Get Mystery Box with random crypto!

Educate Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ educate_ethiopia — Educate Ethiopia E
የቴሌግራም ቻናል አርማ educate_ethiopia — Educate Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @educate_ethiopia
ምድቦች: እውነታው
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 25.70K
የሰርጥ መግለጫ

A channel dedicated to brighten Ethiopia through education .
We share study tips, tricks motivations and resources that will help your academic carrier.
For any questions @EducateEthiopiaBot
For any resources @EducateEthResources

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2022-10-07 17:45:02
የ85 ዓመቱ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ

አቶ ባፋ ባጋጃ ይባላሉ። የ85 ዓመት አዛውንት ናቸው። በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ከሚወስዱ ተፈታኞች መካከል አንዱ ናቸው።

የስምንት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ባፋ፤ በ1949 ዓ.ም የሰባተኛ ክፍል ተማሪ ሆነው ትምህርታቸውን እንዳቋረጡ ይገልጻሉ።

የ85 ዓመቱ አዛውንት በ2009 ዓ.ም ከ66 ዓመት በኋላ ያቋረጡትን ትምህርት በድጋሚ በመጀመር በባይራ ኮይሻ ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተዋል።

"እውቀት መቅሰም በእድሜ አይገደብም" የሚሉት አቶ ባፋ፤ ዓላማቸው ተምረው ለአገር ውለታ መስራት መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል።

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከሀድያ እና ከወላይታ ዞኖች የተውጣጡ ከ30 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በመቀበል ላይ ነው።

ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ

Credit: tikvah
1.6K viewsedited  14:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 14:43:45
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ  የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው።
----------------------------------------------

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ2014ዓ.ም  የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር ማህበራዊ ሳይንስ  ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል።

የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል( ዶ/ር ) ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ዝግጅት  ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀው ተፈታኝ ተማሪዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት እየተቀበለ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ዩኒቨርስቲው በመጀመሪያ ዙር 12,587 የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞችን ተቀብሎ የሚያስፈትን መሆኑን ገልፀዋል።

የ2014ዓ.ም የ12ኛየመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች ከ ትላንት ጀምሮ ወደ ዩኒቨርስቲዎች እየገቡ ይገኛሉ
1.8K views11:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 14:49:10
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች(የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች) ከዛሬ ጀምሮ ፈተናውን ወደ ሚወስዱበት ዩኒቨርስቲ እየገቡ ይገኛሉ።

የሰመራ፣ጎንደር፣ ዋቸሞ፣ቦንጋ እና ደብረታቦር ዩኒቨርስቲዎች በከፊል
1.7K views11:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 08:20:00
የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች በደብረ ታቦር ዩኒቨርስቲ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስፈተን የተደረገውን ዝግጅት ተመለከቱ
----------------------------------------------

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ (ዶ/ር) እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር እንዲሁም የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በደብረ ታቦር ዩኒቨርስቲ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስፈተን የተደረገውን ዝግጅት ጎበኝተዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አነጋግረኝ ጋሻው በጉብኝቱ ወቅት እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስፈተን ሰፊ እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግ መሰንበቱን ጠቁመዋል።

በተለይም ለተማሪዎች የሚሆን የምግብ፣ የመኝታ፣ የመመገቢያ እና የመፈተኛ ስፍራዎችን የማዘጋጀት ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስፈተን በመፈተኛ ክፍሎች፣ በምግብ ቤት ዝግጅት እና በተማሪዎች ማደርያ ዙሪያ አስቀድመው የተደረጉት ዝግጅቶች አጥጋቢ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስፈተን ያደረገው ዝግጅት ሰፊ፣ አስፈላጊና መሠረታዊ ጉዳዮች የተሟሉበት መሆኑን በጉብኝቱ ወቅት መታዘባቸውን አብራርተዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር !
1.9K viewsedited  05:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 15:50:01
#ማስታወቂያ

መስከረም 30/2014 ዓ.ም. ለሚጀምረው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች መስከረም 26-28 ተጠቃለው በመግባት መስከረም 29 ስለፈተናውና ተያያዥ ጉዳዮች በየተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች ገለጻ የሚደረግበት ዕለት መሆኑን መግለጻችን ይታወሳል፡፡

ሆኖም የእስልምና እምነት ተከታዮች መስከረም 28 የመዉሊድ በዓል አክብረዉ መስከረም 29/2015 ዓም እሁድ ጠዋት መግባት እንዲችሉ በልዩ ሁኔታ የተፈቀደላቸዉ መሆኑን እና የፈተና እና ተያያዥ ጉዳዮች ገለጻ /Orientation/ ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እሁድ ከሰዓት በኋላ እንዲሰጥ መደረጉን በአክብሮት እየገለጽን የእምነቱ ተከታይ ተማሪዎችም ይህንን አዉቃችሁ በተጠቀሰዉ ሰዓት በመገኘት ገለጻ /Orientation/ እንድትከታተሉ እናሳስባለን ፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር !
1.4K views12:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 15:36:47
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ(ዶ/ር) የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስፈተን ያደረገውን የቅድመ ዝግጅት ጎበኙ
_____________________________________________

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ (ዶ/ር) ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስፈተን ያደረገውን የቅድመ ዝግጅት ስራ ትናንት ማምሻውን ተመልክተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲፈተኑ መደረጉ ዓላማዎች ተማሪዎች ፈተናን በራሳቸው ሰርተው ማለፍ የሚችሉበትን ባህል መመለስ እና ፈተናን ከማጭበርበርና ከስርቆት ነጻ የማድረግ መሆኑን ገልጸዋል ።

ከዚህ በተጨማሪ ፈተናን በመስረቅ ወይም የተሳሳቱ መልሶችን በማህበራዊ ትስስር ገጾች በማሰራጨት ተማሪዎች በራሳቸው ተማምነው እንዳይሰሩ የሚደረግበትንና የሚደርስባቸውን የስነ ልቦና ጫና ለማስቀረት እንደሚያስችል ዶ/ር ፋንታ አስረድተዋል።

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ተማሪዎች ተቀብሎ እንደሚያስፈትን ጠቅሰው፤ ለዚህም የቅድመ ዝግጅት ሥራውን በአካል ተገኝተው መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።

በተለይ የተማሪዎችን የመፈተኛ፣ የመኝታና የመመገቢያ ክፍሎች መጎብኘታቸውን ገልጸው ጥሩ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።

ብሔራዊ ፈተናው ያለምንም እንከን በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን በየደረጃው ያለው አመራር ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ምንጭ;- የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ህዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት
1.1K views12:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 12:05:48
#DireDawUniversity

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ማህበር (AAU) አባል ሆኗል።

በአውሮጳውያኑ 1967 የተቋቋመው ማህበሩ፤ ለአፍሪካ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ድምጽ በመሆን እየሰራ የሚገኝ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ነው።

የማህበሩ የአስተዳደር ቦርድ የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲን የአባልነት ማመልከቻ በጥልቀት ከመረመረ በኋላ የአባልነት ሰርተፊኬት ሰጥቷል።

የማህበሩ አባል መሆኑ በርካታ የምርምር፣ መማር ማስተማር፣ ማማከር እና ሌሎች ጥቅሞችን እንደሚያስገኝለት ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል።

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ 12 የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ማህበር (AAU) አባል ናቸው።

መቀመጫውን በአክራ፣ ጋና ያደረገው ተቋሙ፤ ከ400 በላይ ዩኒቨርሲቲዎችን ከመላው አፍሪካ በአባልነት ይዟል።

ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ

Credit: tikvah
476 viewsedited  09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 07:49:47 #ለወላጆች

" ወላጆች ያምኑናል ብለን ተስፋ እንደርጋለን " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈታኞች ከቤተሰባቸው ርቀው ነው ፈተናውን የሚወስዱት በዚህ ወቅት ስልክን ጨምሮ ምንም አይነት የመገናኛ ቁሳቁስ ይዘው መሄድ አይችሉም ፤ ተማሪዎቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገናኘት ባለመቻላቸው የሚፈጠር #የስነልቦና_ጫና ይኖር ይሆን ? ይሄ እንዴት ይታያል ? የወላጆች ኃላፊነትስ ምንድነው ?

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ (የትምህርት ሚኒስትር) ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ የተናገሩት ፦

" .... ሆን ብለው ችግሮችን ለመፍጠር ካሰቡ ብዙ ምክንያቶችን ማድረግ ይቻላል ግን አሁን እነዚህ ልጆች ማትሪክ ሲያልፉ ከቤተሰቦቻቸው ወጥተው ሊኖሩ ነው አይደለም እንዴ ለረጅም ጊዜ ፤ ለአራት ቀን ለአምስት ቀን ሲሆን እንደውም በዛ እድሜ ላይ ያሉ ልጆች ደስ እያላቸው የሚሄዱ ነው የሚመስለኝ።

ይሄ አድቬንቸርም ነው ከቤት ወጥተው ፣ ዩኒቨርሲቲ ሄደው ይፈተናሉ ይሄ አዲስ ነገር ነው። በዚህ አመት ለሚያደርጉት ይሄ ነገር የተጀመረው የመጀመሪያዎቹ ተማሪዎች ስለሚሆኑ ለልጆቻቸውም የሚነግሩት ነገር ይዘው ነው የሚሆነው ፤ ታሪካዊም ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ይሄ የተደረገው ፤ በእኛ ጊዜ ነው ይሄ የሆነው ፣ ይሄ ነገር ምን አለው የሚለውን ያያሉ።

በእኛ በኩል ዋና ኃላፊነታችን ሰላማቸው እንዲጠበቅ ማድረግ ፣ በምግብ ችግር እንዳይኖርባቸው ማድረግ ፣ ህክምና ማዘጋጀት በየዩኒቨርሲቲዎቹ ይሄንን እያዘጋጀን ነው።

ሰላም መግባታቸውን ፣ ችግር በሚኖር ጊዜ ለማሳወቅ ከየክልሉ ትምህርት ቢሮ ተወካዮች አሉ አብረው የሚመጡ ወደ ግቢ አይገቡም ፤ ግን ችግር በሚኖር ጊዜ ከእነሱ ጋር ግንኙነት እየተደረገ ለቤተሰቦቻቸው መንገር የሚቻልበትን መንገድ አስቀምጠናል።

ሁሉን ነገር ለማየት ሞክረናል ይሄ ነገር አዲስ ስለሆነ ቀላል የሎጅስቲክስ ስራ አይደለም አንድ ሚሊዮን የሚደርስ ሰው አንቀሳቅሶ ይሄን ማድረግ በተወሰነ ደረጃ እንደ ሀገርም ያውም ጦርነት እየተዋጋን ባለንበት ሁኔታ መንግስት ይሄን ማድረግ መቻሉ በእውነት የሚገርም ነው። እኛ ውስጥ ስላለንበትም እያየን ስለሆነ ነው ይሄን የምናገረው ቀላል የሎጅስቲክስ ስራ አይደለም።

እጅግ በጣም ብዙ ሰው ነው የሚሳተፍበት ወደ 8 ሺ የፌዴራል ፖሊስ ይሳተፍበታል ፣ ሰላሳ / አርባ ሺህ ፈታኞች ከየዩኒቨርሲቲው ወጥተው ይሳተፋሉ ፣ ብዙ ምግብ አብሳዮች ይሳተፋሉ። በአጠቃላይ ትልቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ ነው። እንደ ሀገርም ችሎታችንን አቅማችንን፣ በተወሰነ ደረጃ እየተጠናከረ ትላልቅ ነገሮችን ለመስራት ያለን ብቃት እየጨመረ የሚሄድበት ነው ፤ ስለዚህ ደስ የሚልም ነገር አለው።

ለቤተሰቦች የምንለው በተቻለን መጠን የልጆቻችሁን ኃላፊነት ወስደን ነው ይሄን ነገር የምንሰራው። እንደ ልጆቻችን ልንጠብቅ ፣ እንደ ልጆቻችን እንዳይራቡ እንዳይጠሙ ልናደርግ ፤ ምንም አይነት የደህንነት አደጋ ውስጥ እንዳይገቡ ተጠንቅቀን ነው ይሄንን ነገር የምናደርገው። ያ ማለት ግን ምንም ነገር አይፈጠርም ማለት አይደለም መቶ በመቶ ማረጋገጫ መስጠት አይቻልም።

ማንኛውም ተማሪ ወደዚህም ቦታ ባይመጣ ቤቱም ሆኖ ሊታመም ይችላል ግን በእኛ በኩል ከህክምና ጋር በተያያዘ የጤና ባለሞያዎችን በየቦታዎቹ ላይ አስቀምጠናል ፤ ችግር በሚኖር ጊዜ ልጆቹ ህክምና እንዲያገኙ።

ቁርሳ ፣ ምሳ እንዲሁም እራታቸውን እንመግባቸዋለን ፤ ምግብ እንኳን ስናዘጋጅ የሃይማኖት ፤ የባህል ነገሮችም እንዳይመጡ እሱን ሁሉ ጥንቃቄ እያደረግን ነው። ወላጆች ያምኑናል ብለን ተስፋ እንደርጋለን።

...ወላጆች ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው። ልጆቻቸው ወደ ፈተና በሚሄዱበት ጊዜ ትብብር ማድረግ ፤ ፈተናውን ለመፈተን በሚሄዱበት ጊዜ የተከለከሉ ነገሮችን ይዘው እንዳይሄዱ ከቤት ነው ይሄ ነገር የሚጀምረው ምክንያቱም የ12 ዓመት ጥረት አፈር ነው የሚገባው አንድ የተከለከለ ነገር ይዘው ቢገቡ ፤ ስለዚህ እኛ እንደውም ፍተሻው ፖሊስ ጋር መጥቶ ከመድረሱ በፊት ቤት ወላጆች ናቸው አይተው መላክ ያለባቸው።

ወላጆች ለልጆቻቸው የሚሰጧቸው የሚያስፈልጋቸው ነገሮች ይኖራሉ ለምሳሌ ፦ እንደ ደረቅ ምግብ ድንገት ለሊት ሲያጠኑ ቢያስፈልጋቸው ቆሎም ይሁን ሌላ የሚሰጧቸው ነገር ካለ ፣ አንሶላ፣ ብርድልብስ እነዚህን እንደሚያዚዟቸው ሁሉ የዛን ያህል የተከለከሉ ነገሮችን እንዳይዙ መቆጣጠር አለባቸው፤ ይህንንም ያደርጋሉ ብለን እናምናለን።

ከዛ ውጭ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚጮኸውን አለመስማት ነው ፤ ምክንያቱም ዋነኛው ስራቸው በእንዲህ አይነት ነገር ማህበረሰብን ማሸበር እንደ ችሎታ እና እንደእውቀት የወሰዱ ጤነኛ ያልሆኑ ብዙ ሰዎች ያሉበት ዘመን ላይ ነው ያለነው።

ወላጆች የልጆቻችሁን ጉዳይ በሚመለከት በቀንጥታ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር፤ የምንነግራችሁ ቁጥሮች አሉ፣ የምንልካቸው የአካባቢው ትምህርት ተወካዮች አሉ በዛ በኩል መገናኘት ያስፈልጋል።

አንድ ነገር ቢፈጠር #በእርግጠኝነት የምንነግራችሁ ፤ ከእኛ ውሸት አትጠብቁ የሆነውን ነገር ይሄ ነው የሆነው ብለን እንነግራችኃለን። ምንም የምንደብቅበት ምክንያት የለም።

ይሄ የፖለቲካ ስራ አይደለም ፤ ይሄ የትምህርት ስራ ነው።  የትምህርት ስራ ደግሞ ሁላችንንም የሚያገናኝ እና የሚያጣብቅ ስራ ነው።

ወላጅን ከአስተማሪዎች፣ አስተማሪዎችን ከአጠቃላይ የትምህርት ስርዓቱና ከትምህርት አስተዳዳሪዎች ጋር የሚያይዘው ውስጣችን ለልጆቻችን ጤንነት ፤ ለልጆቻችን የእውቀት ጥማት እና ህይወትን ለማሻሻል የሚያደርጉትን ጥረት ከማገዝ በላይ ምንም ሌላ ነገር የለም ከዚህ የሚገኝ የፖለቲካ ጥቅም ሆነ ትርፍ የለም።

ይሄን ማወቁ ምንም የፖለቲካ ልዩነቶች እንኳን ቢኖሩ ትምህርትን የዛ መጠቀሚያ አናድርገው ፣ ትምህርትን ከዛ ውስጥ እናውጣው ትምህርት ስለልጆቻችን ነው። "

ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
868 viewsedited  04:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 14:33:25
በቅርቡ በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ባለፉት ዓመታት የተከሰቱ የፈተና ደንብ ጥሰቶች እና ማጭበርበሮች እንዳይደገሙ ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረጉን ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡

ተማሪዎች በሚፈተኑበት ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ እና በፈተና ጣቢያዎች አካባቢ ምንም ዓይነት የጸጥታ ችግር እንዳይፈጠር ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚደረግ
የአገልግሎቱ ም/ዋ/ዳይሬክተር ይልቃል ወንድሜነህ ገልጸዋል።

ፈተና ወረቀቶቹን ወደ ፈተና ጣቢያዎች ከማጓጓዝ ጀምሮ ከፍተኛ ጥበቃ እንደሚደረግ ም/ዋ/ዳይሬክተሩ አመልክተዋል።

ባለፈው ዓመት የተፈጠረው አይነት የኅትመት ላይ ስህተት እና ማጭበርበር እንዳይፈጸም የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የጥንቃቄ ሥራ መከናወኑንም ም/ዋ/ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

ተማሪዎች ወደ ፈተና ቦታዎች ሲመጡ ስልክም ሆነ መሰል የኤልክትሮኒክስ መሳርያዎች እንዳልተፈቀደ የተናገሩት ም/ዋ/ዳይሬክተሩ፤ ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት በየመጡበት ወረዳ ተወክሎ በሚመጣ አካል እና ግቢ ውስጥ ባሉ የመገናኛ ዜዴ አማራጮች እንደተቀመጡ ጠቁመዋል።

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 11/2015 ዓ.ም ይሰጣል። #አሚኮ
1.8K views11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 11:49:14
Educate Ethiopia is attending the grand opening of Ethiopian Science Museum and participating in PANAFRICON AI 2022

ኢዱክት ኢትዮጵያ በታላቁ የኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም መክፈቻ ላይ በመገኘት በፓናፍሪኮን AI 2022 ተገኝታለተች።

ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
1.8K views08:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ