Get Mystery Box with random crypto!

ህፃን እድላዊት ፍቅሩ ገና የስምንት ወር ልጅ እያለች ነበረ በደምዋ ውስጥ የHiv ቫይረስ የተገኘባ | ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️

ህፃን እድላዊት ፍቅሩ ገና የስምንት ወር ልጅ እያለች ነበረ በደምዋ ውስጥ የHiv ቫይረስ የተገኘባት ። ከዛን ግዜ ጀምሮ በዚህ በለጋ እድሜዋ ከፀረ-Hiv መዳኒት ጋር እየታገለች መኖር የሕይወት እጣ ፋንታዋ የሆነባት የምታሳሳ ታዳጊ ህፃን ናት ።

በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ሆኖባት ከወገብ በታች ደግሞ ሙሉ ፓራላይዝድ በመሆኗ እናትዋ በወገብዋ አዝላት የዜሮ ክፍልን ጀምራ ከአንደኛ ክፍል ያቋረጠችና መማር እየፈለገች ከጓደኞቿ ተለይታ ከ6 ዓመት በላይ ከቤት ሳትወጣ መኖር ግድ የሆነባት ህፃን ናት።

ህፃን እድላዊት አሁን ላይ በብርሸለቆ የወታደር ማሰልጠኛ ካንፕ ውስጥ የምትኖርና ከአባትዋ ጡረታ በወር 1000 ብር በሚገኘው ገቢ ስለምትኖር እንኳን በቂ ሕክምና ለማግኘት ቀርቶ ለምትወስደው ፀረ - Hiv መዳኒት እራሱ የተመጣጠነ ምግብ ማግኘት ያልቻለች ልብን የምትሰብር ታዳጊ ልጅ ናት ።

እድላዊት ቢያንስ ሕክምና ማግኘት ብትችል መራመድ የምትችል ልጅ ስለሆነች ቀሪ እድሜዋ በተስፋ የተሞላ እንዲሆንላት በፈጣሪ ስም ስለ እድላዊት እማፀናችዋለሁ ።

እዚህ ቻናል ላይ እንኳን ያለነው 43 ሺህ ሰው እያንዳንዱ 1 ብር ቢልክ አስባችኋል 43ሺህ ብር ብዙ ነገር ያግዛታል ።

ወ/ሮ አታክልት ታደሰ(እናት) #1000149256532 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

0906852090 አትክልት ታደሰ