አዕምሮህን አሰልጥን!
አነቃቂ ንግግር ባትሰማ፣ አነቃቂ ፅሁፍ ባታነብ፣ አይዞህ በርታ የሚልህ ሰው ባታገኝ፣ ከጎንህ የሚቆም አጋዥ ባታገኝ ህይወትህን ሙሉ በሙሉ በእራስህ አነቃቂነትና በችግሮችህ አስገዳጅነት የምትቀይረው ይመስልሃል? ሁሌም ንቁ አትሆንም፤ ሁሌም ዝግጁ አትሆንም። ነገር ግን ከምንም በላይ ንቁና ዝግጁ የሚያደርግህን ተግባር በመፈፀም ንቃትን መላበስና ዝግጁ መሆን ትችላለህ። ያለህበት የገንዘብ እጦት የሚጠበቅብህን ሁሉ እንድታደርግ ካላነሳሳህ አንድ አነቃቂ ንግግር ወይም ፅሁፍ ሊያነቃና ሊያነሳሳህ አይችልም። አንተ ካለህበት ሁኔታ በተሻለ ጠንካራ ሰው እንድትሆን የሚያደርግህ ነገር የለም። የህመምህን ስሜት ታውቀዋለህ፤ የማጣት ስቃይ ደርሶብሃል፤ የመናቅ፣ የመገፋት ሃፍረት አጋጥሞሃል። በሌለህ ነገር መለካት ምንያክል እንደሚያም ታውቀዋለህ።
አዎ! ጀግናዬ..! አዕምሮህን አሰልጥን! እራስህ ላይ ሰልጥን፤ ማንነትህ ላይ ንገስ። ማድረግ ያለብህን ለማድረግ፣ መገኘት የሚገባህ ቦታ ለመገኘት ቆራጥ ሁን። ማመንታት የስኬትህ ጠላት ነው። መወሰን ባለብህ ነገር ላይ በፍጥነት ወስን። ህልምህን ለመኖር ብዙ ያልተሟሉ ነገሮች ይኖራሉ፤ ነገር ግን አዕምሮህን ካሰለጠንክ፣ ማንነትህን ከህልምህ ጋር ካዋሃድክ፣ በአዎንታዊ አመለካከት ከተሞላህ ባለህ ነገር ህልምህን መኖር ትችላለህ። ስልጡን አዕምሮ አነቃቂ (motivation) አይጠብቅም፤ ህልመኛ ማንነት ሰበብ (excuse) አያበዛም፤ አዎንታዊ ስብዕና የአላማውን መሰናክሎች (obstacles) አይቆጥርም። ወደፊት የምትሔደው ሲመችህና የሚገፋህ ስታገኝ ብቻ አይደለም፤ ጉዞህን የምትቀጥለው አበረታች ድጋፍ ስታገኝ ብቻ አይደለም።
አዎ! ማድረግ ላለብህ ነገር የሚያስፈልግህ ምክንያት ሳይሆን ምግባር ነው። እያስጠላህ ጠንክሮ የመስራት ምግባር፤ እየታመምክ እስከጥግ የመታገል ምግባር፤ በማጣት ውስጥ የመፍጨርጨር ምግባር፣ እየተገፉ፣ እየተጠሉ፣ እየተሰደቡና እየተተቹ ህልምን የመኖር ምግባር። ማንም ቢሆን ሰው የሚያወጣው አዕምሮው ውስጥ ያለውን ሃሳብ እንጂ አንተን የሚገልፀውን ነገር አይደለም። እንደምታስጠላ ሲናገር እራሱን እየሰደበ እንደሆነ አይረዳም፤ አትችልም ሲልህ ለእራሱ እንደማይችል እያረጋጋጠ መሆኑ አይገባውም። የምትባለውን እንዳልሆንክ አምነህ ለእራስህ በሰጠሀው ልክ መጓዝም እራሱን የቻለ አንድ ትልቅ ምግባር ነው። በህልሙ ጉዳይ ከማንም የማይደራደር፣ ለራዕይው እውንነት ምንም ምክንያት የማያቀርብ፣ አላማውን ለማሳካት ማንንም የማይጠብቅ መሪ የሆነ ስልጡን አዕምሮ አለህ። በምንም ሁኔታ እንዲረበሽና በአሉታዊ አስተሳሰብ እንዲመረዝ አትፍቀድ። ስልጡኑን አዕምሮ ተጠቅመህ በምትፈልገው መንገድ፣ የምትፈልገውን ህይወት ኑር።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q