የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
እውነታው
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
25.70K
የሰርጥ መግለጫ
A channel dedicated to brighten Ethiopia through education .
We share study tips, tricks motivations and resources that will help your academic carrier.
For any questions @EducateEthiopiaBot
For any resources @EducateEthResources
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
1
3 stars
0
2 stars
1
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5
2022-11-01 10:37:17
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሁለተኛ ዲግሪ ለመማር ያመለከታችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና አርብ ጥቅምት 25/2015 ዓ.ም ጠዋት 3:00 መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
Credit: tikvahUniversity
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
2.5K viewsedited 07:37
2022-11-01 07:33:20
#MizanTepiUniversity
የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ እና ድህረ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች መግቢያ ቀን ተገለፀ።
የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ (ተመራቂ የነርሲንግና የፋርማሲ ት/ት ክፍሎች ተማሪዎች ውጭ) ለሁሉም የቅድመ እና ድህረ-ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2015 ዓ.ም ትምህርት ምዝገባ የሚካሄደው ህዳር 5 እና 6 /2015 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።
ተመራቂ ተማሪዎች የሆኑ የነርሲንግና የፋርማሲ ትምህርት ክፍሎች ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜያ ታህሳስ 3 እና 4 መሆኑ ተገልጿል።
ተማሪዎች በተጠቀሰው ቀን በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ ተብሏል።
* ከተገለጸው ጊዜ ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ ዩኒቨርሲቲው አያስተናግድም።
Credit: tikvahUniversity
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
293 viewsedited 04:33
2022-10-31 21:05:33
#Alert
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ ተማሪዎች ምዝገባን ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘሙ ይታወቃል።
ዩኒቨርሲቲው ጥቅምት 30 እና ኅዳር 01/2015 ዓ.ም የመደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ እንዲሁም ኀዳር 02/2015 ዓ.ም ትምህርት እንጀሚጀመር ማስታውቂያ አውጥቶ የነበረ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው ጥሪውን ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘሙ ይታወሳል።
"ይሁን እንጁ አንዳንድ ማንነታቸው ያልታወቁ ግለሰቦች የዩኒቨርሲቲውን ማስታወቂያ በማስመሰል ለኅዳር 05 እና 06/2015 ዓ.ም እንደጠራ አድርገው የውሸት መረጃ በማህበራዊ ድረ-ገፆች በማሰራጨት ላይ እንደሚገኙ" ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡
መረጃው ፈጽሞ ከእውነት የራቀ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አረጋግጧል።
ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ጥሪ የሚያደርግበትን ተለዋጭ ቀን እስከሚያሳውቅ ድረስ ተማሪዎቹ በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቋል፡፡
ትክክለኛ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊ ድረ ገፆችን ለመከታተል
ፌስቡክ ➤ https://www.facebook.com/mwupresidentofffice
ቴሌግራም ➤ https://t.me/mwustuoffice
Credit: tikvahUniversity
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
1.1K viewsedited 18:05
2022-10-31 17:15:15
መቱ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም በተለያዩ የትምህርት መስኮች በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም በመደበኛ እና በእረፍት ቀናት መርሃ ግብር ለመማር ለተመዘገቡ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ጥቅምት 24/2015 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 እንደሚሰጥ ገልጿል።
አመልካቾች ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ ፈተናውን መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።
ፈተናው የሚሰጠው መቱ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ፣ በበደሌ ግቢ ዋየሳ ጎታ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በቡሬ ግቢ ኒኮላስ ቦም 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
Credit: tikvahUniversity
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
1.5K viewsedited 14:15
2022-10-30 16:23:34
#WoldiaUniversity
በ2014 በመደበኛው መርሀ ግብር ፈተና ጀምረው ያቋረጡ ነባር መደበኛ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ህዳር 2-3/2015 ዓ/ም ነድ።
በጦርነት ምክንያት ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በጊዜያዊነት ተመድበው ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ህዳር 12-13 /2015 ዓ/ም ነው።
* የተግባር ልምምድ ላይ የነበሩ የ4ኛ ዓመት የሲቪል ፣ የ4ኛ ዓመት የመካኒካል፣ የ4ኛ ዓመት የኬሚካል ምህንድስና ተማሪዎች መግቢያ ህዳር 2-3/2015 ዓ/ም ነው።
Credit: tikvahUniversity
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
2.3K viewsedited 13:23
2022-10-29 13:39:29
#JinkaUniversity
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2015 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ ኅዳር 05 እና 06/2015 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።
ትምህርት የሚጀምረው ➭ ኅዳር 07/2015 ዓ.ም
ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን እንደማያስተናግድ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
Credit: tikvahUniversity
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
2.6K viewsedited 10:39
2022-10-29 10:44:38
እንኳን ደስ አላችሁ !
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥቁር አንበሳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 298 የህክምና ዶክተሮችን እያስመረቀ ነው።
በምረቃው ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ይናገር ደሴ፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሐና እና የተለያዩ እንግዶች ተገኝተዋል ።
ከዛሬ ተመራቂዎች መካከል 184 ወንዶች ሲሆኑ 114 ደግሞ ሴቶች ናቸው።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ኮሌጅ የህክምና ተማሪዎችን አስተምሮ ሲያስመርቅ ዘንድሮ ለ51 ጊዜ ነው።
#ENA
Credit: tikvah
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
2.5K viewsedited 07:44
2022-10-29 10:43:33
#JigjigaUniversity
ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የሁሉም የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የ2015 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ ኅዳር 07 እና 08/2015 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።
በቅጣት ለመመዝገብ ➭ ኅዳር 09/2015 ዓ.ም
ለበለጠ መረጃ ➭ www.jju.edu.et
ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን እንደማያስተናግድ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
Credit: tikvahUniversity
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
2.0K viewsedited 07:43
2022-10-29 09:21:30
#DebreMarkosUniversity
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ነባር የመጀመሪያ ዲግሪ እና ሁለተኛ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች የ2015 ትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ ኅዳር 08 እና 09/2015 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።
ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን እንደማያስተናግድ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
Credit: tikvahUniversity
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
1.9K viewsedited 06:21
2022-10-29 08:52:07
#BoranaUniversity
ቦረና ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 30 እና ኅዳር 01/2015 መሆኑን አሳውቋል።
በተጠቀሱት ቀናት በአካል ቀርቦ ያልተመዘገበ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
Credit: tikvahUniversity
ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
1.7K viewsedited 05:52