2023-01-31 01:53:26
18 40 60 መርህ!
18 40 60 Principle!
በአስራ ስምንት ዓመትህ ሰዎች ሁሉ ስላንተ የሚያወሩ ፣ አንተን ብቻ የሚመለከቱ ፣ የሚከታተሉህ ፣ የዘወትር ጉዳያቸው አንተ እንደሆንክ ታስባለህ ። በዚህም ልክ ከእራስህ በላይ ሰዎች ስለሚሰጡህ ስምና ከእነርሱ ስለምታገኘው ምላሽ በመጨነቅ ጊዜህን ታባክናለህ ፤ እራስህን ከማስደሰት በላይ ለሰዎች ደስታና እርካታ ትልቅ ዋጋ ትከፍላለህ፤ ሰው ምን ይለኛል በሚል ሃፍረት ትታሰራለህ ፤ ነፃነትህን ለማወጅ ባሰብክ ቁጥር የሰው ምላስ ከፊትህ ተደቅኖ ትመለከታለህ ፤ ባጠቃላይ ህይወትህ በሙሉ ለሰዎች በሚከፈል መሱዓትነት ይሞላል ። በአርባ ዓመትህ የሰው ነገር ምንም አይመስልህም ፤ ምንም ብትባል ግድ አይሰጥህም ፤ ስለፈለጉት ቢያወሩብህ ፣ ስምህን ቢያጠፉ ፣ ስራህን ቢተቹ ፣ አንተን ቢነቅፉህ ምርጫቸው እንደሆነ ይገባሃል ። በቀደሙት አመታት ሲያስጨንቁህ የነበሩ ጉዳዮች ማስጨነቃቸውን ያቆማሉ ፤ ሌላ የተለየ አጀንዳ ውስጥ ትገባለህ ። በስልሳ ዓመትህ የሁለቱንም ልዩነት ማመዛዘን ትጀምራለህ ፤ ለሰዎች ብለህ ያጣሀው ነገር ካለ በእርሱ ትቆጫለህ ፤ ማንም ግድ በማይሰጠው ጉዳይ ስትጨነቅ እንደነበር ታስተውላለህ ፤ የሰዎች ስጋትና ፍራቻ ሁሉ የውሸት እንደነበር ይገባሃል ።
አዎ! ጀግናዬ..!
መርሁን አስተውል ፤ በሚገባ ተረዳው ። ብዙዎች ስላላወቁት ይሸወዳሉ አንተ ግን ካወከው ዘንዳ ፣ ከተረዳሀው ፣ ከገባህ ለመተግበር ወደኋላ አትበል ። ማንም ሰው ግድ ለማይሰጠው ጉዳይ እየፈራህና እየተጨነክ አትኑር ። ያዩኛል ፣ ይከታተሉኛል ፣ ይተቹኛል ፣ ምን ይሉኛል ብለህ የምትጨነቅላቸው ሰዎች በሙሉ የእራሳቸው የማያልቅ ጉዳይ አለባቸው ። ማንም ያንተ አዲስ ነገር መጀመር ፣ በተለየ መንገድ መጓዝ ፣ በአዲስ አቋም መታደስ አያሳስበውም ። ሁሉም የግሉ ሩጫ ላይ ነው ። ምናልባት በአጋጣሚ ሲያይህ የመጣበትን ቃል ሊሰነዝርብህ ይችላል ከዛ ቦሃላ ግን ትዝም አትለውም ። እያንዳንዱ ሰው በግል ጡዘት በተጠመደበት ጊዜ አይኖች ሁሉ እኔ ላይ ናቸው ብለህ አትሸወድ ።
አዎ! ሰበብ አታብዛ ደስታ የሚሰጥህን ፣ ያመንክበትን ፣ የሚጠቅምህን ነገር በጊዜ አድርግ ። ህይወትህን በፍረሃት አትሰራት ፤ መኖርን በማይሆን ገደብ አትከልላት ። በትንሹም ቢሆን ጥረትህን ጀምር ፤ ደስታህን ወደ መፍጠር ተሸጋገር ፤ የእራስህን አለም አበጃጅ ፤ ፈጣሪህ ያይሃል ፤ አምላክ ያውቅልሃል ፤ ይረዳሃል ፤ ይቀድምልሃል ። ስለመጪው ጊዜ ቁጪትና ብትስጪት የምትጨነቅበት ምክንያት የለህም ። በአጋጣሚ ያገኘህና የተመለከተህ ባላወቀህ መጠን ሊናገር ይችላል ፤ አስቦና ፈልጎ የሚመለከትህ ግን በእርግጥም ሊደግፍህ እንደሚመጣ አትጠራጠር ። ልዩነት መፍጠሩን አሁኑኑ ጀምር ፤ በልብህ የያዝከውን ፣ በአዕምሮህ ያነገብከውን ሃሳባዊ አለም ከምድራዊው ተጨባጭ አለም ጋር ቀላቅለው ። የመጣው ይምጣ ፤ የሆነው ይሁን ፤ የማይቀር ነገር እንደሆነ የመጣውን ተቀበል ። በእራስህ ተመማመን ፤ ለእራስህ ብለህ ድፈር ፤ ጠንክር ፤ ለእራስህ ብለህ ህይወትህን በሙላት ኑር ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
4.1K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited 22:53