Get Mystery Box with random crypto!

ሰሌዳ | Seleda

የቴሌግራም ቻናል አርማ seledadotio — ሰሌዳ | Seleda
የቴሌግራም ቻናል አርማ seledadotio — ሰሌዳ | Seleda
የሰርጥ አድራሻ: @seledadotio
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 50.47K
የሰርጥ መግለጫ

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
@seleda_support ለማንኛውም አይነት ጥያቄ

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 150

2022-11-02 09:06:08
በሀገረ ብራዚል የተጧጧፈው አዲስ "የታማኝነት ፈተና" ስራ መነጋገሪያ ሆኗል

በብራዚል በማራኪ ሴቶች ባሎች ለትዳራቸው ምን ያህል ታማኝ ናቸው በሚል የተጀመረው አዲስ "የታማኝነት ፈተና" ስራ ከብራዚል አልፎ አለምን እያነጋገረ ይገኛል። የብራዚል ታማኝነት ተቆጣጣሪዎች (loyalty inspectors) እንደ ቲክ ቶክ እና ኢንስታግራም ባሉ ማህበራዊ የሚዲያ አውታሮች ተፈላጊነታቸው እየጨመረ መጥቷል።

ብዙውን ጊዜ ወጣት እና ማራኪ ሴቶች በመጠቀም ስራው የሚከናወን ሲሆን ባሎቻቸውን ለመፈተን የሚፈልጉ ሚስቶች ከ4 ዶላር እስከ 30 ዶላር መክፈል ይጠበቅባቸዋል። እነዚሁ የታማኝነት ተቆጣጣሪ ሴቶች በዋትስአፕ እና በሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ በኩል ወንዶቹን ማውራት ይጀምራሉ።

በንግግራቸው እና የተለዋወጡትን ፎቶዎች በማስረጃ በማያያዝ ለሚስቶች ያስረክባሉ። በዚሁ የታማኝነት ፈተና በቻይና በ2021 ዓመት ለመፈተን የሄደት አንዲት ግለሰብ ከተፈታኙ ጋር በፍቅር ወድቀው ከትዳር አጋሩ ጋር የተለያየበት አጋጣሚ ነበር።
6.8K views06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 08:09:41
ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበራት ወደ ባንክ ራሳቸውን እንዲያሳድጉ  ጥሪ አቀረበ።

ባንኩ ጥሪውን ያቀረበው በአለም አቀፍ ደረጃ ለ74ኛ ጊዜ ፤ በኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ እና በአዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር ለ5ኛ ጊዜ የገንዘብ ቁጠባና ብድር የህብረት ስራ ቀን "የቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበራት ለተጠናከረ የፋይናንስ አቅም" በሚል መሪ ቃል በተከበረበት ወቅት ነዉ።

ባለፉት አራት አመታት የፋይናንስ ዘርፉ በእጥፍ ቢያድግም ካለው ፍላጎት ጋር ተመጣጣኝ መሆን እንዳልቻለ የብሔራዊ ባንክ ም/ል ገዢ አቶ ሰለሞን ደስታ ተናግረዋል። ብሔራዊ ባንክ አካታች የፋይናንስ ስርአት ለመፍጠር ቁርጠኛ መሆኑን የገለጹት አቶ ሰለሞን የብሔራዊ ዲጂታል ክፍያ ስርአትን ጨምሮ ሌሎች ስትራቴጂዎችን ቀርጾ ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰዋል።

አቶ ሰለሞን አክለውም ማህበራቱ ወደ ባንክ እና ኢንሹራንስ የማደግ ፍላጎት ካላቸው በብሔራዊ ባንክ በኩል ለማስተናገድ ሙሉ ዝግጁነት መኖሩን አረጋግጠዋል። ፍላጎት ያላቸው ማህበራት ለብሔራዊ ባንክ ፍላጎታቸውን በመግለጽ እና መስፈርቶቹን በማሟላት ማደግ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።

ኢትዮ የንግድና ኢንቨስትመንት መድረክ
7.4K views05:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 18:28:03
አየር መንገዱ "ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ" ሽልማት 2022 ተሸላሚ ሆነ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህንን ሽልማት ከቢዝነስ ትራቭለር ሪደርስ አዋርድ ሲያገኝ ይህ ለተከታታይ ሦስተኛ ዓመት መሆኑን በይፉዊ የቲውተር ገጹ ባሰፈረው መልዕክት አስታውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመስከረም ወር 2015 በለንደን SKYTRAX 2022 የአለም ምርጥ አየር መንገዶች ሽልማት ላይ ለተከታታይ አምስተኛ ጊዜ ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ በመባል መሸለሙ ይታወሳል። በዚሁ SKYTRAX ምርጥ የአለማችን 100 አየር መንገዶች ዝርዝር ውስጥም አስራ አንድ ደረጃዎችን በማሻሻል 26ተኛ ደረጃ ላይ ለመቀመጥ መቻሉ ተገልጿል።
7.7K views15:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 17:14:21
#Admass_digital_lottery

አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ወጣ።

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የአድማስ  ድጅታል ሎተሪ በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር በቀጥታ ስርጭት በይፋ ወጥቷል ፡፡ የወጡ ዕድለኛ የሚያደርጉ ቁጥሮች ከላይ ተያይዟል።
7.6K views14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 16:49:57
ከገበሬው የምርት ስርጭት አገልግሎት ተጀመረ።

ፐርፐዝ ብላክ ኢትኤች ትሬዲን ከገበሬው የምርት ስርጭት አገልግሎት በዛሬው እለት አስጀምሯል፡፡ የፕሮጀክት ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ሰናይት አየለ ለኢትዮ የንግድ እና ኢንቨስትመንት መድረክ እንደተናገሩት ከገበሬው ምርት ስርጭት አገልግሎት በዋናነት የግብርና ምርቶችን ከገበሬው በቀጥታ ወደ ሸማች ቤት ለቤት አቅርቦትን ጨምሮ የሚያካትት ነው፡፡

በዚህ ፕሮጀክት ሸማቾች የአባልነት ቅጽ በመሙላት በቋሚነት ተጠቃሚ የሚሆኑበት በፈለጉት መጠን ምርት የሚያገኙበት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም የኢንዱስትሪ ምርቶችም በዚሁ ስርአት ለሸማቹ ይቀርባሉ ብለዋል፡፡ በሁሉም የአዲስ አበባ ክ/ከተሞች ይህን ግብይት የሚመሩ ሀላፊዎች መመደባቸውን እና መዋቅሩም እስከ ወረዳ የተደራጀ መሆኑን ወ/ሮ ሰናይት ተናግረዋል፡፡

በሶስት ቀናት ውስጥ ብቻ ከ1400 በላይ ሰዎች የሸማች አባልነት ቅጽ መሙላታቸው የተገለጸ ሲሆን ከ1000 በላይ ዜጎችም በኤጀንትነት የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል፡፡ የክፍያ ስርአቱም በሞባይል ባንኪንግ ፤ በባንክ ፤ በቴሌብር እና እጅ በእጅ ይሆናል፡፡ ፕሮጀክቱን ወደፊት በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማስፋት እና በዱቤ ለመስጠት መታቀዱን ወ/ሮ ሰናይት አስረድተዋል፡፡

ኢትዮ የንግድና ኢንቨስትመንት መድረክ
7.2K views13:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 16:04:00
ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር በመጀመሪያ ሩብ ዓመት 377.4 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር በ2015 የመጀመሪያው ሩብ የበጀት ዓመት ዘጠኝ የሎተሪ ዓይነቶችን ለገበያ በማቅረብና ከዕድል ጨዋታ ኮሚሽን 377.4 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ለአዲስ ማለዳ አስታውቋል። በሦስት ወራት ውስጥ ዘጠኝ የሎተሪ ዓይነቶችን ለገበያ በማቅረብና ከዕድል ጨዋታ ኮሚሽን ለማግኘት ከታቀደው 91.6 በመቶውን ማሳካት ተችሏል።

በዚህም አስተዳደሩ በአጠቃላይ የተጣራ 136.1 ሚሊዮን ብር ትርፍ ያገኘ ሲሆን፣  በሩብ ዓመቱ የእቅዱን 148 በመቶ ማሳካት እንደተቻለ አሳውቋል። ይህ የገቢና የትርፍ መጠን ብሔራዊ ሎተሪ በሩብ በጀት ዓመቱ ለሽያጭ ባቀረባቸው ዘጠኝ የሎተሪ አይነቶችና ከዕድል ጨዋታዎች ኮሚሽን በሚያገኘው ገቢ ሲሆን፣ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር አዲስ ያስጀመረውን አድማስ የአጭር መልዕክት የሞባይል ሎተሪ የተገኘውን ገቢ አያካትትም።

ከአድማስ ሎተሪ ከሚገኘው ገቢ 25 በመቶውን ኢትዮ ቴሌኮም 75 በመቶውን ደግሞ ብሔራዊ የሎተሪ አስተዳድር የሚወስድ ሲሆን፣ ከፋይናንስ ጋር ያሉ የሲስተም ሥራዎች ባለመጠናቀቃቸው በዚህ ሩብ የበጀት ዓመት ከአድማስ ሎተሪ የተገኘውን ገቢና ትርፍ ለመናገር እንደማይቻል ተነግሯል።
7.0K views13:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ