቻ የምግብ ወጪ ዋጋ በ8.7 በመቶ መቀነሱ ተመላክቷል።

የጣሊያን ብሔራዊ የሸማቾች ህብረት (ዩኤንሲ) ኃላፊ ማሲሚሊያኖ ዶና ሪፖርቱን ጣሊያናውያን መዋግ ንብረት ሳቢያ ምግብ ለመቀነስ መገደዳቸውን “አሳዛኝ” ሲሉ ገልጸዋል።
4.9K views12:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 14:02:57
የኤሌትሪክ መኪና አምራቹ ቴስላ የመኪና ሽያጩ ደርቶልኛል አለ

ግዙፉ የኤሌትሪክ መኪና አምራች ቴስላ ሽያጩን ለማሳደግ የዋጋ ቅናሽ ካደረገ በኋላ ባለፉት 3 ሶስት ወራት ከ450 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን መሸጡን አስታወቀ፡፡

ዋና ስራ አስፈጻሚው ኤሎን መስክን ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው የኩባንያው ሽያጭ ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረ ቢሆንም የጥሬ ዕቃ እና ግብአቶች ወጪ መናር ዓመታዊ ትርፉን በ24 በመቶ እንዲቀንስ አድርጎታል፡፡

ኤሎን መስክ ሌሎች ከፍተኛ የሚባሉት የመኪና አምራቾችም የዋጋ ቅናሽ ያደረጉ ቢሆንም ለቴስላ ኩባንያ ዘላቂነትና ውጤታማነት ግን ብዙ በመሸጥ ዝቅተኛ ትርፍ ማግኘት “የምንጊዜም ትክክለኛ ምርጫ” ነው ማለታቸውን የቢቢሲ ዘገባ አስረድቷል፡፡
5.4K viewsedited  11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 12:29:10
የፈረንሳይ አመፀኞች የ " ቮልስ ዋገን " ተሽከርካሪ ዘረፉ

በፈረንሳይ ሀገር አንድ የ17 ዓመት ታዳጊ በፖሊስ መገደለን ተከትሎ የተቀሰቀሰው አመፅ አሁንም ቀጥሏል። በዚሁ አመፅ በርካታ ተቋማት ተዘርፈዋል።

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በታዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች የአፕል፣ ዛራ፣ ናይክ የመሳሰሉ ትልልቅ ድርጅቶች ዘረፋ ሲፈፀምባቸው ታይቷል።

በተጨማሪም በማርሴ ከተማ አንድ  የ " ቮልስ ዋገን " ተሽከርካሪ መሸጫ በአመፀኞች ሲዘረፍ ታይቷል። በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተሰራጨ ተንቀሳቃሽ ምስል ፤ የመኪና መሸጫ ውስጥ የገቡ አመፀኞች አዳዲስ መኪናዎችን እያሽከረከሩ ሲወጡ ይታያል።

ከዚህ ባለፈ በፈረንሳይ አመፀኞች የቤት አስቤዛ በሚሸጥባቸው መደብሮች እየገቡ ዘይትን እና ሌሎች አስቤዛዎችን ዘርፈው ሲወጡ ታይተዋል።
5.8K views09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 10:41:57
“የልጄን ሕይወት በአንድ ሚሊዮን ብር ገዛሁ” - ልጃቸውን ከእገታ ያስለቀቁ አባት

ገንዘብ ለማግኘት ሲባል ስለሚፈጸሙ እገታዎች መስማት በተለይ በሀገራችን አስደንጋጭነቱ እየቀረ ይመስላል። ተደጋግሞ እየተከሰተ ቤተሰብ ያለውን ሁሉ በማሟጠጥ ከፍሎ ሲያስለቅቅ፣ በአጋቾች እጅ ወጥተው የቀሩ ሰዎችም አሉ።

ልጃቸው የታገተባቸው የምሥራቅ ጎጃሙ ጡረተኛ መምህር ቤታቸውን እንኳን ሸጠው የማይመልሱት ዕዳ ውስጥ በመግባት ልጃቸውን አስለቅቀዋል። እንዴት ልጃቸውን በእጃቸው እንዳስገቡ ሲያስገዱም “በአንድ ሚሊዮን ብር የልጄን ነፍስ ገዛሁ” ብለዋል ለቢቢሲ በሰጡት ቃል።
6.0K views07:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 10:02:50
ኢትዮጲያውያኑ አትሌቶች በዳይመንድ ሊጉ ድል ቀንቷቸዋል

ትላንት ምሽት በስቶኮልም በተደረገው የ1500 ሜትር የሴቶች ዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጲያውያኑ ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት አሸንፈዋል።

ፍሬወይኒ ኃይሉ ውድድሩን በ1ኛነት ያጠናቀቀች ሲሆን ድሪቤ ወልተጂ እና ሂሩት መሸሻ 2ኛ እና 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል።

በዚሁ በስቶኮልም በተደረገው የሴቶች 5 ሺህ ሜትር የሴቶች ውድድር ለምለም ኃይሉ እና መዲና ኢሳ 2ኛ እና 3ኛ በመሆን ገብተዋ።

መዲና ኢሳ የግሏን ሰዓት ማሻሻሏም ታውቋል። በዚህ ውድድር 1ኛ የወጣችው ቢያትሪስ ቼቤት መሆኗን አትሌትክስ አፍሪካ ዘግቧል።
6.1K views07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 09:44:42
የመቀሌው አይደር ሆስፒታል ሰራተኞቹ በውዝፍ የቤት ኪራይ መቸገራቸውን አስታወቀ፡፡

በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት በአይደር ሪፈራል ሆስፒታል ያገለግሉ የነበሩ የጤና ባለሙያዎች ለበርካታ ወራት ደሞዝ ስላልተከፈላቸው አሁን ላይ ውዝፍ የቤት ኪራይ ዕዳቸውን መክፈል አልቻሉም ተብሏል።

ሆስፒታሉ ታህሳስ 2015 የ ደሞዝ ክፍያ እስኪጀመር ድረስ ሰራተኞቹ ያለ ደሞዝ በመቆየታቸው ለተደራራቢ ችግር እንደተጋለጡ ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል።

ሆስፒታሉ የሰራተኞቹን ችግር ለመፍታት ለፌደራል መንግስቱ ጥያቄያ ቢያቀርብም መፍትሄ እንዳልተሰጠው የአይደር ሪፈራል ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር አብረሃ ገብረመድን ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።
6.1K views06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 14:12:13
በመዲናዋ የቤት እና የህንፃ ኪራይ እንጨምራል የሚሉ አከራዮች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ቢሮው አሳሰበ፡፡

በመዲናዋ በቅርቡ የጋራ መኖሪያ ቤት እና የህንፃ ባለንብረቶች የግብር ክፍያ መጀመሩን ተከትሎ አንዳንድ የህንፃ ባለቤቶች እና አከራዮች በተከራዮች ላይ ጭማሪ ለማድረግ ሙከራ እያደረጉ እንደሚገኙ መረጃው እንደደረሰው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ አስታውቋል። 

የከተማ ቦታና ቤት ግብር አከፋፈሉ የግልና የንግድ በሚል ልዩነት ቢኖረውም  የጋራ መኖሪያ ቤቶች ብቻ ሳይሆን በከተማ  ውስጥ ያሉ ከመኖሪያ እስከ  ህንጻዎች ድረስ ያሉ ቤቶችን በሙሉ የሚመለከት መሆኑንም ጠቅሷል።

የከተማ አስተዳደሩ ይህን ህግ ተግባራዊ ማድረግ የጀመረው በተጠና እና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ማዕከል ባደረገ መልኩ መሆኑን የገለፀው ቢሮው የቤት ኪራይ እንጨምራል የሚሉ አከራዮች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማሳሰቡን መናኸሪያ ሬዲዮ ዘግቧል፡፡
2.8K views11:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ