Get Mystery Box with random crypto!

ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️

የቴሌግራም ቻናል አርማ mirttshefoch — ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️
የቴሌግራም ቻናል አርማ mirttshefoch — ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️
የሰርጥ አድራሻ: @mirttshefoch
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 32.43K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-05-15 18:17:55 ብቻህን ተመሰጥ!

አለምን ተመልከት፤ እረፍት የላትም፤ እለት እለት አጀንዳ አታጣም፤ አዲስ ነገር የሚያመጣ ሰው አይጠፋትም፤ የሚረብሽና ሰላም የሚነሳ ክስተት አይለያትም። አንዱ አጥፊ ሲሔድ ሌላው ይተካል፤ አንዱ በዳይ ሲያልፍ ሌላው በተራው ይመጣል። አለም መቼም የሚወራ አጀንዳ አጥታ አታውቅም፤ መቼም የሰውን የሚያስጨንቅ፣ ፋታ የሚነሳ ነገር ተለይቷት አያውቅም። በዚህ ሁኔታ ውስጥ እንዴት ብቻህን ልትሆን ትችላለህ? ብቻህን የሆንክ ይመስልሃል ነገር ግን አይደለህም። ስለ ወቅታዊው ጉዳይ የማታውቀው ነገር የለም። ዜናው አያመልጥህም፤ የሰፈሩን ወሬ አትዘለም፤ መሃበራዊ ድህረገፁ አይቀርህም። ሁሉም በእጅህ ነውና የሚሆነውን ታያለህ፤ የምትፈልገውን ትመለከታለህ፤ የተመቸህን ሰው ታወራለህ ነገር ግን በዚህ ሁሉ የተጣረሰ ምህዳር ውስጥ ተቀምጠህ ብቻህን እንደሆንክ ትብሰለሰላለህ።

አዎ! ጀግናዬ..! ብቻህን ተመሰጥ! በፍፁም ለእራስህ ነፃነት ለመስጠት ጊዜ አታባክን። የሚረብሹህን ነገሮች አያንዳንዳቸውን አጥፋቸው፤ ጥቅም ከሌላቸው ተግባሮች ተነጠል፤ እራስህን ከጫጫታ ዞር አድርግ። በምንም አይነት ሁኔታ መረጃ የማትሰማበትን ሁኔታ ፍጠር፤ ለእራስህ ብለህ እራስህን ዝም ፀጥ አሰኘው። "ብቻዬን ነኝ" እያልክ የምታለቅስበት ጊዜ አብቅቷል። ብቸኝነትህ እጅግ በጣም ውዱ ነገር ነው። ብቻህን ስትሆን የምትርቀው ከሰው ብቻ አይደለም፤ ከአምላክህ በቀር ከምንም ውጫዊ ነገር ጋር አትገናኝም። ውስጥህን በጥለቀት ትመረምራለህ፤ ትኩረትህን እራስህ ላይ ብቻ ታደርጋለህ፤ ስብራትህን ትጠግናለህ፤ ህመምህን ትፈውሳለህ፤ ውስጥህን ታጠራለህ፤ ምንያክል ለእራስህ አለኝታ መሆን እንደምትችል ታስመሰክራለህ።

አዎ! አንዳንዴ ከሰው ጋር ሆነህ ብቸኝነት ሊሰማህ ይችላል፤ የከበበህ ጫጫታ ውስጣዊ ብቸኝነትህን ላያጠፋው ይችላል። ምንም ቢሆን እራስህን ለማደስ ከብቸኝነት የተሻለ ሁኔታ አታገኝም። ጠንካራው ሰው ብቸኝነቱን እራሱን ለመጠገን የሚጠቀመው ሰው ነው። ብቻህን መወጣት ያለብህን የቤት ስራ ከማንም ጋር ልትወጣው አትችልም። ያንተ ጉዳይ ላንተ ብቻ የሚተው ነው። "ሰው የለኝም፤ ብቻዬን ቀረሁ፤ የሚረዳኝ የለም" እያላክ እራስህን በብቸኝነት አለንጋ አትግረፈው። በቻህን እንደሆንክ ይሰማሃል? ማንም እንደሌለህ ታስባለህ? እንግዲያውስ ለእራስህ አንተ አንዳለህ አረጋግጥ፤ እራስህን መታደግ እንደምትችል አሳይ። ማብቂያ በሌለው የአለም ጫጫታ አትታበይ። ውዱን ጊዜህን ለእራስህ ስጥ፤ እራሰህ ላይ ለመስራት ምንም ቅድመሁኔታ አታስቀምጥ፤ በቻልከው መጠን በብቸኝነትህ ውስጥ ተመሰጥ፤ በሚገባው ልክ ለእራስህ ተገን ሆነህ ተገኝ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
3.2K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 18:17:54 ምግብህ ቃሉ ነው!

ስጋዊ ምግብ ስጋን ያበረታል፤ ጉልበት ይሆናል፤ ሃይልን ይሰጣል። የአምላክ ቃል ግን ከእርሱ በላይ ነው፤ ስጋን ያበረታል መንፈስን ያድሳል፤ ነፍስን ያነፃል፤ ውስጥን ያረጋጋል፤ ብርታት፣ ጥንካሬ ይሆናል። እራሱን ለማበርታት የሚፈልግ፣ በማያልቀው በረከቱ መታነፅ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው መንፈሳዊ ህይወቱ ላይ መስራት ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው። ከስጋ በላይ በነፍስ ፍቃድ መመራት እጅግ ደስ ያሰኛል፤ ሰላምም አለው። የነፍስን ፍቃድ መፈፀም ከምንም በላይ የህይወት ጠዓምን ይቀይራል፤ ወደ አምላክ ያቀርባል፤ እውነተኛውን ውስጣዊ እርጋታ ያጎናፅፋል፤ የአለምን ጫጫታ ዝም ያሰኛል፤ ማንነትን በበረከት ይቃኛል። አለም ምን አለው? ከአለም ምን ይገኛል? ገንዘብ፣ ንብረት፣ ዝና። ከመንፈሳዊ ህይወትስ? ከአምላክ በረከትስ ምን ይገኝ ይሆን? እርጋታ፣ ፍፁም ደስታ፣ የአምላክ በረከት፣ የማያልቀው ምህረቱ፣ የሚያረጋጋው ቃሉ፣ ህያው ማዳኑ፣ የማያልቀው ይቅርታው።

አዎ! ጀግናዬ..! ምግብህ ቃሉ ነው! ወጣህ ወረድክ፣ ብዙ ደከምክ፣ ከልብህ ለፋህ፣ ታተርክ ውስጥህ ግን የሚፈልገውን እረፍት አላገኘም፤ የተጠማውን እርካታ አላገኘም። ከማይቋረጠው ጥረትህ በላይ እለት አለት የምታቀርበው ምስጋና፣ ከሚያደክምህ እረፍት አልባ ሩጫ በላይ በቆሸሸው ልብህም ቢሆን   የምታደርሰው ፀሎት የላቀ ዋጋ አለው፤ የተሻለ ውጤትም ያመጣልሃል። አማኝ ስለሚደረግለት ነገር፤ ስለሚደመጠው ፀሎት፣ ወደፊት ስለሚሰጠው በረከት፣ ስለሚመለስለት ጥያቄ ቀድሞ ያመሰግናል፤ ቀድሞ ይደሰትበታል፤ አስቀድሞ በሚፈልገው ውስጣዊ መሻት በፍቅር ይሞላል፤ ፍቅሩም እምነቱን ከልቡ ያፀናዋል፤ ከአምላኩ ጋር ያስተሳስረዋል።

አዎ! ዝምታህ መበቀል ስለማትችል አይደለም፤ መልስ የማትሰጠው ምላሽ አጥተህ አይደለም፤ ለበደልህ አፀፋ የማትሰጠው አቅም አነሰሶህ አይደለም። ፈሪሃ እግዚአብሔር ውስጥህ አለ፤ አምላክ ሁሉን እንደሚያይ ታውቃለህ፤ ፈጣሪ የልብህን እንደሚያውቅ ታውቃለህ። ክፉ ያደረገብህ ክፉ እንዲደርስበት አትፈልግም፤ የበደለህ እንዲበደል፣ ያሳጣህም እንዲያጣ አትፈልግም። ቢቻል የሆነው መጥፎ ነገር ሁሉ ባንተ ላይ እንዲቆም ታደርጋለህ፤ ነገሮችን ካንተ የግላዊ ጉዳት ከፍ አድርገህ ትመለከታለህ፤ የመልካምነትህ ዋጋ በአምላክ መልስ እንደሚያገኝ ታምናለህ፤ ውስጣዊ መረጋጋትህ በበቀል ወይም ያልተገባ መልስ በመስጠት እንደማይመጣ ታውቃለህ። ቃሉን ተመገብ፤ ነፍስህን አረስርስበት፤ እራስህን አንፃበት፤ አስተማሪና ተምሳሌት ህይወትን ፍጠርበት። ብትችል በማደሪያው፣ ባትችልም በማደሪያህ ጊዜ ሰጥተህ አድምጠው፤ ልብህን በማረጋጋት እንዲሰራብህ ፍቀድ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
3.5K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 16:59:01 ምርጥ ጽሑፎች pinned a photo
13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 07:16:54
አንተ ምን አረከኝ?

ለቅፅበታት ራሴን  ሆኜ ፣
ልረሳህ እልና ልቤን አጀግኜ፣
ወላዋይዋን ነፍሴን ላንዳፍታ ለምኜ፣
#የሌላ መሆንህን ውስጤን አሳምኜ

ልተውህ እልና አይኔን ረግሜ
ውብ ሳቅህን እንዳላይ ደግሜ
እንድረሳህ ብዬ ካንጀቴ እጥራለሁ
ካይንህ #ተደብቄ ቀናት ቆጥራለሁ

ሞክራለሁ እንጂ መች ረሳሀለሁ
በወሬዬ መሀል ሁሌ አነሳሀለሁ

አየህ
ያንን ሁሉ ጊዜ ላመታት ስርቅህ
#በይመጣል ተስፋ ሁሌ ምጠብቅህ

የሚባክንልህ ልቤ ሚስኪኑ፤
ልክ እንደ ድራማ ሁሌ በየቀኑ፤
አንተን እያሳየ እኔን ያከሰረኝ፤
እንዳልተውህ አርጎ አጥብቆ ያሰረኝ፤

የመልክህ ሰአሊ ለመላ አካላቴ
አንተ ምን አረከኝ ህልሜ ነው ጠላቴ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
5.0K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 07:08:42 ይሄው ነው!

እውነት ነው፤ ያለምንም ጥርጥር ከቆይታ ቦሃላ የተሻልክ ሰው ትሆናለህ፤ መጀመር ስለምታስበው ነገር ብዙ ትማራለህ፤ ብዙ ታውቃለህ፤ በተሻለ ደረጃም ትገኛለህ። አንተ ባትፈልግም የህይወት ግፊት፣ የሰዎች ጫና፣ የሁኔታዎች ከባድ መሆን በትንሹም ቢሆን ይበልጥ እንድትሰራና ለተሻለ ስፍራ እንድትበቃ ያደርግሃል። ነገር ግን በዚህ መንገድ ከመደበኛው ለውጥ የተለየ ነገር አታደርግም። ምኞትህ ልባዊ ሆኖ ተግባር ባይኖረው እንደማንኛውም ሃሳብና ምኞት እንዳለው ሰው ከመደበኛው የህይወት መዓቀፍ አትወጣም። ልዩ ነው የምትለው መርህ በውስጥህ ቢመላለስና ለመተግበር ድፍረቱ ባይኖርህ ዛሬም በነበርክበት ትቀጥላለህ። ዞሮ ዞሮ እዛው መገኘት ምንም የተለየ ጠዓም አይኖረውም።

አዎ! ጀግናዬ..! ከተግባር በቀር አትለወጥም፤ ካላደረከው ምንም አታመጣም፤ ካልጀመርክ አንዳች ነገር አትመለከትም። የትም ብትሔድ ፍረሃት አለ፤ ምንም አዲስ ነገር ለማድረግ ብታስብ መስጋትህ አይቀርም። ምክንያቱም ከለመድከው የሃሳብ እርከን ትወጣለህና፤ ምክንያቱም አድርገህ የማታውቀውን ነገር ለማድረግ ተዘጋጅተሃልና። በህይወትህ ተጨባጭ ለውጥ ማየት ከፈለክ የለውጥ ሃሳብህን አድርጎ መገኘት ምርጫ የሌለው አማራጭ ነው። ያስቀመጥካቸው ቅደመሁኔታዎች እስኪሟሉ ጊዜ ቆሞ አይጠብቅህም። የአለምን የለውጥ ፍጥነት ተመልከት፤ አንተ ግን ዛሬም በይሉኝታ ታስረህ ትጨነቃለህ። ሃሳብህ ምንም ይሁን አዎንታዊ ከሆነና ካንተ ጀምሮ የሰዎችን ህይወት የተሻለ የሚያደርግ ከሆነ ማንም ምንም ቢል ጉዳይህ ሊሆን አይገባም። ሃሳብህ መስረቅ አይደለም፤ ሃሳብህ ወንጀል መስራት አይደለም፤ ምኞትህ ሰዎችን መጉዳት አይደለም። ስለዚህ መጀመሩን ለምን ፈራሀው? ለምንስ በሰዎች አሉታዊ ቃላት ተሸበብክ?

አዎ! እርሱ ሳይመጣ አንተ ሂድለት፤ ሳያስገድድህ በውዴታ ጀምረው። ኑሮ ከብዷል፤ ሰው ክፉ ሆኗል፤ ፈተና ተደራርቧል፤ ችግር ላይ የወደቀ ሰው በዝቷል። ከዚህ በላይ ሃሳብህን መሬታ ላይ እንድታወርድ የሚያደርግህ ሁኔታ ምን ሊሆን ይችላል? አንዳንዴ የነገሮች ዋጋቸው መናር አይቀሬ ቢሆንም የእኛ በነበርንበት ስፍራ መሰንበት ደግሞ ንረቱን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል። የዛሬ አምት አመት በሚከፈልህ ደሞዝ እንዴት የዛሬውን ኑሮህን በሚገባ ተቋቁመህ ማለፍን ታስባለህ? የነገሮች ዋጋ ሲጨምር ያንተም ዋጋ በትንሹም ቢሆን መጨመር ይኖርበታል። ጊዜው ትልቅ ሃሳብ ታቅፎ ለሚያባብል ሰው አይሆንም፤ ጊዜው ምኞትን እየተመገበ ለሚኖር ሰው አይሆንም። ሁሌም ቢሆን እራስን አዘጋጅቶ መጀመር፣ ወደ ተግባር መግባት መስራት፣ መስራት ብቻ። አትፍራ፤ ለሚያድገው ህልምህ ዛሬ መሰረቱን ጣል፣ በየጊዜው በሙሉ አቅምህ ስራበት፤ በዚህ ሁኔታ በፍፁም ያለማደግ ምርጫ ሊኖረው አይችልም። ይሄው ነው፤ በርታ!
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
4.0K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  04:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 07:07:42 ቁጪትህን ቀንስ!

ህይወትህን ወደኋላ ተመልከት፤ ዳግም መፈጠር ቢቻል ዳግም በአሁኑ ማንነት የመፈጠር፣ እንደገና በመጣህበት መንገድ መምጣት፣ ሁለተኛ እዚው አሁን ያለህበት ስፍራ የመገኘት ድፍረቱ አለህን? ወይስ ዳግም በመፈጠር ውስጥ ሌላ ሰው ሆነህ፣ በሌላ መንገድ አልፈህ፣ ሌላ የተለየ ማንነትን ይዘህ መፈጠርን ትፈልጋለህ? ብዙ እራስህን እንድትወድ ወይም እንድትጠላ፤ በመጣህበት መንገድ እንድትኮራ ወይም እንድታፍር፤ በማንነትህ እንድትደሰት ወይም እንድታዝን የሚያደርጉህ ነገሮች ይኖራሉ። ያለህበትን ቦታና ማንነትህን አትወደውም ማለት ህይወትህ በቁጪት ተሞልቷል ማለት ነው፤ ውስጥህ በአሉታዊት እየተቦረቦረ ነው ማለት ነው፤ እያደር አቅም እያነሰህ፣ ወኔ እያጠረህ ነው ማለት ነው። በዚህ መንገድ ሳታውቀው እራስህን ትጎዳለህ፤ ከማትወደው ደረጃ ወዳነሰ ስፍራ በፍጥነት ትንደረደራለህ፤ መቀየር በማትችለው ታሪክህ ምክንያት አብዝተህ ትብሰለሰላለህ።

አዎ! ጀግናዬ..! ቁጪትህን ቀንስ፤ ታሪክህን ቀይር፤ አዲስ ማንነትን ፍጠር፤ የሚያኮራህን ስብዕና ገንባ። የአሁኑን ማንነትህን ካልወደድከው ልታደርግ የምትችለው ብቸኛ ነገር እለት እለት በእርሱ መበሳጨት አይደለም፤ በየቀኑ በእርሱ ማዘን አይደለም፤ ለሰዎች ማሳየትና ማስገምገም አይደለም፤ አንድና አንድ መቀየር ነው፤ ማደስ ነው። ካልፈለከውና ስሜት ካልሰጠህ፣ ካላደክበት፣ ሁሉ ነገሩ ካልተመቸህ ስለምን ተሸክመሀው ትዞራለህ? የማትወደው ልማድ ካለብህ ቀይረው፤ Just Change it. የሚያሳፍርህ አቋም ካለህ ስራበትና ለውጠው፤ የሚያስቆጭህ ታሪክ ካለ አዲስ የሚያኮራህን ታሪክ መስራት ጀምር። ለምንም ነገር ጊዜው አሁን ነው። መቁረጥ ያለብህ ግንኙነት ካለ በሚገባ ተረጋግተህ አስበህበት ቁረጠው። የትኛውም ቁስል ካልዳነ አካልህን እየጎዳና እያመናመነው ይመጣል። የሚያስቆጭህና ማንነትህን እንድትጠላ የሚያደርግህ ነገርም ካለ በጊዜ ካልተወገደና ካልተቀረፈ ከአጭሯና ውዷ እድሜህ ላይ አስደሳቿን ጊዜ እየቀነሰ ይሔዳል።

አዎ! ቀላል ስራ አይደለም፤ በትንሽ ጊዜ የሚፈፀም ነገር አይደለም፤ ስለፈለክ ብቻ የምታደርገውም አይደለም። ከፍላጎት በላይ ህመመህን በቃሀኝ ልትለው ይገባል፤ ከሃፍረትና መሸማቀቅ በላይ ዘወትር በአንድ ጉዳይ መጨነቅንና መብሰልሰለን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ልታስወግደው ይገባል። ዙሪያህን በአፅንዖት ተመልከት ተመችቶሃል አልተመቸህም? እያሳደገህ ነው ወይስ እያሳነሰህ? እየቀየረህ ነው ወይስ ወደ ባሰ አዘቅት እየከተተህ? በእራስህ ሚዛን የሚበጅህን የለውጥና የእድገት ውሳኔ ወስን። ነገሮችን በማወሳሰብ ይበልጥ አታክብዳቸው። ካሳመመህ፣ ካስጨነቀህ፣ እረፍት ከነሳህ፣ ሰላምህን ካሳጣህ ተላምደሀውና ተስማምተሀው ብትኖር እንኳን አንድ ቀን ዳግም በቁጪት መልክ መገለጡ አይቀርምና ከአሁኑ በትንሹ እርምጃ ውሰድበት፣ በሂደትም አዲሱን ተወዳጅ ማንነትን ገንባበት።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
3.8K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 06:09:56
ግን ለምን
የውስጤን ዘርግፌ እኔነቴን ብሰጥሽ
ምኞት ፍላጓቴን ገልጬ ብነግርሽ ፣
ፍቅሬን አጣጥለሽ ዝቅ አርገሽ ገመትሽው
መውደዴን አርቀሽ ማፍቀሬን ጠላሽው።
        
ውደዴን አርክሰሽ ማድነቄ አቅልለሽ ፣
መቅረቤን አውግዘሽ ፣ እንዳልነበር አርገሽ ፣
ከጓዳና ወጠሽ አጋልጠሽ ሰጠሽው ፣
ማፋቀሬን ገደልሽው ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.7K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  03:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 06:03:18 ሁለት ሰዓት ይበቃሃል!

ብዙ ሰዓት መስራት አይጠበቅብህም፤ ረጅሙን ጊዜህን እርሱ ላይ ማጥፋት አይኖርብህም። በቀን ስምንት የስራ ሰዓት አለህ፣ ሌላው ስምንት ሰዓት የእንቅልፍ ነው፤ ቀሪው ስድስት ሰዓት ለምግብ፣ ለመጠጥና ለመዝናናት ሊውል ይችላል ሁለቱ ቀሪ ሰዓት ግን ህልምህን የምትኖርበት ነው፤ ራዕይህን አቅጣጫ የምታሲዝበት ነው፤ የህይወት ትርጉምህን የምታገኝበት ነው። ህይወት ከፈተናዋና ከችግሯ ብዛት ህልምን ለመኖር ጊዜ ላትሰጥህ ትችላለች፤ በፈለከው መንገድ እንድትኖራት ላትፈቅድልህ ትችላለች። የሆነ ሰዓት የገባህበት ስራ መፈናፈኛ ያሳጣሃል፤ ሳታስበው የጀመርከው ትምህርት እረፍት ይነሳሃል፤ በአጋጣሚ የተዋወከው ጓደኛህ አጉል ልማድ ውስጥ ይከትሃል። ህልምህ ግን ሳይታሰብ የሚደረግ፣ ያለእቅድ የምትከውነው፣ በአጋጣሚ የሚሆን ነገር አይደለም። ከዘፈቀደው አኳሃን በተለየ በሚያስበው የአዕምሮ ክፍል ተመዝኖ ቦታና ጊዜ የሚመደብለት ብርቱ ጉዳይ ነው።

አዎ! ጀግናዬ..! ሁለት ሰዓት (2:00) ይበቃሃል፤ ህልሜ የምትለውን ነገር ለማሳካት፣ ህይወትህን አቅጣጫ ለማስያዝ፣ ደስተኛና የተረጋጋ ህይወት ለመኖር ገንዘብ አያስፈልግህም፤ የሰው እርዳታ አያስፈልግህም፤ የመንግስት ድጎማ አስፈልግህም። አንድ በዋናነት ሊያስፈልግህ የሚችለው ነገር ካለህ ሃያ አራት ሰዓት ውስጥ  ሁለቱን ሰዓት ብቻ ለህልምህ መስጠት ነው። ምናልባት ከህልምህ ጋር የሚገናኙ መፅሃፍትን ማንበብ ሊሆን ይችላል፤ ምናልባት በራዕይህ ዘርፍ ሰዎችን ማገልገል ይሆናል፤ ምናልባት ከህልምህ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች ሁን ብሎ ማግኘትም ሊሆን ይችላል። ስለ ህልምህ ስታወራ እህ.. ብሎ የሚሰማህን ሰው ከገኘህ እራሱ እርሱ በጣም ትልቅ ነገር ነው። ከሰማህ ቦሃላ ማረጋገጫ ባይሰጥህ እንኳን ህልምህን በቃላት ሰድረህ መግለፅ መቻልህ በእራሱ ግልፅነቱን እንድትረዳው ያደርግሃል።

አዎ! ወጥነት ያላቸው፣ በየቀኑ የማይቋረጡ የሁለት ሰዓት ድርጊቶች አሁን ሙሉ ህይወትህን እንድትመራበት ካስቻለህ የስምንት ሰዓት ስራ ነፃ እንደሚያወጣህ አትጠራጠር። የምትኖረው ህይወት ነው። መኖር ውስጥም ጠዓም አለ። ጠዓሙም የሚጎላው በምትወደውና በምትፈልገው ነገር ውስጥ ነው። የምትወደው ነገር ደግሞ ሙሉ በሙሉ ህልምህ ውስጥ አለ፤ ራዕይህ ውስጥ አለ፤ አላማህ ውስጥ አለ። ህልምህን መኖር ለመጀመር አሁን ከምትማረው ትምህርት ጋር መጋጨት አያስፈልግህም፤ ስራህን ማቆም አይጠበቅብህም፤ ሰዎች እንዲያምኑብህ መጣር አይጠበቅብህም፤ እርዳታ ከየአቅጣጫው መጉረፍ አይኖርበትም። ህልሜ ለምትለው ነገር ተገቢውን ጊዜ ስጠው፤ በየቀኑ ሁለት ሰዓት ብቻ ስራበት፣ በእርሱ ዙሪያ ግንኙነትህን አስፋ፤ እንደ ትግል ሳይሆን እንደ አስደሳች ሁነት ተመልከተው፤ በውስጡ እራስህን አድስ። በስተመጨረሻም ከምታስበው በላይ ዋጋህን እንደሚከፍልህ እመን።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.6K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  03:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 20:25:39 አትመካ!

እየተከታተለ ድክመትህን ከሚነግርህና ደካማ ጎንህን፣ ማሻሻል የሚገባህን፣ መጨመር ያለብህን ነገር ከሚነግርህ የትኛውን ትመርጣለህ? በእርግጥ ከስርስርህ ትንሿን ተግባርህን እያገነነ መሬት እንዳይበቃህ የሚያደርግህን፣ ከተግባርህ በላይ የገዢነት ስሜት እንዲሰማህ የሚያደርግህን፣ አንዳንዴም ከሆንከው በላይ ሊያሞግስህ የሚጥርን ሰው ከወረጥክ የትምክህተኝነት መንገድ ላይ እንደሆንክ አስተውል። ትምክህት እንድትታበይ፣ በሰራሀው ትንሽ ስራ እንድትመፃደቅና እጅግ የተጋነነ ስፍራን ለእራስህ እንድትሰጥ ያደርግሃል። ከሰዎች በሚዘንብልህ ተከታታይ የአድናቆት ቃል ብትመካና ብትታበይ ከማንም በላይ ውድቀትህን የምታፈጥነው አንተ ነህ። አንዳንዴ የሚገነቡህ አስተያየቶች አሉታዊ ተብለው የሚፈረጁ አስተያየቶች ናቸው። አንተ አዎንታዊ ከሆንክ አሉታዊ ሃሳብና አስተያየቶችን በአዎንታዊነት በመመልከት ለተሻለው ጥንካሬና ብርታት ልትጠቀማቸው ትችላለህ።

አዎ! ጀግናዬ..! አትመካ! ባለህ ነገር አትመካ፤ በተሰጠህ መክሊት አትታበይ፤ በደረስክበት ደረጃ አትዘናጋ። ህይወት የት እንደምታደርስህ አታውቅም። ትምክህት አንድም ለውድቀት ሌላም ለመታለል ይዳርግሃል። ምናልባት እንደምትባለው አይነት ሰው ላትሆን ትችላለህ፤ ምናልባት የተሰጠህ ስም የሚገልፅህ ላይሆን ይችላል። ባልሆንከው መመካት ሸክም እንጂ ፀጋ አይደለም። በማይገልፅህ ማንነት መኩራራት የእራስን ክብር አለማወቅ እንጂ ምንም አይደለም። የማይታይህን ድክመትህን ወዳጆችህ አይተው ቢነግሩህ ምንም ክፋት የለውም፤ ክፍተትህን አሉታዊ ከተባሉ አስተያየቶች በመነሳት ብትሞላቸው ብታተርፍ እንጂ አትጎዳም። የክፉ ቀን ወዳጅ አለ፤ ውድቀትህን አይፈልግምና ለጊዜው ቢያናድድህም የሚጠቅምህን አስተያየት ከመስጠት ወደኋላ አይልም፤ ለጊዜው ቅራኔ ቢፈጥርብህም ከጊዜያዊው ቅራኔ በላይ የሚታየው ያንተ በአስተያየቱ መታነፅና መቀየር ነው።

አዎ! ምድራዊ ነገር በሙሉ ጊዜያዊ ነው። መቼ እንደሚጠፋ አይታወቅም፤ ነገሮች መቼ እንደሚቀየሩና እንዳልነበሩ እንደሚሆኑ አይታወቅም። በሚያልፍ ነገር ብትመካ ትምክህትህም አብሮት ያልፋል፤ ባልሆንከው ማንነት ብትመፃደቅ ካለህበት ስፍራ አትንቀሳቀስም። ለውጥን ከፈለክ ባለህ ነገር አትመካ፤ እንደገትን ከተመኘህ በሰዎች ሸንጋይ ቃላት አትታበይ፤ በሚነገርህ ጊዜያዊ ማሞካሻዎች አትመፃደቅ፤ አትዘናጋ። ማደግ ለሚፈልግ፣ ለሚሰራ ሰው ከከንቱ ውዳሴ ይልቅ ቁንጥጫና ደካማ ጎኑን የሚገልፁ አስተያየቶች ይጠቅሙታል። ከአምላክህ በቀር በእራስህም አትመካ። መመካት ስትጀምር እራስህን ታካብዳለህ፤ ካንተ በላይ ሰው ያለ አይመስልህም፤ ማንም አንተን የሚፎካከር እንደሌለ ታስባለህ፤ ምንም ሳታደርግ ትልቅ ነገር እንዳደረክ እራስህን ትመለከታለህ። አትመካ፤ በገዛ መሰናክልህ እራስህን አትጣል።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
3.0K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 20:25:06 አትናቅ!

የሰው ልጅ ደክሞ የሚያጣውን ትንሽዬ ገንዘብ አትናቅ፤ የሰው ልጅ ህይወትን ለማሸነፍ ዝቅ ብሎ የሚሰራውን ስራ አትናቅ፤ የሰው ልጅ ብዙ ዋጋ ከፍሎ የደረሰበትን ደረጃ አትናቅ፤ የሰው ልጅ የሰው ፊት እየገረፈው፣ ብዙ እየተባለ የገነባውን ቤት አትናቅ። ምንም ቢሆን መናቅና ማንቋሸሽ የመጨረሻ ምርጫህ ሊሆን አይገባም። ሰዎች ነን በሰውነታችን ብቻ ሁላችንም ክብር ይገባናል። የምንናገረው፣ የምናደርገው ነገር፣ የምናጠፋው ጥፋት ከሰውነታችን ቦሃላ የሚመጣ ነገር ነው። ማንንም ወድቆ ብታየው በመውደቁ ልትንቀውና ክብርን ልትነፍገው ትችላለህ፤ ነገር ግን ነገ የት መድረስ እንደሚችል አታውቅም። ሰውን በሰውነቱ ከመለካት ይልቅ ባለው ነገር፣ ባለበት ሁኔታ፣ በገጠመው ችግር፣ በደረሰበት ነገር ለመለካት እንቸኩላለን። ሰምተህ እንዳልሰማህ ማለፍ የሚገባህ ነገር ይኖራል፣ ሰው ግን በጊዜያዊ ማንነቱና ባጣው ነገር ምክንያት ሊናቅና ሊንቋሸሽ የሚችል ፍጡር አይደለም።

አዎ! ጀግናዬ..! አትናቅ! ያጣ፣ የገረጣ፣ ከፈጣሪና ከእራሱ በላይ ምንም የሌለው ሰው ብታገኝ ከመናቅ በላይ ሃዘኔታን አስቀድም፤ በመልካምነት እጅህን ዘርጋለት። ማንም ሰው ሸክም አለበትና በሸክሙ ላይ በንቀት ውስጡን አትጉዳው። ነገሮች በምክንያት ይሆናሉ፤ ሰውን እየናቅክ ክብርን ልታገኝ አትችልም፤ ሰውን እያንቋሸሽክ በሰው ዘንድ ቦታ ሊኖርህ አይችልም። የሰጠሀው መመለሱ ሳይታለም የተፈታ ነገር ነው። ንቀት መናቅን ይወልዳል፤ ማንቋሸሽ መንቋሸሽን ያመጣል፤ መጠየፍ መገለልን ያስከትላል። ባናደርገው እንኳን ውስጣችን ያለው መጥፎ ስሜት በብዙ መልኩ ይገለጣል። አንደኛውም መገለጫ ንቀት ነው፤ ለሰዎች ክብር አለመስጠት ነው። የሰዎች ታሪክ ይቀየራል። እድሜ ልክህን አለቃ ሆነህ አትኖርም፤ እድሜህን ሁሉ መሪ ሆነህ አትቀጥልም። አንድ ቀን ከአለቅነትህ ትወርዳለህ፣ የመሪነት ስፍራህን ትለቃለህ። በተራህ አለቃ ይሾምብሃል፤ በሌላ መሪም ትመራለህ።

አዎ! በሔድክበት ሁሉ ለሰው ልጅ ክብር ይኑርህ፤ አዛኝ ልብ ይኑርህ። ውስጥህን በሚገባ አፅዳው። ውስጥህ የሚመላለሰው ሃሳብ ሁሌም ይከተልሃል። አሉታዊ አስተሳሰብ በውስጥህ ቢመላለስ ውጪም የምታገኘው የዚህኑ አስተሳሰብ ነፀብራቅ ነው። አምላክ ሰውን የሚደግፈው እራሱ ከሰማይ ወርዶ አይደለም። ይህን ሊያደርግ የሚችለውም በሰው በኩል ባንተ ነው። ሰውን ብትንቅ የምትንቀው እራስህን እንደሆነ እወቅ። አጎንብሶ የሚያገለግልህ ሰው አንድ ቀን ቀና ይላል፤ አንተ ካለህበት ስፍራም ከፍ ይላል። በደና ጊዜ ብታከብረውም ያከብርሃል፤ በደጉ ወቅት ጊዜ ብትሰጠውም ሳይሰስት ጊዜ ይሰጥሃል። የሰጠሀው መመለሱ ላይቀር እንዲደረግብህ የማትፈልገውን ነገር በማንም ላይ አታድርግ፤ በብዙ እጥፍ ማግኘት የምትፈልገውንም ለሰው ስጥ።
═════════❁✿❁ ═════════
ሶሻል ሚዲያ ያገኘነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!! የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q
2.4K viewsምኖረው እኔ ሚፈርደው ሌላ, edited  17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ