Get Mystery Box with random crypto!

ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️

የቴሌግራም ቻናል አርማ mirttshefoch — ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️
የቴሌግራም ቻናል አርማ mirttshefoch — ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️
የሰርጥ አድራሻ: @mirttshefoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 31.94K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 33

2023-02-06 06:04:41
ማንም ሰው በሀይማኖቱ ምክንያት #መሞት የለበትም ። #ሀይማኖት የሁሉም ደካማ ጎን ነው ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታይ የሆናችሁ #ወገኖቼ በሙሉ የመጣብንን ችግር አልፈን መልካም ጊዜ እንዲመጣልን ልባዊ ምኞቴ ነው #_ሀገራችንን_ፈጣሪ_ሰላም_ያድርግልን
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
678 viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  03:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 20:07:43 አምላክህ ማነው?

ሁሉም ሰው እንደ አቅሙ ንብረት አለው ፣ ሀብት አለው ፣ ስም አለው ፣ ዝና አለው ፣ ታሪክ አለው ፣ ዘር አለው ፣ ብሔር አለው ። ከዚህ ሁሉ አምላኩ ፣ ገዢውና ጌታው የሆነ ፣ ከመዓቱ የሚያድነው ፣ ከህመሙ የሚፈውሰው ፣ ከለምፁ የሚያነፃው ፣ ከችግሩ የሚያወጣው ፣ ነፍሱን የሚያሳርፍለት ፣ መረጋጋትን የሚድለው ከፈጣሪው ውጪ አንዳች ነገር የለም ። በምድራዊ ህይወትህ ብዙ የሚያስመካህ ነገር ሊኖርህ ይችላል አምላክን እንደ አምላክ ካለስቀደምክና ካልተደገፍከው ግን ወዳቂ ነህ ። ማንም ምንም ከምድር መፈጠር በፊት ከነበረ ፣ ከምድር ማለፍ ቦሃላም ከሚኖር ዘላለማዊ ህያው አምላክ የሚበልጥ ነገር የለም ። ብታከብረው ትከበራለህ ፤ በስሙ ብትነግድ ፣ ሽፋን አድርገሀው ብትበድል ፣ የግል አቋምህን ብታራምድ ፣ ጥላቻህን ብታሳብቅ ከሁሉ ቀድመህ የምትጠፋው አንተ ነህ ። ሁሉንቻይ ፈጣሪ ሁሉን ይችላል ፤ ሲቆጣ ግን ሁሉ ነገርህን ያጠፋዋል ።

አዎ! ጀግናዬ..! አምላክህ ማነው ? ህያው የአለም ፈጣሪ ቅዱስ እግዚአብሔር (አላህ) ወይስ ምድራዊ ታፔላና ስም ? አልፋና ኦሜጋ ቸር አምላክ ወይስ ዘር ፣ ቋንቋና ብሔርህ ? ሩህሩህ ጌታ ወይስ ምድራዊ ንብረት ፣ ዝናና ስልጣን? የምታመልከውን እወቀው ፣ ከልብህ ምረጥ ። ግልፅና ግልፅ እውነታ አለ ከእምነት ውጪ ሌላው ትርፍ ነው ፤ ምድር ላይ የሚቀር ፣ ጥለሀው የምትሔደው ፣ ነገ ሌላው የሚረከበው ፣ ስምህን እንኳን የማያስታውስ ነው ። ህያው የሚያደርግህ አምላክ አለህ ፤ የሚፈውስህ ፅኑ ቃል አለህ ፤ የምትድንበት ፣ በቀኙ የሚያቆምህ ፣ የፅድቅን በር የሚከፍትልህ ብርቱ ምግባር አለህ ። ህግጋት ይገዙሃል ፤ ህሊናህ ግን ይሰራሃል ። ውስጥህ የሚመላለስ የማስተዋል ፀጋ የህይወትህ መሪ ነው ። በስሜት ሳይሆን በእውቀት ፣ በጥበብ ፣ በማስተዋል ተመራ ። ምንም ነገር አብልጠህ ልትወድ ትችላለህ ከምታምነው አምላክ የሚበልጥ ነገር ግን ሊኖርህ አይችልም ።

አዎ! ጥያቄ ይኖርሃል ፤ ልብህ ያልረካበት ጉዳይ ይኖራል ፤ ሰላም የማይሰጥህ አጀንድ አለ ። ነገር ግን ለሁሉም ጥያቄና ውግዘት የእራሱ አግባብና ስረዓት አለው ። በስረዓት አልበኝነት ገመድ ተጠልፈህ እንዳትወድቅ ተጠንቀቅ ፤ በጎጠኝነት አባዜ እምነትህን እንዳትረሳ ፤ ስልጣንህን ተማምነህ ፣ በወገንህ ተመክተህ እራስህን እንዳታጣ ። ከምታነግሰው ፈጣሪ ውጪ ሌላ የምትተክለው እሾህ በውስጥህ እንዳይኖር ። ሁሉም ነገር ከእምነትህ ቦሃላ የሚመጣ ነው ፤ ፈጣሪህን አስቀድሞ የሚከተል ነው ። የትኛውም አማኝ ምግባር አለው ፤ ስረዓት አለው ፤ ህግ አለው ፤ ሀይማኖታዊ አቋም አለው ። አምላክህን በጥበብ ምረጥ ፤ በማስተዋል እወቀው ፤ ለእርሱም በሙሉ ልብህ ተገዛ ፤ ስልጣኑን ተቀበል ፤ ህግጋቱን አክብር ፤ ማንነትህንም አስገዛለት ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.6K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 20:07:42 በፅናት ተሻገር!

በህይወት መኖር የማስደሰቱንም ያህል በእጅጉ መፈተኑ ፣ ማሳመሙ ፣ ማሳዘኑ ፣ ማስለቀሱም የማይቀር ጉዳይ ነው ። ነገር ግን በድልም ሆነ በሽንፈት ፣ በብርታትም ሆነ በድካም ፣ እንዲሁ በጥንካሬም ሆነ አቅም በማጣት ወቅት ፅናት ያስፈልግሃል ። ብርቱ ነኝ ፣ አቅሙ አለኝ ፣ የሚችለኝ የለም ብለህ አቅምህን በደካማው ላይ ለማሳየት አትሞክር ። ጊዜው ከፍቷል ፤ መከራ በዝቶብኛል ፤ አቅም አንሶኛል ፤ ጫናው በርትቶብኛል ብለህም ተስፋ አትቁረጥ ፣ አንገትህን አትድፋ ፣ በብዙም አትከፋ ። ዋጋህ በሰው ፊት አይደለም ፤ ድርሻህ ምድራዊ አይደለም ። ስጋህ ብዙ ይመኛል ፣ ብዙ ያስባል ፣ ብዙ ይናፍቃል ለዛም በቶሎ ይሰበራል ፤ በፍጥነት ይደክማል ፤ ይዝላልም ። ስጋህ ሲደክም ፣ ተስፋ ሲያጣ ፣ ብርታት ሲጎድለው ህያዊት ነፍስህን አድምጥ ፤ የአባቷን ቃል ስማ ፤ የአምላኳን ፍቃድ ጠይቅ ። ፅናት ካለህ ሁሉን እንደ አመጣጡ ማሳለፍ ትችላለህና ምንም አይመጣብህ ፤ ምንም አይደርስብህም ፤ አንዳች አትሆንም ፤ ምንም አይነካህም ፤ አትፍራ ።

አዎ! ጀግናዬ..! በፅናት ተሻገር! በእርግጥ የሚፈትን ጊዜ ሁለመናህን ይፈትናል ። እምነትህን ፣ ፅናትህን ፣ ድፍረትህን ፣ ተነሳሽነትህን ፣ ቆራጥነትህን ፣ ታታሪነትህን ፣ ትጋትህን ፣ መልካምነትህን ፣ አርዓያነትህን በሙሉ ይፈተናል ። እያንዳንዱ ነገር እንደሚወራው ቀላል አይደለም ፤ እንደሚሰማውም ከባድ አይደለም ። ብርቱ ፅናት በመከራ ጊዜ ይፈተናል ፤ በእምነት እስከ ጥግ መፋለም በችግር ጊዜ ይፈትናል ፤ ላመኑበት ወደፊት መጓዝ በአጣብቂኝ ሰዓት ይለካል ። ፅናትን ይዘህ አታፍርም ፤ ፍቅርን አንግበህ አትሸነፍም ፤ ተስፋ ኖሮህ ወደኋላ አትመለስም ፤ በእምነት ቆመህ አትሰበርም ። ምንም የሚያስፈራና የሚያስጨንቅ ፣ የማትወጣውና የማያልፍ ቢመስልህም ሁሉም በጊዜው ያልፋል ። ምንም ነገር በምክንያት ይሆናል ፤ ማንም ቢሆን እንደ ስራው ይከፈለው ዘንድ የግድ ነው ። ያንተ አብዝቶ መጨነቅና መስጋት የሚያመጣው ነገር አይኖርም ።

አዎ! በቻልከው አቅም ላመንክበት ነገር በፅናት ታገል ፤ ለማንም ሳይሆን ለእራስህ ታመን ፤ ለአምላክህ ተገዛ ፤ በህግጋቱ ኑር ። ሰዎች ምድራዊ ህግጋትን ያወጣሉ ፤ ስረዓት ያበጃሉ ፣ ህግና ደንብን ይዘረጋሉ ። ነገር ግን እራሳቸው አፍራሹና አጥፊው ሆነው ይገኛሉ ። የማይገዛቸውን ህግ እንደ ጌታ ያዩታል ። ከህጎች በላይ የህሊና ህግ አለ፣ ነገ የሚፈርድብህ የገዛ ህገ ልቦና አለ ። ሁሉም ሲያልፍ ጥለሀው ለምትሔደው ምድራዊ ቁስ ክብርህን አታሳንስ ፤ ማንነትህን አታዋርድ ። ሌላው ይቅርና የተሸከምከው ስጋ እንኳን ባዳ ነው ። ነገ ጥሎህ ይጠፋል ። ከማንም ብትቀማ ለጊዜው ያንተ ቢሆን እንጂ ዘላለም የእራስህ የምታደርገው ነገር የለም ። ቦሃላ እንደ ጤዛ ለሚጠፋ ንብረት ፣ ዝና ፣ እውቅናና አድናቆት ብለህ ሰውነትህን አትጣ ። ዛሬ የተከተለህ ሁሉ ነገ እንደማይሸጥህ ምንም ዋስትና የለህም ። አተህም አግኝተህም ፅና ፤ ተደንቀህም ተዋርደህም ፅና ፤ ተገፍተህም ተወደህም ፅና ። ክፉውንም ደጉንም በፅናት ተሻገር ፤ አላፊውንም እንደ ሁኔታው አሳልፍ ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.2K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 20:07:33 ህልምህ ይፈትንሃል!

ከማንም ተለይቶ ወዳንተ የመጣ ህልም በቀላሉ ህልምና ተልቁ የህይወትህ ስንቅ አይሆንም ። ይፈትንሃል ፤ ዋጋ ያስከፍልሃል ። አቅምና ብርታትህን በእራሱ መንገድ ይለካል ። ለህልምህ እንደሞትገባውና የእርሱ እንደሆንክ ማረጋገጡ ያንተ ድርሻ ነው ። ውሎህ ሌላ ስራህ ሌላ ቢሆን ለህልምና ራዕይ የመታመን ሁኔታ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ይገባል ። የትኛውም ህልመኛና ባለራዕይ ይፈተናል ፤ መከራ ውስጥ ይወድቃል ፤ ይታመማል ፤ ይሰቃያል ። በቀላሉ ትልቅነት አይገኝም ፤ እንዲሁ በዋዛ ፈዛዛ ተፅዕኖ ፈጣሪነት አይመጣም ። እጩነቱን መሻገር ፣ ህልምን በእጅ ማስገባትና በእርግም እውነተኛ ህልመኛና ባለራዕይ መሆን ይጠበቅብሃል ። ዋጋ የሌለው ፣ መሱዓትነት የማያስከፍል ነገር ቀላልና የወረደ ነገር ብቻ ነው ። ትልቅ ነገር ስታስብ ክፍያህም ያድጋል ፤ የሚጠበቅብህ ግዴታም እንዲሁ ይጨምራል ።

አዎ! ጀግናዬ..! ህልምህ ይፈትንሃል! ዋጋህን በምትከፍለው መሱዓትነት ይወስናል ፤ አቅምህን በምትወጣው ሃላፊነት ልክ ይመዝናል ። አንዳንዴ የምትችለውን ብቻ ማድረግ ህልምህ የሚጠብቅብህ ላይሆን ይችላል ። ከምታስበው በላይ ከወዳጆችህ ይለይሃል ፤ በሰው ያስተችሃል ፤ ከመንጋው ይነጥልሃል ፤ ውሎህን ያስለውጥሃል ፤ መጥፎ ልማዶችህን ያስተውሃል ፤ ወሬህን ያስቀይርሃል ፤ ዙሪያህን ያጠራዋል ። የህልምህን ትልቅ መሆን በሃሳብህ ትልቅነት ታረጋግጣለህ ። የራዕይህን ሁለተናዊነት በምትፈጥረው የተለያየ ግንኙነት ትለየዋለህ ። ሹመት ያለፈተና አይሰጥምና ያንተ በህልምና ራዕይህ ላይ መሾም በፈተና ይሆናል ፤ ተገቢነትህን በማረጋገጥ ይሆናል ። የፈለከውን እያደረክ ፣ የፈለክበት እየተገኘህና ያሰኘህን እየፈፀምክ ስለ ህልምና ራዕይህ እውንነት አትናገርም ። ህልመኛ የሚያደርግህ የእራስህ መንገድ አለህ ፤ ህልምህን እውን የሚያደርግና የሚያሳካም ትክክለኛ ጎዳና አለ ።

አዎ! ያንተ የሆነው ህልም ላንተ ስለመሆኑ ማረጋገጫ ይፈልጋል ፤ በእርግጥም አንተ እንደምትገባውና እንደምትመጥነው መታወቅ ይኖርበታል ። ትልቅ ህልም አለኝ ስላልክ ብቻ ህልመኛ አትሆንም ፤ ደጋግመህ ስለ ህልምህ አመጣጥና እውንነት ስላወራህ ብቻ ህልምህን የትም አታደርሰውም ። ህልሜ የምትለው ነገር የሚፈልገውን አይነት ሰው ሆነህ የመገኘት ግዴታ አለብህ ፤ የእርሱን አቅጣጫ መምረጥም ይኖርብሃል ፤ መስፈርቱን ማሟላት ይጠበቅብሃል ። ህልምህ ችግር ፈቺና ለሰው የማይደርስ ከሆነ ገና ወደ ህልምነት አላደገም ማለት ነው ። ራዕይህ ሁሉን አካታችና አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያራምድ ካልሆነ ራዕይነት ላይ አልደረሰም ማለት ነው ። በገዛ ህልምህ ተፈትነህ ፣ ባንተው ራዕይ ተመዝነህ አልፈህ ከሆነ ወደኋላ የምትመለስበት ምክንያት የለህምና ፈተናህን ተሻገር ፣ ምዘናውንም አልፈህ ተገኝ ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.2K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 04:57:03 ለቀንም ቀን አለ!

ብርሃን ሲኖር ጨለማ አይኖርም ፤ የብረሃን መጥፋትም ጨለማን ይፈጥራል ። ጥፋት ጥፋትን እስኪወልድ መጠበቅ ከአጥፊነት አይተናነስም ። እሳት በጊዜ ካልጠፋ የሚያጠፋው ጥፋት ይበዛል ፤ አደጋው በሒደት እያየለ ይመጣል ። ዝምታም እንደ እሳት ነው ፤ የሚታይ ግልፅ ተቃውሞና ትቺት ባይኖር እንኳን ዝምታን የመረጠ መቀጣጫ በምንም አይመለስም ። አምላክ ስራውን በሚሰራበት ሰዓት እራስን እንደ አምላክና ፍፁም አድርጎ መመልከት ማንነትን መዘንጋት ፣ ሰውነትንም መርሳት ነው ። ሌትና ቀንን የፈጠረ አምላክ የረዘመውን ለሊት ፣ አላልቅ ያለውን ጨለማ ማሳጠር አያቅተውም ። ሁሉም ማለፉ ላይቀር ሰንፈን ከብርቱ ፣ ጥሬውን ከብስሉ ፣ ገፊውንም ከደጋፊው ለይቶ ያሳያል ። እምነት ያለው ትውልድ ፣ የምርም አምናለው ፣ አምላኬን አውቃለሁ ፣ በእርሱ እታመናለሁ ፣ በእርሱ እመካለሁ የሚል አማኝ ከማንም እምነቱን ይወዳል ፤ ከምንም እምነቱን ያስቀድማል ።

አዎ! ጀግናዬ..! ለቀንም ቀን አለ! ለጨለማም ነጉሱ ብረሃን ይመጣል ፤ ለምድር ሹማመንትም የሰማዩ ገዢ የምድሩ አለቃ ይወርዳል ። ሰላም አለ ፣ ፍቅር አለ ፣ መተሳሰብ ፣ መዋደድ ፣ መከባበር አለ አንድና አንድ አምላክን ማክበር ሲቻል ብቻ ። የሰው ልጅ ታመህ ብታለቅስ ለመረበሽ ያለቀስክ ይመስለዋል ፤ ስቃይህ ቢያስነባህ ለፌዝ ምታነባ ይመስለዋል ። የሰማይ አምላክ ግን እንባ ያቀረረ አይንን ይረዳል ፤ የባባ ሆድን ያውቃል ፤ የሚያዝን አንጀትን ይመለከታል ። ምድር ትሳቅብህ ፤ ፍርዷን ትንሳህ ፣ መከራውን ታብዛብህ ፣ አንገትትሀን ታስደፋህ ፣ ታሳፍርህ የምታምነው አምላክ ግን እውነተኛ ፍርድን ይሰጥሃል ፤ እንባህን ያብሰዋል ፤ ከሳሾችህን ይከሳል ፤ ፈራጆችህንም ይፈርድባቸዋል ።

አዎ! አምላክን ከያዝክ ፅና ፣ ተስፋ አድርግ ፣ ታገስ ፣ ጠብቅ ። መጥፎ ጊዜ እህሉ ከእንክርዳድ የሚለይበት ወቅት ነው ። እንክርዳዱ በምክንያት ይጣላል ፤ ሰብሉም በጊዜው ይለመልማል ፣ ፍሬንም ያፈራል ። ፀሎትህ ወደ አምላክህ ይሁን ፤ ጩሀትህ ወደ ሰሚው ፈጣሪ ይሁን ። አምላክ አብሮህ ካለ ፣ እርሱ ከቀደመልህ የማትወጣው መከራ ፣ የማታልፈው ስቃይ የለም ። እውነት ጊዜ አላት እስከዛም ውሸት ምድርን ትዞራለች ፤ በመድሎና በፍረደ ገምድል ትከበባለች ። እውነት በነገሰች ወቅት ግን መኖሯም ይዘነጋል ። አመፅ ይነሳል አምላክህን ይዘህ ታገል ፤ ፍርድ ይዛባል ፈጣሪ እንዲፈርድ ተማፀን ፤ በደል ይደርስብሃል አምላክ እንዲያበረታህ ጠይቅ ። ሰው ይስታል ፣ ሰው ይሳሳታል መታረም ቢፈልግም ይታረማል ፤ አውቆና ፈቅዶ ካደረገው ግን ስህተት ሳይሆን አቋሙ ነውና ለእራስህ አቋም ታማኝ ሁን ። የተስፋዋ ቀን ትመጣ ዘንድ ፅና ፤ ሰላምን ታገኝ ዘንድም አምላክህን ያዝ ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.5K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  01:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 04:54:49 ባልሰራሀው አትናደደ!

ውጤት እንዳልመጣለህ ታስባለህ ፣ በጠበከው ልክ የፈለከው ቦታ እንዳልደረስክ ይሰማሰሃል ፣ እርካታ ርቆሃል ፤ መረጋጋት ተስኖሃል ፤ የምትችለው ያክል እንዳላደረክ ይሰማሃል በዚህ ምክንያት በእራስህ ትናደዳለህ ? በእራስህ ታዝናለህ ? እራስህን ትወቅሳለህ ? አስታውስ ፤ ሳትሰራ ይመጣል ብለህ በምትጠብቀው ውጤት ፣ ምክንያት አልባና ያለ በቂ ጥረት የሚመጣ አይደለም ። ውጤትን ብቻ እየጠበክ ብታደርግ ያለህን ታጣለህ እንጂ የምታተርፈው ነገር የለም ። ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ እንተባለው ምንም ሳትለፋ ፣ ሳትተጋ ፣ ሳትደክም እንደማንኛውም ሰው በማቀድና በማሰብ ብቻ ጊዜህን እያራዘምክ ፣ እቅድህን እያደስክ ፣ ሰበብህን እያሳመርክ ብትቀጥል ጊዜውም ይሔዳል ፤ ያንተም ሃሳብና እቅድ እንዲሁ እየተነነ ይመጣል ።

አዎ! ጀግናዬ..! ባልሰራሀው አትናደድ! ምንም ሳትሞክር በማይታይ ውጤት እራስህን አታጨናንቅ ፤ ዋጋ ሳትከፍል በማታየው ለውጥ አትረበሽ ፤ ሳትሞክር በማይመጣ ለውጥ አትደናገጥ ። ምንም ሳታደርግ ምንም እንደማይፈጠር እወቅ ። ምክንያት መደርደር ላይ ብትጀግን፣ እቅድ ማውጣት ላይ በርትተህ ትግበራውን ወደጎን ብትለው ፣ ከትጋትህ በላይ ሃሳብ ላይ ብታተኩር ፣ ከስራው በተሻለ ውጤቱን በጉጉት ብትጠብቅ አንዳች ነገር አይመጣም ። የጠበከው ይርቅሃል ፤ የተመኘሀው ይሸሽሃል ፤ ያሰብከው ይበተናል ፤ ያቀድከው መና ይቀራል ። ለትግበራው ዛሬ ነገ ብትል ውጤቱ እንዲሁ ዛሬ ነገ ማለቱ አይቀርም ። መሬት ላይ ያልወረደ ሃሳብ ሃሳብ ብቻ ነው ፤ ያልተኖረ እውቀት ባዶ እውቀት ነው ፤ የማይተገበር እቅድ የውድቀት ማበረታቻ ነው ።

አዎ! ውጤቱን ባለማየትህ ፣ የጠበከው ባለመሆኑ ፣ የተመኘሀው ባለመፈፀሙ ቅንጣት ብስጭት ውስጥ አትግባ ። ዋጋውን ካልከፈልክ ዛሬም ነገም እንዲሁ ውጤት እየናፈክ ፣ የተሻለ ህይወት እንደተመኘህ ትቀጥላለህ እንጂ ምንም የሚመጣልህ አዲስ ግኚት አይኖርም ። ችግርህ የጥረትህ ማነስ ፣ የተግባርህ መድከም ፣ የልፋትህ ዋጋ ማጣት ከሆነ ጥረቱን መጨመር ፣ ክፍያውን ማሳደግ በተቃራኒውም የምትጠብቀውን ውጤት ማሳነስ ይኖርብሃል ። በባዶ ሃሳብ ታላቅነትን ማሰብ ሌሊት የሚታየውን ህልም ጠዋት በድጋሜ ለማየት እንደመንደርደር ነው ።

አዎ! ተናደድክ አልተናደድክ ፣ ተበሳጨህ አልተበሳጨህ ፣ አዘንክ አላዘንክ ስራህ ለውጤት የሚያበቃህ ፣ ልፋትህ የምትመኘው ቦታ እንደሚያደርስህ በሚገባ ታውቀዋለህ ። በምታውቀው ጉዳይ ንዴታና ብስጭትም አያስፈልግም ። ካልሰራህ ውጤት የለም ፤ ሌት ተቀን ካልተጋህ ጠብ የሚል ነገር አይኖርም ። ህይወት ውጣውረድ አላት ወቶ መውረድም ያንተ ድርሻ ነው ። የሚጠበቅብህን ሃላፊነት በበቂ ሁኔታ ሳትወጣ ፣ አቋራጭ መንገድን እንደ ዋንኛ አማራጭ እየተመለከት ፣ ከስራና ጥረት ባላይ ውጫዊው ተግባሮች ላይ ተማምነህ ፣ እንኳን የጠበከው ትልቅ ውጤት ይቅርና ከጠበከው በታች ተስፋ ሰጪ የሚያበረታታ ነገርም ላይመጣ እንደሚችል አስብ ። ውጤቱን ከፈለክ ትጋቱን እኩል በእኩል ፈልገው ፤ ስራው ላይም በርትተህ ተገኝ ። ያልሰራ ውጤት የለም ፤ ያለልፋት ከፍታ አይመጣም ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.5K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  01:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 16:00:03 ዛሬ የመርሳት ቀን ቢሆን በህይወታችሁ ምን መርሳት ትፈልጋላችሁ
3.5K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, 13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 15:56:04 ስንት ይሆን ኪሎዬ?

በኑሮዬ መስመር ላይ በህይወት ጎዳና
ጉዞዬ ከሆነ ውሃ አልባ ደመና
ፍቅር ካልቋጠርኩኝ በልቤ ስልቻ
ዘግይቼ ከወጣው የምግባር እንጎቻ
ተስተካክሎ ቢቆም ልብስና ስጋዬ
በነፍስ ሚዛን ላይ ስንት ይሆን ኪሎዬ?
3.4K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, 12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 04:14:12
#_ስትሞቺ_እሞታለሁ
ደስታሽ ከፊትሽ ላይ ተነጥሎ ካየሁ
ባንቺ ማዘን ብቻ እኔም ብዙ አዝናለሁ
አንዲት ዘለላ እንባ ከአይኖችሽ ካገኘሁ
የጎርፍ ያህል እንባ እኔም አነባለሁ

ታመሽም ከሆነ ተኝተሽ ከአልጋ ላይ
እኔንም ይመመኝ ስቃይሽን እንዳይ
አንቺን ደስ ካለሽ ሀሴት ከተሰማሽ
አንዲት ክፉ ነገር ፈፅሞ ካልነካሽ

እኔም ደስ ይለኛል ባንቺ ደስታ ብቻ
የህይወት ቁልፌ ነሽ የልቤ መክፈቻ
ይህንን ልንገርሽ እንዳትረሺ ፍቅሬ
አንቺ ስትኖሪ ነው በደስታ መኖሬ

የማያት ሻማዬ ጨርሳ እንዳትጠፋ
ብርሀን የያዘች የመኖሬ ተስፋ
አንቺ ነሽ ምክንያቷ የነብሴ መለምለም
እሩቅ አሻግሬ ህይወትን እንዳልም

ህመምሽ ህመሜ እንባሽ ነው እንባዬ
ቃልኪዳን አለብኝ ልኖር አንቺን ብዬ
ፈጣሪ ከጠራሽ በአይኔ ሞተሽ ካየሁ
እወቂልኝ ፍቅሬ ስትሞቺ እሞታለሁ
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.9K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  01:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 03:48:53 ስም ይጥልሃል!

ስምህን ለማሳመር ፣ በሰዎች ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት ፣ ከላይ ከላይ ጎልቶ ለመታየት ፣ ለመወደድ ፣ ለመደነቅና ለመሞገስ የምታደርገው የትኛውም ጥረት ጥፋትን ሊያስከትልብህ እንደሚችል እወቅ ። ሰዎች ተቀብለውህ አንተ እራስህን ባትቀበል ምን ይጠቅምሃል ? ሰዎች በሚያዩት ነገር ቢያጨበጭቡልህና አንተ በምታውቀው ነገር ብታዝን ምን ታተርፋለህ ? አንድ ቀን የሚፈርስ ጥሩ ስም ከመገንባት ይልቅ ሁሌም አብሮ የሚቆይ ፅኑ ማንነትን መገንባት ይሻልሃል ። አንተነትህን ስትገነባ ፣ ብቁ ለመሆን ስትተጋ ፣ እራስህ ላይ ስትሰራ ተቀባይነት ማግኘት ፣ መወደድ ፣ መደነቅ ፣ መሞገስ ዋናው መስፈርትህ አይደለም ። ትልቁና ዋነኛው ምክንያትህ ለውጥና እድገትህ ነው ፤ ስኬትና ተፅዕኖ ፈጣሪነትህ ነው ። ማንም ነገ የሚለቅ የተቀባባ ፣ የተሽሞነሞነና ለጊዜው የሰዎችን ትኩረት ብቻ ሊስብ የተዘጋጀን ነገር የመጀመሪያ ምርጫው ሊያደርግ አይችልም ። ወርቅ ቅብ ነሐስ እውነተኛው ነሃስነቱ ሲታወቅ ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት አይከብድም ።

አዎ! ጀግናዬ..! ስም ይጥልሃል! ስምህን ለመገንባትና ክብርን ለማግኘት ያልሆንከውን ነኝ ፣ ያሌለህን አለኝ ፣ ያልሰራሀውን ሰርቼያለው ፣ ያንተ ያልሆነውን የእኔ ነው ብትል ለጊዜው የምትገነባው ጥሩ ስም ሊኖርህ ይችላል በሒደት ግን የሚፈርስ ማንነት ይኖርሃል ። ማንም ሰው ውሸትን አይወድም ፤ መታለልን አይፈልግም ፤ በሌለ ማንነት መተዋወቅም አይመቸውም ። በምላስ የተሽሞነሞነና በማንነት የሚታወቅ ሁለት ገፅታ የውድቀት ሁሉ መሰረት ነው ። እራስህን የጠቀምክ እየመሰለህ ሰዎችን ለማስደመም ብቻ ወጪህን ብታበዛ ፣ ለታይታ ደስተኛ ብትመስል ፣ ለይስሙላ እንደ ሃብታም ብትንቀሳቀስ ውጫዊ ገፅታህን እያስዋብክ እራስህን ትጥላለህ ። ያንተ ለብሶ መታየት ፣ ደምቆ መገኘት ፣ እንዳለው ለማሳየት ደረቱን ነፍቶ መሔድ የሚያሳስበው ሰው ያለ ይመስልሃል ? በፍፁም ።

አዎ! ማንነትህን በስምህ ለመገንባት አትሞክር ፤ እራስህን በምታገኘው ተቀባይነት አተለካ ፤ ሰውነትህን በውጫዊ ሙገሳና አድናቆት አትመዝነው ። ሊቀይርህና ሊታወቅ የሚገባው ከላይ በወሬና በጌጣጌጥ የደመቀው ገፅህ ሳይሆን በውስጥ የተደበቀው እውነተኛ አንተነትህ ነው ። የምታገኛቸው ሰዎች ነገ አብረውህ አይኖሩም ፤ የሚያውቁህ ሰዎች ዘወትር አብረውህ አይኖሩም ። ሰዎችን ለማታለል ትጥራለህ እንጂ የምታታልለው የገዛ እራስህን ነው ፤ ሰጣ ገባ ውስጥ የምትገባው ፣ ሃሳብህን የምታጋጨው አንተው ነህ ። ገፅህን አይተው ፣ ዝናህን ሰምተው ፣ ለእራስህ በሰጠሀው ሃሰተኛ ስም ተታለው የሚመጡ ሰዎችም ሆኑ ሌሎች ጥቅማጥቅሞች በእርግጥም ሊቀይሩህና ሊያሳድጉህ ሳይሆን ሊጥሉህና ማንነትህን ሊያጎድፉ ነው ። ከስምህ ማንነትህን አስቀድም ፤ ከገፅህ ስብዕናህን አሳውቅ ፤ ከውጫዊው ከበሬታ ውስጣዊውን የእራስህን ክብር ጠብቅ ፣ አስጠብቅ ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.5K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  00:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ