የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
196.23K
የሰርጥ መግለጫ
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን 251913134524
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
1
3 stars
1
2 stars
0
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 164
2022-12-06 11:53:52
በውርስ ከተያዙ ተሽከርካሪዎች ላይ ሰሌዳ እየፈታ ለህገ-ወጥ ተግባር ሲያከራይ የነበረ ግለሰብ ተያዘ።
የድሬዳዋ ቅርንጫፍ የጉምሩክ የውርስ መጋዘን ፀሀፊ የነበረው በውርስ ከተያዙ ተሽከርካሪዎች ሰሌዳ እየፈታ ለህገ-ወጥ ተግባር ሲገለገልበት እጅ ከፍንጅ መያዙን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገለጸ፡፡
ተጠርጣሪው ወንጀሉን የፈፀመው የድሬዳዋ ቅርንጫፍ የጉምሩክ የውርስ መጋዘን ፀሀፊ ሆኖ እየሰራ ባለበት በሥራ አጋጣሚ በውርስ ከተያዙ ተሽከርካሪዎች ሠሌደ ቁጥር እየፈታ ለደላሎችና በዚህ ህገ-ወጥ ተግባር ላይ ለተሰማሩ ሰዎች በ15 ሺህ ብር ያከራያል።
ሰሌዳውን የሚከራዩት ግለሰቦች ይህንን ሰሌዳ ቁጥር እየተጠቀሙ ከሶማሌ ላንድ ሠነድ አልባ ተሽከርካሪዎችን በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ሲያደርጉ እንደነበር ተገልጿል፡፡
ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር የዋለው 15 ሺህ ብር ተቀብሎ በውርስ ከተያዘ ተሸከርካሪ ሠሌዳ ፈቶ ሲሰጥ በድሬዳዋ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ እጅ ከፈንጅ ተይዞ ፖሊስ ምርመራ እያጣራበት እንደሆነ ከፌደራል ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
@tikvahethmagazine
21.7K views08:53
2022-12-06 11:49:25
"በኢትዮጵያ ላላው ድርቅ ምላሽ ለመስጠት ከጠየቅነው ገንዘብ ውስጥ ያገኘነው 14% ብቻ ነው" - ፋኦ
በኢትዮጵያ በድርቅ በተጠቁ አካባቢዎች የሚገኙ 10 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው የተባበሩት መንግስታት የምግብና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ) አስታውቋል።
ፋኦ በመግለጫው የሶማሌ፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ እና የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች በከፍተኛ ሁኔታ የተጠቁ አካባቢዎች ናቸው ብሏል።
የሶማሌ ክልልን የጎበኙት የድርጅቱ የአስቸኳይ ግዜ ዕርዳታ ሃላፊ የሆኑት ሬይን ፖልሰን የድርቁን ከፍተኛ አሳሳቢነት አንስተው፣ የተሻለ የአስቸኳይ ግዜ ምላሽ ያስፈልጋል ብለዋል።
ኃላፊው አክለው ለረድኤት ሥራዎች ዋናው ጋሬጣ የሆነው የገንዘብ በበቂ አለመገኘት ሲሆን፣ ፋኦ በኢትዮጵያ ላላው ድርቅ ምላሽ ለመስጠት ከጠየቀው ውስጥ ያገኘው 14 በመቶውን ብቻ እንደሆነ ጠቁመዋል።
በሶማሌ ክልል ብቻ 691 ሺህ 500 የሚሆኑ ሰዎችን በህይወት አድን ዕርዳታ መታደጉን የገለጸው ድርጅቱ፣ በያዝነው የፈረንጆች ዓመት በኢትዮጵያ 7.5 ሚሊዮን ሰዎችን መርዳቱን አመልክቷል። (VOA Amharic)
@tikvahethmagazine
18.9K viewsedited 08:49
2022-12-06 11:45:01
የሰው ነብስ አጥፍቶ ለ18 ዓመት ከህግ ተሠውሮ የቆየው ግለሰብ...
ጌታወንድፍሬ አበባው የተባለው ግለሰብ ግንቦት 7/1997 ዓ.ም በመቅደላ ወረዳ ኮሬብ 023 ቀበሌ ላይ ሟች ይብሬ ሙሀመድ የተባለውን ግለሰብ በቂም በቀል ተነሣሥቶ በዱላ በመደብደብና ህይወቱን በማጥፋት ከአካባቢው ተሰውሮ ለ18 ዓመት ከኖረ በኀላ ህዳር 16 ቀን 2015 ዓ.ም በጋምቤላ ክልል ሜጅንግ ዞን ጎደሬ ወረዳ ላይ በቁጥጥር ሥር ውሏል።
የመቅደላ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤትም ፖሊሶችን ወደ ቦታዉ በመላክ ህዳር 26/2015 ዓ.ም ወንጀሉን ወደ ፈፀመበት መቅደላ ወረዳ በማምጣት በቁጥጥር ስር ማድረጉን ከወረዳው ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@tikvahethmagazine
18.2K viewsedited 08:45
2022-12-06 11:43:47
በህገወጥ የማዕድን ዝዉዉር የተጠረጠሩ ግለሰቦችና ቁሳቁሶች በቁጥጥር ስር ዋሉ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ምዕራብ ህዝቦች ክልል ኦሞ ዞን ቤሮ ወረዳ በተደረገዉ ድንገተኛ ፍተሻ የተለያዩ ማዕድን ዉጤቶችና መሳሪያዎች መገኘቱ ተገልጿል።
በዚሁ መሠረት 2,260(ሁለት ሺ ሁለት መቶ ስልሳ) ግራም ወርቅ፣ 3 የወርቅ መጠቆሚያ ማሽን ፣2 ክላሽ 1 ሽጉጥ ከ76 መሠል ጥይቶችና 2,129,100(ሁለት ሚሊዬን አንድ መቶ ሀያ ዘጠኝ ሺ አንድ መቶ ብር) በፖሊስ በቁጥጥር ስር ዉሏል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 21 ሠዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ በመጣራት ላይ የሚገኝ ሲሆን የህግ ማስከበሩ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
@tikvahethmagazine
17.7K views08:43
2022-12-06 11:43:21
- በሪል ስቴት ልማት
- በሆቴልና ቱሪዝም
- በትምህርት ኢንቨስትመንት
- በማርብል፣ ጠጠርና ኮንስትራክሽን ግብአቶች ምርት ኢንዱስትሪዎች
- በእንጨት፣ ብረታብረትና አልሙኒየም ውጤቶች ምርት ስራ
- እንዲሁም በሌሎች ፋይናንሻል ኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ የተሰማራውና ሶስት አስርት ዓመታትን በትርፋማነቱ የዘለቀው አያት አክስዮን ማህበር ለሽያጭ ያቀረባቸውን ጥቂት አክስዮኖች እንዲገዙና እስከ 44% የደረሰው ትርፋን እንዲጋሩ ጋብዝዎታል!
አሁኑኑ ይደውሉ
0930653333
አያትን የሰማ ትርፋማ!
18.7K views08:43
2022-12-06 11:43:15
ለመኖርያ ቤት ለቢሮ ለንግድ ቦታዎ ውብ እና ማራኪ የሆኑ ዲዛይኖችን በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ካለው የፊኒሺንግ ስራ ጋር ሰርተን እናስረክቦታለን። ይደውሉልን።
የምንሰጣቸው አገልግሎት
የኢንቴርየር ዲዛይን እና የፊኒሺንግ ስራ
አርቴክቸራል ዲዛይን
የኢፓክሲ ስራ ( Epoxy Work )
የእንጨት ፓርቲሽኖችን መስራት
አጠቃላይ የእንጨት ስራ
ብራንዲንግ
Contact us @etheldesign1
0939902740
0919361804
Join Telegram: t.me/etheldesign
20.5K views08:43
2022-12-05 21:09:24
ለህንፃ ግንባታ በተቆፈረ ጉድጓድ ምክንያት አለት ተደርምሶ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ
በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 08 ልዩ ስሙ 31አምሳ ቆርቆሮ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ ዋልያ ኮንስትራክሽን በሚያስቆፍረው የህንፃ መሰረት ድንገት አለት ተደርምሶ የአንድ ግለሰብ ህይወት አልፏል።
የመደርመስ አደጋው የደረሰው ዛሬ ረፋድ 4:30 አካባቢ ሲሆን፤ ህይወቱ ያለፈው ግለሰብ ታማሚና ከቤት ወጥቶ የማያውቅ እንዲሁም በሰዓቱ ምንም አይነት የቁፋሮ ስራ አለመኖሩ ተጠቁሟል።
ሆኖም ስጋት ስለነበረ በአካቢው የሚኖሩ ሰዎች እንዲነሱ በሚደረግበት ወቅት አደጋው መድረሱ ተገልጿል። የሟች አስከሬን የእሳት አደጋ ሰራተኞች ከፍርስራሽ ውስጥ በማውጣት ለአዲስ አበባ ፖሊስ ያስረከቡ ሲሆን፤ ወደ ሚኒልክ ሆስፒታል መሸኘቱን ወረዳው አስታውቋል።
@tikvahethmagazine
15.8K views18:09
2022-12-05 20:33:52
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለ100 የልብ ሕሙማን ሕጻናት ቀዶ ጥገና ወደሚያደርጉበት ሀገር ደርሰው የሚመለሱበትን ሙሉ የትራንስፖርት ወጪ እንደሚሸፍን አስታወቀ፡፡
በዛሬው ዕለትም አየር መንገዱ ለመጀመሪያ አራት ተጓዦች ሽኝት የተደረገላቸው ሲሆን በሽኝቱ ወቅትም የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦርድ ሰብሳቢ ግርማ ዋቄ በሽኝቱ ላይ እንደተናገሩት÷ ሕጻናትን ማዳን ግዴታችን ነው ብለዋል፡፡
በውጭው ሀገር የሚታከሙትን ሕጻናት የቆይታ እና የሕክምና ወጪ ደግሞ ሮተሪ ኢትዮጵያ እንደሚሸፍን ተገልጿል፡፡(FBC)
@tikvahethmagazine
18.7K viewsedited 17:33
2022-12-05 14:03:57
1ሺህ 167 ኢትዮጵያውያን ወንዶች ከሳኡዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል
በዛሬው ዕለት በሶስት ዙር በተከናወነ በረራ በሳኡዲ አረቢያ በችግር ያሉ ዜጎችን የመመለስ ስራ 1ሺህ 167 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ ተችሏል።
በዛሬው እለት ወደ ሀገር ከተመለሱ ዜጎች መካከል 1ሺህ 165 ወንዶች ሲሆኑ 2 ደግሞ እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ናቸው ተብሏል፡፡
ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማእከላት እንዲሄዱ መደረጉም ተገልጿል።
ከህዳር 12 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን በተከናወነ ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ 7968 ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉን ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
@tikvahethmagazine
14.7K viewsedited 11:03