Get Mystery Box with random crypto!

Educate Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ educate_ethiopia — Educate Ethiopia E
የቴሌግራም ቻናል አርማ educate_ethiopia — Educate Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @educate_ethiopia
ምድቦች: እውነታው
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 25.70K
የሰርጥ መግለጫ

A channel dedicated to brighten Ethiopia through education .
We share study tips, tricks motivations and resources that will help your academic carrier.
For any questions @EducateEthiopiaBot
For any resources @EducateEthResources

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-01-30 11:56:17
"የተገኘው የፈተና ውጤት ከስርቆትና ከኩረጃ በፀዳ መልኩ በትክክል የተመዘገበ መሆኑን ያመላከተ ነው" ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ 
-------------------------------------------

ጥር 22/2025ዓም (ትምህርት ሚኒስቴር)  የትምህርት ሚኒስትሩ  ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በ2014ዓም የ12ኛ ክፍል ፈተና የተገኘው የፈተና ውጤት ከስርቆትና ከኩረጃ በፀዳ መልኩ በትክክል የተመዘገበ መሆኑን የሚያመላክት እንደሆነ ገልጸዋል።

የዚህ አመት የፈተና ውጤት አንድምታም ለዓመታት ሲንከባለል የቆየ በርካታ ችግሮች መገለጫ እና ተሸፋፍኖ የቆየውን እውነተኛ የትምህርት ስርዓታችን ያለበትን ደረጃ  የሚያሳይ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትሩ በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የተሰጠው ፈተና ስርቆትን እና ኩረጃን ማስቀረት የተቻለበት እንደሆነ ገልፀው ውጤቱም የዚህ ማሳያ ነው ብለዋል።

በተገኘው ውጤት መሰረትም ከ 50 በመቶ በታች ያመጣ ተማሪ ወደ ዩኒቨርስቲ እንደማይገባም ተናግረዋል።

በ2014 ዓ.ም በተሰጠው ፈተና በሁለቱም የትምህርት መስክ ፈተናውን ከወሰዱት 896 ሺህ 520 ተማሪዎች ውስጥ 29 ሺህ 909 የሚሆኑት ተማሪዎች 50% እና ከዚያ በላይ ማስመዝገባቸው ተገልጿል።

በመሆኑም  በቀጣይ እንደሀገር በትምህርቱ ዘርፍ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሁሉም አካላት ቅንጅት እንደሚፈልግ ገልጸዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን  አስመልክቶ መግለጫ  መስጠቱ ይታወሳል።

Credit: MOA
4.0K views08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-29 14:32:24
ምን ያህል ተማሪዎች በማጠናከሪያ ፕሮግራም ወደ ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ?

በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ 896,520 ተማሪዎች መካከል 29,909 ተማሪዎች ብቻ በቀጥታ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚገቡ የትምህርት ሚኒስቴር መግለጹ ይታወቃል።

የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላስመዘገቡና የተሻለ ውጤት ካመጡ ተማሪዎች መካከል 100 ሺህ የሚሆኑት ተማሪዎች በደከሙባቸው የትምህርት አይነቶች በልዩ ክትትል እንዲማሩ ከተደረገ በኋላ ድጋሜ እንዲፈተኑ በማድረግ ሁለተኛ ዙር ዕድል እንደሚሰጣቸው የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

ይህም እንደ ዩኒቨርሲቲዎቹ የመቀበለ አቅምና የተማሪዎቹን ውጤት መሠረት አድርጎ በሚፈጸም የምልመላ መስፈርት የሚከናወን ነው።

ውጤት ያላመጡ ተማሪዎቹ በደከሙባቸው የትምህርት ዓይነቶች የማጠናከሪያ ድጋፍ ተደርጎላቸው በድጋሜ ፈተና እንዲወስዱ ተደርጎ የሚያልፉ ብቻ የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ይደረጋል፡፡

በፈተናው ወቅት ለሴቶች እና በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ለሚገኙ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብ ላይ እገዛ ይደረግላቸዋል ተብሏል፡፡ 

Source: Tikvah
4.4K views11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 16:19:00
#update

በ2014 የትምህርት ዘመን 899 ሺህ 520 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናውን ወስደዋል።

ከነዚህ ውስጥ ከግማሽ በላይ ውጤት ያመጡት 29 ሺህ 909 ወይም 3 ነጥብ 3 በመቶ ብቻ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር አነስተኛ በመሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አሰራር ለመከተል ማቀዱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

ከግማሽ በላይ ያመጡት 30 ሺህ ገደማዎቹ ተማሪዎች በሚቀጥለው ዓመት በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ ገብተው የአንደኛ ዓመት ተማሪ ይሆናሉ ብለዋል።

ቀሪዎቹ ደግሞ የዩኒቨርሲቲዎችን የመቀበል አቅም መሰረት በማድረግ የተሻለ ውጤት ያመጡት ተመርጠው ወደ ዩኒቨርሲቲ እንዲገቡ እንደሚደረግ አስረድተዋል።

ይሁንና እነዚህ ተማሪዎች በቀጥታ የዩኒቨርሲቲ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች እንደማይሆኑ ጠቁመዋል። ተማሪዎቹ “የደከሙባቸው ትምህርቶችን” ለአንድ ዓመት በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እየተማሩ ከቆዩ በኋላ በዓመቱ መጨረሻ ፈተና ወስደው ካለፉ በዩኒቨርሲቲዎች የአንደኛ ዓመት ተማሪ ሆነው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
5.6K viewsedited  13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 14:58:02
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ምን ምን ጉዳዮችን አነሱ ?

- በ2014 የትምህርት ዘመን ለፈተና የተመዘገቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በጠቅላላ 985 ሺህ 354 ተማሪዎች ሲሆኑ ለፈተና የቀረቡት 92 ነጥብ 2 % 908 ሺህ 256 ተማሪዎቹ ሲሆኑ 77 ሺህ 98 ተማሪዎች ፈተና አልወሰዱም።

- በደንብ ጥሰት ፣ለመኮራረጅ በመፈለግ እና በሌሎች ምክንያቶች 50 ሺህ 170 ተማሪዎች ሳይፈተኑ ቀርተዋል።

- በ2014 የትምህርት ዘመን 899 ሺህ 520 ተማሪዎች ተፈትነዋል ።

- በፆታ ማዕከልነት የአማካይ ውጤት በወንዶች 30 ነጥብ 2 እንዲሁም ሴቶች 28 ነጥብ 09 % አማካይ ውጤት አስመዝግበዋል።

- በትምህርት ዘርፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከማህበራዊ ሳይንስ በተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን የተፈጥሮ ሳይንስ 31 ነጥብ 63 ከመቶ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ 27 ነጥብ 79 ከመቶ በአማካኝ አስመዝግበዋል።

- በክልል ደረጃ ይህየ ነው የሚባል የውጤት ልዩነት የሌለ ሲሆን አዲስ አበባ ፣ ሐረሪ እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የተሻለ ውጤት አስመዝግበዋል።

- ከተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ወንድ ከ 700፤ 666 ያስመዘገበ ሲሆን 650 ሴት ተማሪ አስመዝግባለች ።

- በማህበራዊ ሳይንስ ከ600 ወንድ 524 አስመዝግቧል።

- ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር እውቅና እና ሽልማት ይሰጣቸዋል።

Credit : WMCC
4.9K views11:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 13:20:05
ከሰዓት በኋላ በ12ኛ ክፍል ውጤት ዙሪያ መግለጫ ይሰጣል።
------------------------
የትምህርት ሚኒስቴር እና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በጋራ በ12ኛ ክፍል ውጤት ዙሪያ ዛሬ ከሰዓት በኋላ መግለጫ ይሰጣሉ።

መግለጫውም ከ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በትምህርት ሚኒስቴር ቅጥር ግቢ የሚሰጥ ይሆናል።

ስለሆነም ተማሪዎች ከተዛቡ መረጃዎች እራሳቸውን በመጠበቅ ከሚመለከታቸው አካላት የሚሰራጩ መረጃዎችን ብቻ እንዲከታተሉ እናስታውቃለን።

Credit: MOE

ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
4.7K viewsedited  10:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-27 09:17:13
እስካሁን ከታየው ዝቅተኛው 120 ከፍተኛው 666 ነው።

በአጠቃላይ ከውጤት ጋር በተያያዘ ትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

እስካሁን የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ያልተደረገ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር ታውቋል ፤ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆኗል እየተባሉ የሚሰራጩ መረጃዎች ትክክለኛ አይደሉም።

Credit: tikvah

ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
5.4K views06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 18:37:22 ማስታወቂያ
ለ2014 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ተፈታኞች በሙሉ
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት የተለቀቀ በመሆኑ ተፈታኞች ከዛሬ ጥር18 2015 ዓ.ም ከሌሊቱ 5፡30 ጀምሮ፡-
• በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ወይም
• በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም
• በቴሌግራም ላይ https://t.me/eaesbot
ማየት የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
• ማንኛውም ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳያስፈልግ እስከ ጥር 26/2015 ዓ.ም ድረስ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ላይ Compliant የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማቅረብ ይችላሉ፡፡

via t.me/ethio_moe
6.4K views15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 13:11:26
ከ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት

ባለፈው ሳምንት ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር " የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መቼ ይፋ ይደረጋል ? " ብለን ጠይቀናቸው ፤ ከጥር 15 ጀምሮ ባሉት ቀናት የሚል ምላሽ ሰጥተውን ነበር።

ከነገ እንደማያልፍ " በዚገይ ደግሞ እስከ ቅዳሜ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመውናል።

ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የተሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ930 ሺ በላይ ተማሪዎች መውሰዳቸው መገለፁ የሚዘነጋ አይደለም።

Credit: tikvah

ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
6.6K viewsedited  10:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-19 22:36:25
አብርሆት ቤተ-መጻሕፍት የአባልነት ምዝገባ መጀመሩ ይታወቃል። 

የኦንላይን ምዝገባ ለማድረግ ይህን ቅደም ተከተል ይከተሉ፦

1. በ www.abrehot.org.et/register/ በመግባት የምዝገባ ፎርሙን ይሙሉ።

2. ፎርሙን እንደጨረሱ ክፍያ ገፅ ይፈጽሙ፤ ዓመታዊ የአባልነት ክፍያ በቴሌብር ወይም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል መክፈል ይችላሉ።

3. ቅድመ ተከተሉን እንደጨረሱ አባልነትዎ ይረጋገጣል።

በ15 ቀን ውስጥ ዲጂታል የአባልነት መታወቂያ በኢሜይል ይደርስዎታል።

Credit: tikvah

ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
433 viewsedited  19:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 12:14:50
ነፃ የእንግሊዘኛ ቋንቋ መማሪያ ገፅ

የትምህርት ሚኒስቴር  ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ነፃ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ ያለምንም ክፍያ  አቅርቦሎታል።

ልጆችዎ ይማራሉ  - እርስዎም የእንግሊዝኛ ቋንቋዎን ያሻሽሉበታል።

የትም ሆነው ይማሩ  የቋንቋ ክህሎትዎን ያዳብሩ!

አገልግሎቱን ለማግኘት ከታች የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ


https://learn-english.moe.gov.et/

ለበለጠ ትምህርታዊ መረጃ @educate_ethiopia ቤተሰብ ይሁኑ
668 viewsedited  09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ