Get Mystery Box with random crypto!

ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️

የቴሌግራም ቻናል አርማ mirttshefoch — ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️
የቴሌግራም ቻናል አርማ mirttshefoch — ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️
የሰርጥ አድራሻ: @mirttshefoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 32.43K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-05-12 20:24:34 ውሃ አጠጣው!

እንዲያድግ የምትፈልገውን፣ አድጎም ጥላ እንዲሆንህ፣ ለማረፊያነትና ለመዝናኛነት እንዲያገለግልህ የምትፈልገው ተክል ካለ በየጊዜው ውሃ አጠጣው፤ መግበው፤ ተንከባከበው። እርሱን ሳይሆን ከእርሱ የምታገኘውን ጥቅም ብቻ መፈለግህ የምትፈልገውን ነገር በበቂ ሁኔታ ላያስገኝልህ እንደሚችል እወቅ። ያስደስተኛል፤ ስሜት ይሰጠኛል፤ ወደፊትም ያሳርፈኛል ብለህ የምታስበው ሙያ ካለህ፣ ክህሎት ካለህ ጊዜ ማጥፋት አያስፈልግም በፍጥነት ስራበት፤ በሚገባ እወቀው፤ አሳድገው፤ አንተም እደግበት። እያሳመመህም ቢሆን ከፈለከው ዋጋ መክፈል ይኖርብሃል። ክህሎቱን ያወቀ፣ እርሱም ላይ የሰራ፣ እለት እለት 1% እላዩ ላይ እየጨመረ የሚጓዝ ሰው የጊዜ ጉዳይ እንጂ እስካላቆመ ድረስ እንደሚያልፍለት ምንም ጥርጥር የለውም።

አዎ! ጀግናዬ..! እችለዋለሁ፤ ይሳካልኛል፤ ያሳልፍልኛል ብለህ የምታስብ ከሆነ በየሰዓቱ ውሃ አጠጣው! ተንከባከበው፤ ጠንክረህ ስራበት። መማር እስካለብህ ጠንክረህ ተማር፣ መስራት እስካለብህ ጠንክረህ ስራበት። እራስ ላይ መስራት፣ ክህሎትን ማዳበር፣ በየቀኑ አንድን ነገር እየደጋገሙ መገኘት፣ ለረጅም ጊዜ ውጤት የማያሳይ ነገር ላይ ረጅም ጊዜ ማሳለፈ እጅግ ከባድና አሰልቺ መሆኑ አይቀርም። ነገር ግን ይህ የሚሆነው ተግባሩን ካልወደድከው፣ ክህሎትህ እንደሆነ ካልተቀበልክና በሂደቱ ደስተኛ ካልሆንክ ብቻ ነው። በዚም ሆነ በዛ ጊዜ ማለፉ ላይቀር አንተም ሳትሰራበት፣ እራስህን ፈልገህ ሳታገኝ፣ እራስህ ላይ ሳትሰራ እንዲያልፍ አትፍቀድ። ለእራስህ ጉዳይ እራስህ ሃላፊነት ትወስዳለህ፤ የእራስህን ተግባር እራስህ ትከውናለህ፤ እየቻልከው ስለምን ሌሎች በማድረጋቸው ቀናተኛ ትሆናለህ? እየቻልክ ስለምን እንደማይችል ትኖራለህ?

አዎ! ቆመህ የምታይበት፣ በአላፊ አግዳሚው የምትደነቅበት፣ በምኞት አለም የምትዋትትበት ጊዜ አብቅቷል። ከጆሮህ አልፈው ወደ አዕምሮህ የሚገቡትን፣ ከአዕምሮህ አልፈው ደምስርህን የሚቆጣጠሩ፣ ማንነትህን የሚገሩ፣ ስብዕናህን የሚቀይሩ ንግግሮች ላይ ጥንቃቄ አድርግ። ማደግ የሚፈልግ ሰው ስሩን በሚያደርቁ፣ ውሃ በሚከለክሉት፣ ከአዎንታዊነት በሚነጥሉት ነገሮች እራሱን አያጥርም። እራስህ ላይ የምትሰራው በመጀመሪያ ለእድገትህ ከማይጠቅሙህ ሰዎችም ሆነ ሌሎች ነገሮች በመራቅ ነው። ከዛም ያለማንም ከልክይና አሰናካይ እለት እለት እራስህን መመልከት ትጀምራለህ፤ እራስህን ትንከባከባለህ፤ እራስህን ታስተምራለህ፤ ታሰለጥናለህ። የሚባለው ላይ ሳይሆን በእርግጥም የሚጠቅምህ ላይ ታተኩራለህ። ያለማቋረጥ ውሃ ያጠጣሀው፣ የተንከባከብከው ማንነትህም በጊዜው ፍሬ አፍርቶ፣ ለብዙዎች ተርፎ፣ ሌሎችንም አስጠልሎ ትመለከተዋለህ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.0K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 20:24:03 አውጥተው ይጥሉሃል!

ምንም ያክል የዋህ ልትሆን ትችላለህ፣ ምንም ያክል የፍቅር ልብ ሊኖርህ ይችላል፣ ምንም ያክል ልትታመን፣ ቃልህን ልትጠብቅ፣ እንዲሁም እንደፍቃዳቸው ልትሆንላቸው ትችላለህ ነገር ግን በሚያሳዝን ሁኔታ አንድ ቀን ትቀየራለህ፤ አንድ ቀን የተሻለ በሚሉት ሰው ይተኩሃል፤ አይንህን ለአፈር ይሉሃል፤ ፊታቸውን ያዞሩብሃል። ቢያምም እውነታው ግን ይሄው ነው። ምክንያቱም ሰዎች ስንባል እራስወዳዶች ነንና ነው፤ ምክንያቱም ሰዎች ስንባል ከሚወደን ይልቅ የምንወደውን መከተል የሚቀናን ሚስጥር የሆንን ፍጥረቶች ስለሆንን ነው፤ ምክንያቱም ሰዎች ስንባል ከእኛ ስሜት በላይ ለማንም ስለማንጨነቅ ነው። ተቀይረው ባሳመሙህ ሰዎች ላይ አትናደድ፤ ምክንያቱም ለእራሳቸው ታምነው ስለሚኖሩ፤ ቢያንስ በጊዜ ስለተለዩህ፣ የእራስህን መንገድ ለእራስህ ስለተውልህ።

አዎ! ጀግናዬ..! አንድ ቀን ትቀየራለህ፤ አንድ ቀን እንደ ሸንኮራ ታኝከህ ትተፋለህ፤ አንድ ቀን እንደፈለጉት ተጠቅመው አውጥተው ይጥሉሃል። ለእራስህ የምትሰጠውን ክብር ጠንቅቀህ እወቅ፤ ለእራስህ የምትሰጠውን ጊዜ በሚገባ አስተውል። ነገ ለሚጥልህ ሰው እራስህን አሳንሰህ አትሽቆጥቆጥ። ከማንም ጋር ሰላም መሆን ደግ ነው፤ ሰውን መውደድ፣ መፈለግ፣ ማፍቀር መልካም ነው። ነገር ግን ተመጣጣኝ ስሜት በሌለበት ሁነት ውስጥ አንድ ቀን የመተውና የመቀየሩ ነገር የማይቀር ጉዳይ ነውና ለእራስ የሚገባው ፍቅር ሊጎድል አይገባም። አንዳንዴ የዋህነትህ ዋጋ ያጣል፤ አሳቢነትህ ትርጉም አያገኝም፤ ፍቅርህ ከቁብነገር አይቆጠርም፤ እንክብካቤህ እንደ ጂል ያስመለክትሃል፤ ደግነትህ በሞኝነት ያስፈርጅሃል። የትኛውንም ግንኙነትህን ለማዳን ያንተ እረፍት አልባ ጥረት ብቻ ምንም ሊያመጣ አይችልም።

አዎ! ሰው የሚፈልገውን በመፈለግ ተጠምዷል፤ የሚወደውን በማሳደድ እረፍት አጥቷል፤ የሚያፈቅረውን በማስጨነቅ ለእራሱም ተጨንቋል። በተቃራኒው እርሱን የሚፈልገውን፣ ለእርሱ ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ የሆነውን ዞር ብሎ መመልከት ቢችል ምን ነበረበት? የሚፈልግሽን አሻፈረኝ ብለሽ ሄደሽ የምትፈልጊው ሲጫወትብሽ መመለከቱ ምን ያስገኝልሽ ይሆን? ለአይን የምትሳሳልህን ገፍተህ ልታይህ እንኳን የምትጠየፍህ ላይ መጣበቅህ፣ እርሷ ስርስር ማለትህ ምን ይረባህ ይሆን? የምትፈልጊውን በቀየርሽበት አኳሃን አንቺም አንድ ቀን ይህ እጣ ይደርስሻል፤ የቀረበልህን ሲሳይ ገፍተህ በሔድክበት ማግስት የመገፋትን ልክ በተራህ ትቀምሳለህ። ለእራስህ የምታስብ ከሆን የሚበጅህን በጥንቃቄ ምረጥ፤ የአምላክን ፍቃድ ጠይቅ። እንደ ንጉስ ተወደህና ተከብረህ መኖር እየቻልክ ስለምን ተገፍተህና ተዋርደህ እንደ ባሪያ እንደምትኖር እራስህን ጠይቅ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.4K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 21:39:08
ፈጣሪህን አስቀድም!
አንዳንድ በሮች ይዘጉብሀል፤ ቦታህ ስላልሆኑ
አንዳንድ በሮች ይዘጉብሀል፤ ጥንካሬህን ሊፈትኑ
አንዳንድ በሮች ይከፈቱልሀል ፤ ያንተ ስለሆኑ
አንዳንድ በሮች ይከፈቱልሀል ፤ በግድ ስለታገልካቸው
እናም ተዘጋ ማለት በቃ ማለት ብቻ አይደለም ተከፈተም ማለት ሆኗል ማለት አይደለም እናም አስተውልና ከፈጣሪህ ጋር ተማክረህ መንገድህን ቀጥል ከፊትህም ፈጣሪህን አስቀድም !
2.4K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, 18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 21:05:36
#_ዕድሌ_ነው
በሚስትልወሰን ፣ እኔ ትዳር ሲያምረኝ ፤
ሳታገባ 'ምትቆይ ፣ አንድም ሴት አትገኝ
#_ዕድሌ_ነው
እኔዲግሪ ስይዝ ፣ ዲግሪ ዋጋ ያጣል ፤
ገንዘብ ያለው ሁሉ ፣ ዶክትሬት ያመጣል
#_ዕድሌ_ነው
እኔመድረክ ስይዝ ፣ ይፈታል ጉባኤ ፤
እኔ መጾም ሲያምረኝ ፣ ይሆናል ትንሣኤ ።
#_ዕድሌ_ነው
በቁርባንለመኖር ፣ ንሰሐ ስገባ ፤
አቁራቢው ፖትልኮ ፣ ቤተመንግሥት ገባ ።
#_ዕድሌ_ነው
እኔኳስ ስገዛ ፣ ሜዳው ይታረሳል ፤
እኔ ቤት ሲኖረኝ ፣ ሰፈሬ ይፈርሳል ።
#_ዕድሌ_ነው
ለተሾመሁሉ ፣ እንዳልኖርሁ ስለፋ ፤
እኔ አለቃ ስሆን ፣ የሚታዘዝ ጠፋ ።
#_ዕድሌ_ነውና
ከዕለታትአንድ ቀን ፣ መንገሤ ባይቀርም ፤
እኔ ንጉሥ ስሆን ፣ ሀገሪቱ አትኖርም ።
2.4K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 20:52:19 መዳረሻህ በእጅህ ነው!

መነሻህ የትም ይሁን፣ የመጣሀው ከየትም ይሁን፣ ውልደትህ ከየትኛውም ቤተሰብ ይሁን፣ አሁን ያለህበት ሁኔታ ምንም ይሁን ነገር ግን አሁንም መዳረሻህ በእጅህ ነው፤ መጨረሻህን የምታሳምረው አንተ ነህ። ታሪኮቻችን መገለጫችን ሳይሆኑ መሸጋገሪያ ድልድዮቻችን ብቻ ናቸው፤ ገደባችን ሳይሆኑ ግፊቶቻችን ናቸው። የሆነ ጊዜ ምንም እንዳልነበሩ ጥለናቸው እንወጣለን፤ በእነርሱ ማለፋችንንም እንረሳዋለን፤ በእነርሱ ተሰርተን ፍፁም የተለየውን ማንነት እንፈጥራለን። የት ነበርን? ዛሬስ የት ነን? ነገስ የት እንሆን ይሆን? የረጅም ጊዜ ጥረት፣ እልህ አስጨራሽ ትግል፣ የሚታክት ውጣውረድ ቢሆንም የተሻለውን እስከ ፈለግን፣ የሚልቀው እንደሚገባን ካመንን ማቆም የሚባለውን ነገር በመርሳት የሃሳባችን ስፍራ መድረሳችን አይቀርም።

አዎ! ጀግናዬ..! መዳረሻህ በእጅህ ነው፤ የምትደርሰው ግን ካላቆምክ ብቻ ነው። በሚመጥንህ ደረጃ፣ በሚወክልህ ሁኔታ ግብህን የምታዘጋጀው፣ ውጥኑን የምታስቀምጠው አንተ ነህ። የእራስህ ግብ እስኪኖርህ የመስሪያ ቤትህን ግብ፣ የአሰሪዎችህን ራዕይ፣ የመንግስትን እቅድ ለመምታትና ለማሳካት መጣርህ ክፋት የለውም። ያንተ ላልሆነው ይህን ያክል ከጣርክ የእራስህ ሲሆን፣ ትርኩም የሚሰጥህና በብዙ እጥፍ አስደሳችና የሚያረካ ሲሆን ደግሞ ምን ያክል እንደምትጥር አስበው። ውጪ ላይ በማስተዋል የሚከታተልህ፣ የት እንደነበርክ የሚያውቅ፣ አሁን የት እንደሆንክ ጠንቅቆ የሚያውቅ ሰው አለ። ምናልባትም ክትትሉ ሊያበረታታህ ወይም ሊማርብህ ወይም አደናቅፎ ሊጥልህ ይሆናል።

አዎ! እራስህን እየጠበክ ወደ መዳረሻህ ተጠጋ፤ ለእራስህ በቂ ጊዜ እየሰጠህ ራዕይህ ላይ ጠንክረህ ስራ፤ እራስህን እየተንከባከብክ እቅዶችህን ወደመከውን፣ ህልምህን ወደመኖር ግባ። እያንዳንዱን ውሳኔዎችህን የምታከብረው፣ ለገዛ ቃልህ የምትታመነው ሌላ ለማንም አይደለም፤ ለእራስህ ነው፤ እለት እለት እንዲሆንልህ ለምትመኘው መዳረሻህ ነው፤ ለትልቁ ህልምህ እውንነት ነው። መጋፈጥ ያለብህ ብዙ ጉዳይ ይኖርብሃል፤ ብዙ ማሰር፣ መፍታ ያለብህ እንቅፋት ይኖርሃል። ከመዳረሻህ በላይ ሂደቱ እንደሚያስፈልግህ እንዳትዘነገጋ። የአሸናፊነት አስተሳሰብ በውስጥህ እንዲሰርፅ አድርግ፤ ከተሸናፊዎች ራቅ፤ እንዳንተው ለመዳረሻቸው ከማይተጉ፣ ባንተ የእሳቤ ደረጃ ከማይመላለሱ፣ ህይወታቸውን በአላስፈላጊ ወሬና ንትርክ ከሚያባክኑ ሰዎች ተነጠል፤ የእራስህን ስኬትም እራስህ ወስን።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.0K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 20:51:43 ዝ..ምም በል!

አዎ! " ዝም በል! ምንድነው ችግርህ? ምንድነው የምትፈልገው? ወድቄ እንድቀር፣ ተስፋ እንድቆርጥ፣ ቦሃላ እንድቆጭ ነውን? እራሴን እንድጠላ፣ ከሰዎች እንድጠብቅ፣ እጅ እጃቸውን እንድመለከት፣ እነርሱን ስማፀን እንድኖር ነውን?" ይህን ንግግር ጥግ ይዞ ከሚቃወምህ የእራስህ ማንነት ጋር አድርገው። በእራሱ ላይ ህፀፅ እያወጣ የሚኖር ሰው መቼም በእራሱ ሊኮራና ሊደሰት አይችልም። ውስጥህ እየተመላለሰ የሚጨቀጭቅህን የእራስህን አሉታዊ አስተሳሰብ ዝም አሰኘው፤ መንገዱን ዝጋበት። አንድ ነገር ለማድረግ በተነሳህ ቁጥር የምትወድቀው ለእራስህ በሰጠሀው በገዛ አመለካከትህ ነው። ውስጥህ እንደማትችል ይነግርሃል፣ አንተም ትሰማዋለህ፤ እንግዲ አብቅቷል፣ ሊጀመር ታስቦ የነበረው ተግባር እንዳልታሰበ ተደርጎ ይተዋል፤ ይረሳል፤ ይቀለበሳል።

አዎ! ጀግናዬ..! እራስህ ለእራስህ ከምትሰጠው ሃሳብና አስተያየት በቀር የውድቀትህ ምክንያት የለም። "ዝ..ምም በል!" የምትለው ማንንም ሳይሆን አሉታዊውን የውስጥ ጩሀትህን፣ አሰናካዩን የገዛ አመለካከትህን ነው፤ በፍረሃት እያሰረ፣ በስጋት እየወጠረ፣ በሰበብ እየተበተበ ምንም ማድረግ እንደማትችል ሊያስረዳህ የሚሞክረውን ካንተ የወጣ ነገር ግን የማይገልፅህን በወረደ አስተሳሰብ የታጠረውን ማንነትህን ነው። ቅድም ሁኔታ ሳትደረድር፣ ምክንያት ሳታበዛ ይህን ሰው ዝም አሰኘው። ለዓመታት በእርሱ ስትመራ ሰንብተሃል፤ ለዘመናት በእርሱ ምክንያት ተደናቅፈሃል፤ አንገትህን ደፍተሃል፤ ከሚገባህ ኑሮ በታች ኖረሃል፤ አሁን ግን ይበቃሃል። የአሉታዊው አመለካከትህ ማብቂያ መድረሱን ለእራሱ በመንገር ልታስመሰክር ይገባል።

አዎ! አዲስ ነገር ለመጀመር በተነሳህ ቁጥር ላንተ አሳቢ በመምሰል ስጋቶችን እየደረደረ፣ በሌሉ ችግሮች እያስፈራራ፣ ጊዜያዊ ምቾቱን ብቻ እያሳደደ ያንተን ትልቅ አሳቢነት ዋጋ ቢስ ሲያደርገው ተመልክተሃል። ማንኛውም ሰው ሁለት ተቃራኒ ንግግሮችን ያስተናግዳል፤ እነርሱም የሚመነጩት ሁለት ማንነት ካላቸው ነገር ግን በአንድ ሰው ስብዕና ውስጥ በሚኖሩ ተቃራኒ አመለካከቶች ነው። የአሳቢነት መልክን የያዘው ማንነትና ትክክለኛው ትልቅነትን የሚያስብና ለትልቅነት የታጨ ማንነት። የአሳቢነትን መልክ የያዘው ማንነት በእርግጥም የሚያስብልህ ቀኑን ሙሉ ሶሻል ሚዲያ ላይ እያንከራተተህ ነው፤ ከአደጋ የሚጠብቅህ እየመሰለ በአየነ-ህሊናህ ኪሳራህን እያስመለከተህ ነው፤ በሰዎች መተቸትህን እያሳየህ ነው። ከዚህ በላይ የታላቅነት አስተሳሰብህን የሚገታ ሃይል ኬትም ሊመጣ አይችልም። ሳይውል ሳያድር፣ ከዚህ በላይ አሳስሮ ሳያስቀምጥህ በቶሎ ዝም አሰኘው፤ ትኩረትህን ንፈገው፤ ፊትህን ወደ ታላቅነት ጉዞህ አዙር።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.3K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 20:51:14 ከየትም አይመጣም!

ያልታሰበ ነገር ከየት ይመጣል? ከየትም! ሆድ ውስጥ የሌላ፣ በሃሳብ ያልተያዘ፣ በውስጣችን ያልተመላለሰ ነገር በፍፁም ወጥቶ ሊገለጥ አይችልም። በተለይ ሳይመዘን፣ ያለማስተዋል፣ ያለምንም ጥንቃቄ የሚደረግ ወይም የሚነገር ነገር ብዙ ጊዜ በአጋጣሚ ገንፎሎ የሚወጣ የውስጥ ብሶት፣ የውስጥ ተደጋጋሚ ሃሳብ የወለደው ውጤት ነው። ሆዱ ባዶ የሆነ፣ የዋህ ሰው ውስጥ ተስፋ አስቆራጭ፣ ሞራልን የሚነካ፣ አድካሚ ቃል ምንም አይሰራም። ስትናገር ልትጠነቀቅ ትችላለህ፤ ከአፍህ ከወጣ፣ በተግባር ከተገለጠ ቦሃላ ግን ምንም ልታደርግ አትችልም። ጥንቄው የሚያስፈልገው ከሆድ ሳይወጣ፣ ምላስን ሳይሻገር ነው። ከሆነና የሰውን ቅስም ከሰበረ ቦሃላ ምንም ሰበብ ብታበዛ ልታስተካክለው አትችልም። አንዴ የወጣ ቃል ዳግም ወደ ሆድ አይመለስም።

አዎ! ጀግናዬ..! ከየትም አይመጣም! ያልተዘራ ነገር አይበቅልም፤ ያልተሰራ ነገር ውጤት አያመጣም፤ ያልታሰበውም አይወራም። እንደመጣልህ ተናገር፣ እያመዛዘንክ ተናገር የምትናገርው ቀድሞ ስታስበው የነበረውንና ውስጥህ የነበረውን ነገር ነው። ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ። የልብን ካደረሱ፣ ሰውን ካሳመሙ ቦሃላ ተፀፅቶ ምክንያት ከመደርደር ከሁሉም በፊት አስቀድሞ ደጋግሞ ማሰብና መጠንቀቅ ተገቢ ነው። ንግግርህ ለዛሬ ብቻ አይደለም፤ እንደ ቀልድ የምታወጣው ቃል፣ እንደ ጫወታ የምትፈፅመው ተግባር ውጤቱ ዛሬ ላይ ብቻ የሚያቆም አይደለም። መናገርህን ብቻ ሳይሆን "ንግግሬን ማን ይሰማል?" ብለህ ጠይቅ። ማድረግህን ብቻ ሳይሆን "ድርጊቴን ማን ሊመለከተው ይችላል? ምንስ ሊያመጣብኝ ይችላል?" ብለህ ጠይቅ።

አዎ! ለምን ስድብ፣ ዛቻ፣ ማስፈራሪያ፣ አሉታዊ ንግግር አይሆንም በጊዜው አስበህበት ወይም ሳታስበው ልትናገረው ትችላለህ ነገር ግን በፍፁም ያልታሰበና በውስጥህ የሌለን ነገር በቃል ወይም በተግባር ልትገልፀው አትችልም። ምላስ አጥንት ሳይኖረው አጥንት ሰባሪ ስጋ ለበስ ጦር ነው፡፡ ጦርህን ለመልካም ነገር ተጠቀመው። ውስጥህን በአዎንታዊነት ከሞላህ፣ በቅንነት ካነፅከው፣ ሰዎችን ለመርዳት ዝግጁ ከሆንክ፣ መልካም አስተሳሰብን ካዳበርክ፣ ደግ አሳቢ ደግ አድራጊ ከሆንክ አሉታዊ የተባሉና ሰዎችን ሊሰብሩ የሚችሉ ንግግሮች ከውስጥህ ሊወጡ አይችሉም። የሌለ ነገር የለም፤ ያለስታሰበ ነገርም ከየትም እንደማይመጣ አውቀህ ሃሳብህ ላይ ስራ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.1K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 20:50:46 መንፈሳዊነትን አስቀድም!

የአለም ሩጫ ማብቂያ የለውም፤ ለፍተህ ለፍተህ እዛው ልትሆን ትችላለህ፤ እራስህን ለዚም ለዛም ሰውተህ ምንም ላታተርፍ ትችላለህ፤ ይህንንም ያንንም ሞክረህ ከየትኛውም ሳትሆን ልትቀር ትችላለህ። መንፈሳዊነት ግን እንዲህ አይደለም። አምላክን ስትመርጠው ከምንም በላይ ተመራጭ ያደርግሃል፤ እርሱን ስታስቀድም በሁሉ መንገድ ቀዳሚነትህ አጠያያቂ አይሆንም። መንፈሳዊ ስኬት ሁሌም መዳረሻው ከፍታ ነው፤ መደምደሚያው ልእልና ነው። በመንፈሳዊ ህይወትህ አትድከም፤ አምላክን ከማስቀደም አትቦዝን፤ በእርሱ ከመታነፅ ወደኋላ አትበል። መንፈሳዊነት ነፍስን ያረሰርሳል፤ ውስጥን ያረጋጋል፤ ሰላምን ይሰጣል፤ ሁለተናዊ ስኬትን ያጎናፅፋል።

አዎ! ጀግናዬ..! መንፈሳዊነትን አስቀድም፤ ፆም፣ ፀሎት፣ ስግደቱን፣ ለአምላክ መገዛቱን፣ ቃሉን ማክበሩን፣ በፍቃዱ መመላለሱን አስቀድም። ሁሌም መንፈሳዊት ቅንነትን ያድላል፤ መልካምነትን ይቸራል፤ ልብን ያበራል፤ በመከራ መሃል ያጠነክራል፤ ፅኑዕ ታጋሽ ያደርጋል፤ እውነተኛውን የሰውነት ጥግ፣ ትክክለኛውን የሰውነት ክብር ያጎናፅፋል። መንፈሳዊነት እራስህን በመውደድ ውስጥ ለሌሎችም እንድትተርፍ ያደርግሃል። አማኝ መመኪያ አለው፣ እርሱም አምላኩ ነው። ወድቆ እንደማይቀር ይተማመናል፤ እንዲሁ እንደ ቀላል እንደማይሰበር ያውቃል፤ እንዲሁ እንደዋዛ ከጀመረው መንገድ ተሰናክሎ እንደማይቀር ያምናል። በየትኛውም ሃይማኖት ውስጥ ብትሆን ያመንከውን አምላክ ከልብህ በመቀበልህና ከልብህ በእርሱ በማመንህ መንፈስህ ሲረጋጋ፣ ውስጥህ ሃሴት ሲያደርግ ትመለከታለህ።

አዎ! መንፈሳዊነትን ስታስቀድም የሚጠነክረው መንፈስህ ነው፤ የአምላክ ስጦታህ ነው፤ ማንነትህ፣ መገለጫህ ነው። በእምነትህ አትቀልድ፤ በመንፈሳዊ ህይወትህ አታሹፍ። ያላከበርከው አምላክህ እንዳንተው ባያከብርህ እራስህን እስከመጠየፍ ልትደርስ እንደምትችል እወቅ። ፈጣሪ ያነሳውን ማንም አይጥለውም፤ አምላክ የባረከውን ማንም በእርግማኑ አያረክሰውም። በመንፈሳዊነትህ ምክንያት፦ የተጫጫነህ ስንፍና፣ የተጠናወተህ ብክነት፣ እረፍት ያሳጣህ ጭንቀትና ብሶት ጥሎህ ይጠፋል። ለአምላክ የሚገባውን ስፍራ ሳትሰጥ እንዲሁ እየጦዝክና እየደከምክ ትልቁን ህልምህን ለመኖር ሳይሆን ለመጀመር ድፍረት አታገኝም። የትኛውም ትልቅ ነገር የተረጋጋ አዕምሮ፣ የሰከነ መንፈስና ውስጣዊ ሰላም ይፈልጋናል። እነዚህም የሚገኙት ከአምላክ ደጃፍ ከመንፈሳዊነት፣ ከፈሪሃ እግዚአብሔር፣ ለቃሉና ለትዕዛዙ ቅድሚያ በመስጠት ነውና ሁሌም መንፈሳዊነትን አስቀድም።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.0K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 20:50:09 አንተው መልስ ስጥ!

ያንተን ጉዳይ ለእራስህ ስጥ፤ ያንተን ጥያቄ እራስህ መልስ፤ መሰናክልህን አንሳ፤ እንቅፋትህን አስወግድ፤ ችግርህን በእራስህ የመቅረፍን ልማድ አዳብር። አዳምጦ የሚስቅ ወይም የሚፈርድ እንጂ ለጉዳይ ቦታ የሚሰጥ ሰው እንደሌለ እወቅ። ችግርህን ችግሬ፣ ብሶትህን ብሶቴ፣ ማጣትህን ማጣቴ ብሎ ዋጋ የከፈለልህ፣ ላንተ ብሎ የተሰቃይ፣ አንተ ያየሀውን አበሳ ለማየት የተፋጠነ ሰው ማነው? ስትወድቅ እንኳን ሊደግፍህ የመጣ፣ ከጎንህ የቆመ ሰው ማነው? ብዙ ጉዳይ አስፈፃሚዎች አሉ፤ ጥቂቶቹም ካንተ በላይ ያስፈፅሙልሃል፤ ጥቂቶቹ ደግሞ አንተ ተጨናንቀህ እንኳን ከምታከናውነው ደረጃ ባነስ ያከናውኑልሃል። የማንንም ብቃት መወሰን ባትችል የምትችለው ነገር አንተ የምትችለውን ማድረግ ነው።

አዎ! ጀግናዬ..! ከመናገርህ በፊት፣ ሁሉም ሰው እንዲረዳህ ከመፈለግህ በፊት አንተው እራስህን ተረዳው፤ ለእራስህ ጉዳይ አንተው እወቅበት፤ ችግርህን አንተው ፍታው፤ ለጥያቄህ አንተው መልስ ስጥ። ያንተን ትግል ማንም አይታገልልህም፤ ያንተን ችግር ማንም አይፈታልህም። ለእራስህ ጉዳይ ብቁ እንደሆንክ የምታስመሰክረው አንተ ነህ። እየዞርን ጆሮ ለማይሰጠን ሁሉ ታሪካችንን፣ ችግራችንን፣ ብሶታችንን መተረክ መሳቂያ መሳለቂያና ማነፃፀሪያ ከመሆን በቀር ምንም አያተርፍልንም። የእራሱን ችግር አሸንፎ ላንተ መፍትሔ የሚያቀርብልህ፣ ሊረዳህ ዝግጁ የሆነ ሰው ብታገኝ እጅግ እድለኛ ነህ። ነገር ግን ማንንም ሰው ብታገኝ ካንተ በተሻለ ሊረዳህ እንደማይችል እወቅ።

አዎ! ሰዎች እንዲረዱት፣ ችግሩን እንዲቀርፉለት፣ ነፃ እንዲያወጡት አብዝቶ ከሚጠባበቅ ሰው በላይ የዋህ ሰው የለም። በእያንዳንዱ ጉዞህ አምላክህ አብሮህ ካለ፣ እርሱን ካስቀደምክ ሰዎችን የምትማፀንበትን ነገር ሁሉ እራስህ የማታደርግበት ምክንያት አይኖርም። ከሰዎች በላይ በአምላክህ ታምናለህ፤ በእርሱም ትታመናለህ። ከተከመረብህ የችግር መዓት፣ አስፎ ከያዘህ አጣብቂኝ ሁነት፣ መፈናፈኛ ካሳጣህ አስጨናቂ ጉዳይ ነፃ ትወጣለህ። ለረጅም ጊዜ ችግርህን እንዲቀርፉልህ ብዙ ሰው ጠይቀሃል፤ ብዙ ሰው እግር ስር ወድቀህ ተማፅነሃል፤ ከልብህ አልቅሰህባቸዋል ነገር ግን የጠበከውን ምላሽ አላገኘህም። አምላክህን ጠይቅ፤ እራስህን ጠይቅ፤ አምላክህን ተማፀን፤ ትክክለኛውን የገዛ ማንነትህን ተማፀን፤ ፈጥኖ ምላሽ የሚሰጥህ፣ ካንተ በላይ የሚያስብልህ አምላክህ ላይ አልቅስ። ከችግሮች በላይ በበረከት፣ ከጭንቀት በላይ በውስጣዊ ሰላም፤ ከሃዘን በላይ በሳቅ ትሞላለህ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
1.0K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 20:49:36 ውጤቱ የታል?

ፅናት አልባ ችኩል ሰዎች የመጀመሪያ ጥያቄያቸው ዛሬ ጀምረህ "ውጤቱ የታል?" ነው። የማይታያቸውን ውጤት አያምኑምና ዛሬ የዘራሀው ዘር ዛሬውኑ ፍሬ አፍርቶ መመልከትን ይፈልጋሉ። ውጤት በፍጥነት ቢመጣ የሚጠላ ሰው የለም፤ ነገር ግን አንተ አብዝተህ ስለፈለከው ፈጥኖ የሚመጣ ውጤትም የለም። ሁሉም የሚሆነው በትክክለኛው ጊዜ ነው። የሚታይ ነገር ካላመጣህ የምትሰራ የማይመስላቸው ሰዎች አሉ፤ ውጤትህ ካልታየ ጥረትህን ከምንም የማይቆጥሩ ሰዎች አሉ። አንተ የሚታይህን ማንም ማየት አይጠበቅበትም፤ ማየትም አይችልም። ኬት እንደመጣህ፣ ምን ውስጥ እንደነበርክ፣ ከማን ስትታገል እንደነበር አንተ ታውቃለህ። ከእራስህ ጋር የነበረውን እልህ አስጨራሽ ፍትጊያ ያላየ ሰው ከሜዳ ተነስቶ ውጤቱ የታለ? ብሎ ቢጠይቅህ ምንም የማስረዳት ግዴታ የለብህም።

አዎ! ጀግናዬ..! የምትችለውን በማድረግህ የምትረካው አንተ ብቻ ነህ። ለሚያይህ እዛው ብትመስልም ውስጥለውስጥ መንቀሳቀስህ አንድ ቀን ያልተጠበቀውን ውጤት ያስመለክትሃል። እየተደነክ፣ እየተሞገስክ፣ እየተጨበጨበልህ ማደግን አትፈልግ። በእራስህ ጭብጨባ ካደክ ቦሃላ የሚመጣውን አደናቆትና ሙገሳ በጊዜው ታገኘዋለህ። ለተቀማጭ ሰማይ ቅርብ ነው፤ ሲነሳ ግን ርገቀቱን ይገነዘበዋል። ትልቅ ነገር ሰርቶ የማያውቅ፣ ምንም ያልሞከረ ሰው ከጅማሬው ቦሃላ፣ ከሙከራው ወዲያ ምን ሊገጥመው እንደሚችል፣ ምን ሊመጣበት እንደሚችል በቅጡ አያውቅም። ከጅማሬህ ማግስት ለውጤት የምትበቃ፣ ልክ እንደ ዘራህ ፍሬውን የምታጭድ ይመስለዋል።

አዎ! የረጅም ጊዜ እቅድህ ፈጣን ውጤት ስላላሳየህ ብቻ እንዳትተወው። ትልቅ ነገር ጊዜ ይፈልጋል፤ ህልምህ የረጅም ጊዜ ጥረት ውጤት ነው። ለመስራት ሳይሆን ለመዳኘት፣ ለመደገፍ ሳይሆን ሃሳብ ለመስጠት፣ ለማበርታት ሳይሆን ተስፋ ለማስቆረጥ ከሚጥሩ ሰዎች እራስህን ጠብቅ። መረዳት ቢችሉ ጥረትህን ብቻ እንደ ውጤት መመልከት ይችሉ ነበር፤ አዎንታዊ ቢሆኑ ከውጤትህ በተሻለ ሃሳብህን ይደግፉት ነበር። ከመጨረሻው ውጤትህ ባሻገር በሂደቱ ውስጥ መሰራትህን አስብ፤ በየጊዜ ማደግህን፣ በየደረጃው መቀየርህን አስተውል። ቢዘገይም አንድ ቀን ፍሬ የሚያፈራ ነገር ጀምረሃልና በመጨረሻው ውጤቱ ብቻ በሚዳኙህ ሰዎች አሉታዊ ቃላት ተስፋ ቆርጠህ እንዳታቆም። ያንተ ለውጥ ለእነርሱ ባይታይ ላንተ ይታይሃልና ካንተ አልፎ ለተፈለገው ወሳኝ ውጤት እስኪያበቃህ ድረስ ጥረትህን ቀጥል።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
978 viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ