የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ነው።
----------------------------------------------
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር ማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል።
የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ፋሪስ ደሊል( ዶ/ር ) ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን ገልፀው ተፈታኝ ተማሪዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት እየተቀበለ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ዩኒቨርስቲው በመጀመሪያ ዙር 12,587 የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞችን ተቀብሎ የሚያስፈትን መሆኑን ገልፀዋል።
የ2014ዓ.ም የ12ኛየመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች ከ ትላንት ጀምሮ ወደ ዩኒቨርስቲዎች እየገቡ ይገኛሉ