ኢትዮጲያውያኑ አትሌቶች በዳይመንድ ሊጉ ድል ቀንቷቸዋል
ትላንት ምሽት በስቶኮልም በተደረገው የ1500 ሜትር የሴቶች ዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጲያውያኑ ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት አሸንፈዋል።
ፍሬወይኒ ኃይሉ ውድድሩን በ1ኛነት ያጠናቀቀች ሲሆን ድሪቤ ወልተጂ እና ሂሩት መሸሻ 2ኛ እና 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል።
በዚሁ በስቶኮልም በተደረገው የሴቶች 5 ሺህ ሜትር የሴቶች ውድድር ለምለም ኃይሉ እና መዲና ኢሳ 2ኛ እና 3ኛ በመሆን ገብተዋ።
መዲና ኢሳ የግሏን ሰዓት ማሻሻሏም ታውቋል። በዚህ ውድድር 1ኛ የወጣችው ቢያትሪስ ቼቤት መሆኗን አትሌትክስ አፍሪካ ዘግቧል።