Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.23K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-06-05 12:30:00 በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት የደረሰዉ የማሀበራዊ እና ስነ-ልቦናዊ ቀውስ ትኩረት ሊሰጠዉ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡
በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ከደረሰዉ ህልፈተ ህይዎት እና የንብረት ዉድመት ባሻገር የስነ ልቦና ቀውስ እና የማሀበራዊ እሴቶች መፈራረስ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች መሆናቸውን የስነ ልቦና ባለሙያዎች አሳስበዋል፡፡ ጉዳዩ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን የሚጠይቅ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
የነፃነት እና አና እኩልነት ፓርቲ ባዘጋጀዉ የድህረ ጦርነት ማገገሚያ መርሃ ግብር ላይ በጦረነቱ የደረሰዉን ዉድመት አስመልክቶ የስነ ልቦና ባለሙያዋ እጩ ዶክተር ሰብለ ሃይሉ ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡ የደረሰዉን የገንዘብ ዉድመት እና ህልፈተ ህይዎት በቁጥር ስናስቀምጥ በስነ ልቦና የተጎዱትን እና የፈረሱ ማህበራዊ መስተጋብሮችን በምንም ልንለካቸዉ አንችልም ነገር ግን የጉዳቱ ጥልቀት እና ስፋት ከፍተኛ ትኩረት ይሻል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ኢትዮጵያ ባላት የጦርነት ታሪክ ዉስጥ ሰለባ የሆኑ እና ጉዳት የደረሰባቸዉ የማህበረሰብ ክፍሎች ትኩርት ሲሰጣቸዉ አይታይም ይህም ሀገሪቷ በተደጋጋሚ ለምትገባበት የጦርነት አዙሪት አንዱ ምክንያት ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.3K views09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 12:28:00 የክልል የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሀሰተኛ የትምህርትና ሲኦሲ ማስረጃዎች መበራከታቸው ተገለጸ፡፡
በሀገሪቱ ከክልል የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚመጡ የድፕሎማ የትምህርት እና ሲኦሲ ማስረጃዎች ሀሰተኝነት አብዛኛዉን ቁጥር መያዙን የተናገሩት በኢፌድሪ ትምህርት እና ስልጠና ባለ ስልጣን የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ እና አቻ ግመታ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ገብረ መድህን ናቸው፡፡
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ እንደቆየና ጉድለቶች እየታዩ በተለይም ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን በተመለከተ የተለያዩ እርምጃዎች ሲዎሰድ እንደቆየ ጠቁመዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማስረጃዎችም ሊፈተሹ የሚገባቸዉ በመሆኑ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ወደ ተግባር ለመግባት ዝግጅቶችን እንዳጠናቀቀ ነው የተናገሩት፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የተማሪዎቻቸዉን መረጃ አሟልተዉ እንዲልኩ የተጠየቁ የግል ከፍተኛ ትምህርተ ተቋማት አብዛኞቹ አጠናቀዉ ማስገባታቸዉን እና ቀሪዎቹም በቅርብ ጊዜ ውስጥ አጠናቀዉ እንደሚያስገቡ ይጠበቃል ሲሉ ለአሀዱ ገልጸዋል፡፡
የግልም ሆኑ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርተ ተቋማት ተማሪዎች በዘንደሮዉ አመት የሚሰጠዉን የመዉጫ ፈተና በአግባቡ እንዲዎስዱና ከሀሰተኛ መረጃ እራሳቸዉን እንዲጠብቁም መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.3K views09:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 12:15:55 የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር በብሩንዲ ያደረጉት ጉብኝት ተልዕኮውን እንዳላሳካ ተነገረ
ብሩንዲ የሞስኮውን ከፍተኛ ዲፕሎማት ሰርጌ ላቭሮቭን ተቀብላ ያስተናገደች ቢሆንም የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ በዩክሬን ላይ አቋም እንድትይዝ ያደረጉት ሙከራ አለመሳካቱ ነው የተነገረው፡፡
ብሩንዲም በዩክሬንና ሩሲያ ጉዳይ ላይ ገለልተኛ አቋም እንዳላት አሳውቃለች ነው የተባለው፡፡
የብሩንዲ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አልበርት ሺንጊሮ ከሩሲያው አቻቸው ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር በዋና ከተማዋ ቡጁምቡራ ተገናኝተው ዝግ ስብሰባ ማድረጋቸው ታዉቋል፡፡
አንበርት ከስብሰባው በኋላ በሰጡት መግለጫም ብሩንዲ በመፍተሄው እንጂ በችግሩ ላይ አቋም መያዝ አትፈልግም፡፡ ብሩንዲ እንደማንኛውም ሀገር ሉአላዊት ሀገር ስትሆን አጋሮቻችንን የምንመርጠው በህዝባችን ፍላጎት ላይ ተመስርተን ነው
ብለዋል፡፡
አያይዘውም የቡርንዲ መንግስት በግጭት ላይ የሚገኙ ወገኖች በተቻለ ፍጥነት ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት እንዲመጡ እንደሚመክርና ይህም ሀገሪቱ የምትከተለው የውጭ ጉዳይ መርህ መሆኑን አስታውቀዋል ተብሏል፡፡
ዘገባው፡-የዘ ኢስት አፍሪካ ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
6.0K views09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 12:15:40 በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረዉ እርዳታ ሊቀጥል መሆኑ ተገለፀ፡፡
ወደ ትግራይ ክልል የሚገባዉ እርዳታ በተለያዩ ህገ ወጥ ምክንያቶች ተቋርጦ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን በዚህም ቁጥራቸዉ ቀላል የማይባል ዜጎች ለከፋ የምግብ እጦት ተዳርገዉ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡
የአለም የምግብ ፕሮግራም እንዲሁም የአሜሪካዉ ተራድኦ ድርጅት ዩ ኤስ አይ ዲ እየተላኩ ያሉት የእርዳታ ቁሳቁሶች በአግባቡ እየደረሱ ባለመሆኑ ምክንያት ድርጊቶቹ እስኪጣሩ ድረስ እርዳታ ማቋረጡን አሳዉቆ ነበር ፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የፌደራል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ለአሐዱ በሰጠዉ መረጃ መሰረት የእርዳታ ስራዉ መልሶ ሊቀጥል መሆኑን አመላክቷል፡፡
በዚህም በሚቀጥሉት 72 ሰአታት ዉስጥ እረዳታዎችን የመዉሰድ ስራዉ ሊጀመር እንደሚችል የተናገሩት የፌደራል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዉ አቶ አታለል አቡሃይ ናቸዉ፡፡
ተፈጥሮ የነበረዉን ችግር ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በመሆን ክትትል እናደርጋለን ነገር ግን እርዳታዉ መቀጠል አለበት በሚል በተደረገዉ ዉይይት መሰረት እንዲቀጥል መደረጉንም አንስተዋል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት የአሜሪካዉ ተወካይ ማይክ ሀመር በቀጠናዉ ባሉ ችግሮች ላይ እና በፕሪቶሪያ ስለተደረገዉ የሰላም ስምምነት አተገባበር ዉይይታ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ ይታወቃል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.6K views09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 12:15:27 የስደት እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ጋር በትብብር ለመስራት ስምምነት ማድረጋቸዉን አስታውቀዋል፡፡
ስምምነቱን ያደረጉት ከስደት እና ስደት ተመላሾች አገልግሎትና የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን በሱማሌ ክልል የቀብሪበያህ ወረዳ ላይ በጋራ ለመስራት እንደሆነ አገልግሎቱ ለአሃዱ በላከዉ መግለጫ አስታዉቋል፡፡
በሶማሌ ክልል በቀብሪበያህ ወረዳ የሀገር ውስጥ እና ከውጪ የሚገቡ ስደተኞችን አንድ ላይ በማካተት እና የአካባቢ ውህደትን የበለጠ ለመፍጠር ያለ ስምምነት መሆኑ ተገልጻል፡፡
ከ16 ሺ በላይ ስደተኞች ላለፉት 30 ዓመታት በቀብሪበያህ ወረዳ ሲኖሩ ነበር የተባለ ሲሆን በቀብሪበያህ ወረዳ እና አካባቢው የሚገኙትን የስደተኛ መጠለያዎች ወደ ወረዳዉ በማምጣት የቤት ፣ የውሀ ፣ የኤሌትሪክ ሃይል ፣ የአስተዳደር እና ሌሎች የመሰረተ ልማቶችን በአንድ እንዲያገኙ ለማድረግ ያስችላል ተብሏል፡፡
የስደት እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋሁን ጎበዜ ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ጋር በጋራ ለመስራት ከስምምነት መደረሱ በአካባቢው ለሚኖሩ የሀገር ውስጥም ሆነ የውጪ ስደተኞች በራስ መተማመን እና ሁለንተናዊ አገልግሎትን ለማጠናከር የሚጠቅም ነዉ ብለዋል፡፡
አክለዉም ኢትዮጵያ በአዉሮፓዉያኑ 2019 በተካሄደው ዓለም አቀፉ የስደተኞች ፎረም ወቅት የገባቻቸዉን ቃለ መሃላዎች ተግባራዊ ለማድረግ አስተዋፅኦ እንዳለዉ ጠቁመዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.5K views09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 12:13:44 በፖለቲካ የሃሳብ ትግል ላይ የሚፈጠሩ ልዩነቶችን ወደ ተሻለ ሃሳብ ማምጣት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፡፡
በቅርቡ ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ ፓርቲ አመራር የነበሩና አባላት ከፓርቲዉ ለቀዉ መዉጣታቸዉ የሚታወቅ ነዉ፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ከፓርቲዉ መልቀቅ ያስፈለገበት ዋነኛ ምክንያት ምንድን ነዉ፤ ለምንስ ችግሩን ዉስጥ ሆኖ መፍታት አልተቻለም የሚለዉ ጥያቄ ከአሃዱ መድረክ የተነሳላቸዉ የቀድሞ የኢዜማ ሊቀመንበር አቶ የሸዋስ አሰፋ በጉዳዩ ላይ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ፓርቲዉ የተነሳበትን አላማ ወደ ጎን በማድረግ የፓርቲዉ ሃሳብ ያልሆኑ ጉዳዮች ላይ ተጠምዷል ይሄ ደግሞ የሆነዉ አሁን አይደለም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ›
አክለዉም የሚስተካከልበትን እና ወደ ቀደመዉ አቋሙ የሚመለስበትን ስራ ለመስራት ብዙ ትግል ብናደርግም ባለመሳካቱ ምክንያት ልንለቅ ተገደናል ይህ ማለትም ፓርቲዉ ሙሉ ለሙሉ በሌሎች ፓርቲዎች ሀሳብ ተዉጧል ማለት ነዉ ሲሉ ሃሳባቸዉን ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩል ፓርቲዉ የህዝብ እንጂ ህዝብ የፓርቲ ሊሆን ስለማይገባዉ እየተካሄደ ያለዉ ተግባር ይህን ያገናዘበ ስላልሆነ ከፓርቲዉ ለመልቀቅ ተገደናል ነዉ ያሉት፡፡ ህዝብ የሚታገልለት ፓርቲ ያስፈልገዋል ያሉት አቶ የሺዋስ አሁን ላይ ግን ከፓርቲዉ የለቀቅነዉ አባላት ቀጣይ መዳረሻችን ምን እንደሆነ ወደ ፊት የምናሳዉቅ ይሆናል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
አክለዉም በፓርቲዉ ዉስጥ የሚታዩ ችግሮችን በመቅረፍ እና ፓርቲዉ እንደ ፓርቲ አቋሙን ይዞ መራመድ ሲኖርበት፤ አላማዉን ወደ ጎን በመተዉ በሰዉ ሀሳብ ተዉጧል ይህ ደግሞ ተስፋ አድርጎ የነበረዉን ህዝብ ያሳዘነ ነዉ ለምን ከተባለ የገዥዉ ፓርቲ እና የኢዜማ አቋም ፍፁም የማይጣጣም በመሆኑ ነዉ ሲሉ አቶ የሺዋስ አጽኖት ሰጥተዉ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.6K views09:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-01 16:59:02 በሰሜን ሸዋ ዞን ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ሁለት ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደት እንዳቋረጡ ተነገረ፡፡

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት በዞኑ በሚገኙ ሁለት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ይሰጥ የነበረው የትምህርት አገልግሎት መቆሙን የገለጹት የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ ታደሰ ሸዋፈራው ናቸው፡፡
ትምህርት ቤቶቹ ል አንዱ በኤፍራታና ግድም ወረዳ ጀውሃ ከተማ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር የሚገኝ መሆኑን ጠቅሰው ትምህርት ቤቶቹ ላይ ግን የደረሰ ምንም አይነት ጉዳት የለም ብለዋል፡፡ ተማሪዎች በሌሎች አካባቢዎች ትምህርት እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል፡

በአዋሳኝ አካባቢዎች በተደጋጋሚ የሚያጋጥመው የሰላም መደፍረስ ለትምህርት መቋረጡ ምክንያት መሆኑንም ገልጸው ሰላም የማምጣት ሂደቱ አስተማማኝ ሁኔታ ላይ እስኪ ደርስ መምህራንና ተማሪዎች ስጋት ውስጥ በመሆናቸው ምክንያት የተፈጠረ ነው ብለዋል፡፡በሌሎች አካባቢዎች ግን በአንጻራዊነት ሰላም በመኖሩ መደበኛ የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱ መቀጠሉን አንስተው በዞኑ የሚገኙ 51 ትምህርት ቤቶች የዘንድሮውን የ12ተኛ ክፍል አጠቃላይ ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
4.3K views13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 20:31:07 የኢራን እና የፓኪስታን መሪዎች የሁለቱን ሀገራት የድንበር ገበያ መርቀዉ መክፈታቸዉ ተገልጿል፡፡

የኢራኑ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ እና የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሻባዝ ሻሪፍ በፓኪስታን ደቡብ ምዕራብ ባሎቺስታን ግዛት የድንበር ገበያን ከፍተዋል ነዉ የተባለዉ። የፓኪስታን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ የትላንቱ ምርቃት "ፓኪስታን እና ኢራን የነዋሪዎችን ደህንነት ከፍ ለማድረግ ያላቸውን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነዉ ብሏል፡፡ የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር በሀገራቸዉ የቴሌቪዥን ጣቢያ በተላለፈው ንግግራቸዉ ሀገራቸው የኢራን ድንበር ደህንነትን ለማሻሻል የተቻላትን ሁሉ እንደምታደርግ ለራይሲ አረጋግጠዋል፡፡ አክለውም ሁለቱም ወገኖች የንግድ እና የኢኮኖሚ ግንኙነታቸውን ለማሳደግ መስማማታቸዉን አስታዉቀዋል፡፡

በኢራን እና በፓኪስታን መካከል ያለው ግንኙነት ከዚህ ቀደም አወዛጋቢ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን እልባት እያገኘ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ ዘገባዉ፡- የኢራን ዋየር ነዉ፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.7K views17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 20:15:11
እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ባደረሰቸዉ አየር ጥቃት በርካታ ፍልስጤማዉያን ከቤት ንብረታቸዉ መፈናቀላቸዉ ተገልጻል፡፡

በቅርቡ እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ ባደረሰችው የአየር ጥቃት 2 ሺ 516 ፍልስጤማውያንን ቤት አልባ አድርጓቸዋል ሲሉ የአካባቢው ባለስልጣናት አስታውቀዋል። በጋዛ የሚገኘው የማህበራዊ ልማት ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ 180 ህጻናት መኖሪያቸውን ካጡት መካከል ይገኙበታል። ሚኒስቴሩ የአረብ፣ እስላማዊ እና አለም አቀፍ ድርጅቶች በእስራኤል በጋዛ ላይ በደረሰው ጥቃት ለተጎዱ ቤተሰቦች እርዳታ እንዲያደርጉ ተማጽኗል።

የእስራኤል ጦር ባለፈው ሳምንት በጋዛ ላይ ለአምስት ቀናት በወሰደውን የአየር ድብደባ ቢያንስ 33 ፍልስጤማውያን ሲገደሉ በደርዘን የሚቆጠሩ ቆስለዋል ሲል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታዉቋል። የፍልስጤም ቡድኖች ወደ እስራኤል ሮኬት በመተኮስ አጸፋውን ወስደው ቢያንስ ሁለት እስራኤላውያንን ገድለዋል ነዉ የተባለዉ። በግብፅ አደራዳሪነት የተኩስ አቁም ስምምነት ከሁለቱም ወገን ከቀናት በፊት ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ በሃማስ የሚመራ የመንግስት ሚዲያ ጽህፈት ቤት እስራኤል በጋዛ ላይ በፈጸመችዉ ጥቃት 2 ሺ 41 መኖሪያ ቤቶች መዉደማቸዉን አስታዉቋል። ዘገባዉ የአናዶሉ ነዉ፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.6K views17:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 20:00:54 በጤና ዘርፉ ሪፖርትና ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ላይ ወሳኝ ሚና ይጫወታል የተባለው የቀጠናዊ ጤና መረጃ ስርዓት ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በመላ ሀገሪቱ ከተዘረጋ ስድስት አመት የሆነው ይህ የመረጃ ስርዓት ከዚህ በፊት ተቋማት በየፊናቸው በተበታተነ መልኩ የሚይዙትን መረጃ ወጥነት ባለው መልኩና በየደረጃው ያሉ የዘርፉ ሰራተኞች ተደራሽ በሆነ መልኩ ተግባራዊ መሆን እንደቻለ ተገልጻል፡፡ የመረጃ ስርአቱ በሁሉም መንግስታዊ እና ብዛት ያላቸው የግል የጤና ተቋማት ተዘርግቶ ስራ ላይ ሲሆን ባለፉት ጥቂት አመታት የኮቪድ 19 ምርመራ ክትባት እና ሌሎች አገለግሎቶችን የመረጃ ክትትል አሰራር ላይ ውጤታማ እንደነበር የገለጹት አቶ ገመቺስ መልካሙ በጤና ሚንስቴር የዲጂታል ጤና መሪ ስራ አስፈጻሚ ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቲቢ ህሙማንን እንዲሁም የቢጫ ወባ ክትባት የወሰዱና ያልወሰዱ ዜጎችን መረጃ አደራጅቶ በመያዝ በኩል ወሳኝ ሚና ተጫውቷል ነው ያሉት፡፡

በሪፖርት አደራረግ በኩል የግል ክሊኒኮች በየጊዜው እየተከፈቱ መዘጋት በግሉ ዘርፍ በኩል የመረጃ ፍሰቱ ላይ ችግር መፍጠሩን ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ ሌላ በቂ የሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት ግንኙነት አለመኖሩ፣ የግብዓት እጥረት፣ በመረጃ ቴክኖሎጂ እና ሌሎች ተመሳሳይ ሙያዎች ላይ የሰለጠነ የሰው ሀይል በሁሉም ተቋማት አለመኖሩ ክፍተት መፍጠሩ ተመላክቷል፡፡
አክለዉም የጤና ሚንስቴርም በየአምስት አመቱ የመረጃ ስርዓቱን የማሻሻል ስራ እንደሚሰራ አስታዉቀዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.3K views17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ