Get Mystery Box with random crypto!

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ(ዶ/ር) የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማ | Educate Ethiopia

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ(ዶ/ር) የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስፈተን ያደረገውን የቅድመ ዝግጅት ጎበኙ
_____________________________________________

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ (ዶ/ር) ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስፈተን ያደረገውን የቅድመ ዝግጅት ስራ ትናንት ማምሻውን ተመልክተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲፈተኑ መደረጉ ዓላማዎች ተማሪዎች ፈተናን በራሳቸው ሰርተው ማለፍ የሚችሉበትን ባህል መመለስ እና ፈተናን ከማጭበርበርና ከስርቆት ነጻ የማድረግ መሆኑን ገልጸዋል ።

ከዚህ በተጨማሪ ፈተናን በመስረቅ ወይም የተሳሳቱ መልሶችን በማህበራዊ ትስስር ገጾች በማሰራጨት ተማሪዎች በራሳቸው ተማምነው እንዳይሰሩ የሚደረግበትንና የሚደርስባቸውን የስነ ልቦና ጫና ለማስቀረት እንደሚያስችል ዶ/ር ፋንታ አስረድተዋል።

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ተማሪዎች ተቀብሎ እንደሚያስፈትን ጠቅሰው፤ ለዚህም የቅድመ ዝግጅት ሥራውን በአካል ተገኝተው መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።

በተለይ የተማሪዎችን የመፈተኛ፣ የመኝታና የመመገቢያ ክፍሎች መጎብኘታቸውን ገልጸው ጥሩ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።

ብሔራዊ ፈተናው ያለምንም እንከን በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን በየደረጃው ያለው አመራር ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ምንጭ;- የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ህዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት