Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 22.23K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-05-15 11:25:07
አሁን ባለው ወቅታዊ የጸጥታ ስጋት ምክንያት ለቀድሞ የአማራ ልዩ ሃይል አባላት ለወራት ያልተከፈለ ደሞዝ በወቅቱ መክፈል እንዳልተቻለ ተገለጸ፡፡

በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ጉዳት ደርሶባቸው በአዲስ አበባ ለሚገኙ የቀድሞ የአማራ ልዩ ሃይል የጦር ቁስለኞች ለወራት ያልተከፈላቸውን ደሞዝ ማድረስ እንዳልተቻለ የገለጹት በቀድሞ የአማራ ልዩ ሃይል የጤና መምሪያ ሰው ሃብት አስተዳደር ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ሽታውዓለም አሰጋ ናቸው፡፡

ከባህር ዳር እስከ አዲስ አበባ የትራንስፖርት በሚስተዋለው የጸጥታ ችግር ምክንያት የፋይናንስ ባለሙያዎችን ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ በመላክ ለአባላቱ ደሞዝ መክፈል አልተቻለም ብለዋል፡፡
ለአንዳንድ አባላት በመተማመኛ እና በሂሳብ ቁጥራቸው ለወራት ያልገባላቸውን ደሞዝ መክፈል መቻሉን ገልጸው ተንቀሳቅሰው የሂሳብ ደብተር መክፈት ላልቻሉ ቁስለኞች ግን የፋይናንስ አባላትን በአየር ትራንስፖርት ወደ አዲስ አበባ በመላክ ገንዘባቸውን ለማድረስ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ቁስለኞቹ በአዲስ አበባ የተለያዩ ካምፖች በቂ የህክምና አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውንም ጠቅሰው ነገር ግን ለቀላል የህክምና አገልግሎቶች ተደጋጋሚ ቀጠሮ የመስጠት ሁኔታ እንደሚስተዋልም ገልጸዋል፡፡ ይህንንም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ችግሩ እየተቀረፈ እንዳለም አንስተዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.4K views08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 15:28:09
ኢራን ብዙ መጠን ያለው የኑክሌር ቦምብ ልትሰራ ትችላለች ስትል እስራኤል አስጠንቅቃለች፡፡

የእስራኤል የመከላከያ ሚንስትር ዮኦቭ ጋላንት በሰጡት ሰፊ ማብራሪያ ኢራን ባለችበት የአሁኑ ደረጃዋ አምስት የኑክሌር ቦምብ ለመስራት ከበቂ በላይ ዝግጅት አድርጋለች ሲሉ ነው ያስጠነቀቁት፡፡
የእስራኤሉ የመከላከያ ሚንስትር ግሪክ ውስጥ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ኢራን አምስት የኑክሌር ቦምብ ለመስራት የሚያስችላትን በሃያ በመቶና በስልሳ በመቶ የበለፀገ ዩራኒየም እንዳላት ደርሰንበታል ነው ያሉት፡፡

ጋላንት አክለውም ኢራን የዩራኒየም ማበልጸግ ስራዋን ዘጠና በመቶ ካደረሰች የመካከለኛው ምስራቅ ቀጣናም ይሁን መላዋ ዓለም ወደ ከፋ ጥፋት ማምራታቸው ነው ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡

ዘገባው፡-የሚይል ኢስት ሞኒተር ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.5K views12:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 15:21:35
በሊቢያ ለሚደረገው ምርጫ አልጄሪያ ማናቸውንም ድጋፍ ለማድረግ መሰናዳቷን አስታውቋል፡፡
በሊቢያ የፓርላማና ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለማድረግ በሚደረገው እንቅስቃሴ ሁሉ አልጄሪያ የትኛውንም ድጋፍ አንድምታደርግላት ነው ያስታወቀችው፡፡
የሁለቱ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አልጄርስ ላይ ተገናኝተው መክረዋል፡፡
ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ሊቢያ ከቀድሞ መሪዋ ፕሬዝዳንት ሙአመር አልጋዳፊ ሞት በኃላ መረጋጋት ተስኗት ህዝብቹም ለሁለት ተከፍለው በመዋጋታቸው ወደባሰ አደጋ ማምራቷ ይታወቃል፡፡
ዘገባው፡-የሚድል ኢስት ሞኒተር ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.2K views12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 14:48:44
ከመጪው ዓመት ጀምሮ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት በአስገዳጅነት የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት እንደሚተገበር ተገለፀ፡፡

ከሁለት ዓመታት በኋላ በ2017 ዓ.ም. በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ እንደሚሆን ተገልጿል፡፡
በዘንድሮዉ ዓመት በ74 የፌድራል ተቋማት ላይ እየተተገበረ ያለው የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ሥርዓት ከቀጣይ አመት ጀምሮ በሁሉም የፌድራል ተቋማት ላይ በአስገዳጅነት እንደሚተገበር የመንግስት ግዥ እና ንብረት ባለስልጣን አስታወቋል፡፡

በ2016 በጀት ዓመት 169 የፌዴራል ተቋማት የማኑዋል ግዥን አስቀርተው ሙሉ በሙሉ እንደሚተገበር እና የኤሌክትሮኒክ የግዥ ሥርዓትን፣ በሲዳማ ክልል በማሳያነት በማስጀመር በቀጣይ በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ መደረግ እንደሚጀምር የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወልደአብ ደምሴ ለአሀዱ ተናግረዋል፡፡

ወደፊት ወደ ዞንና ወረዳዎች በመውረድ የማኑዋል ግዥ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ ወደ ኤሌክትሮኒክ ግዥ የሚቀየርበት ሁኔታ እንደሚፈጠር ገልፀዋል፡፡
እስካሁን ስምንት ሺሕ ያህል አቅራቢዎች እንደተመዘገቡ ገልፀዉ በቀጣይ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ወደ አሠራሩ ሲገቡ ከ30 ሺሕ በላይ አቅራቢዎች ወደ አሰራሩ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡

የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓቱ ከንክኪ የፀዳ፣ ወጪ ቆጣቢና ቀልጣፋ፣ እንዲሁም ግልጽ መሆኑ ዘርፎቹ ለሙስና ያላቸውን ተጋላጭነት ከመቀነሱ በተጨማሪ፣ አቅራቢዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ያለ ውጣ ውረድ ተወዳድረው መሸጥ እንደሚያስችላቸዉ አክለዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.9K views11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 14:45:46
የጤና መድህን አገልግሎት በግል የህክምናና የላቦራቶሪ አገልግሎት መስጫ ተቋማት በቅርብ ጊዜ ውስጥ እንደሚጀመር ተገለጸ፡፡

የጤና መድህን አገልግሎትን በግል የህክምናና የላቦራቶሪ አገልግሎት መስጫ ተቋማት በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለማስጀመር እየሰራን ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ጤና መድህን የአገልግሎት ሰጪዎች ጥራት ማረጋገጥ ዳይሬክተር ወይዘሮ ፈለጉሽ ብርሃኔ ገልጸዋል፡፡
ይህም ከህብረተሰቡ በጤና ተቋማት የተሟላ አገልግሎት አለማግኘት ላይ ለሚነሱ ቅሬታዎች አንዱ መፍትሄ እንደሚሆን ተነግሯል፡፡

ህብረተሰቡም የአልትራሳውንድ የራጅ እንዲሁም ሌሎች የላቦራቶሪ ምርመራዎችን በጤና መድህን አገልግሎት ከግል የህክምና መስጫ ተቋማት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡
የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት በአዲስ አበባ በሚገኙ 9 የፌዴራል ሆስፒታሎች የጤና መድህን አገልግሎትን ለመስጠት ውል መያዙን ገልጸው፤ እነዚህ ውል የያዝንባቸው የህክምና ተቋማት ክፍያ በሚጠይቁበት ጊዜ በውሉ መሰረት አገልግሎት መሰጠቱን በየሶስት ወሩ በሆስፒታሎቹ በመገኘት እንፈትሻለን ሲሉም ተናግረዋል፡፡

አንድ ታካሚ ህክምና ጨረሰ የሚባለው ምርመራዎቹን አጠናቆ መድሃኒት ይዞ ወደ ቤቱ ሲሄድ በመሆኑ ተቋማቱ ሙሉ የህክምና አገልግሎቶችን ለጤና መድህን አባላት መስጠት ይኖርባቸዋልም ሲሉ አሳስበዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.6K views11:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 14:37:55
ከጅቡቲ ወደብ እስከ መሀል ሀገር እቃ ይዘው በሚመጡ የኢትዮጵያ ባህር እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ተሽከርካሪዎች ዘመናዊ መቆጣጠሪያ መገጠሙ ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ባህር እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የጭነት አስተላላፊ ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሲራጅ አብዱላሂ የድርጅቱ ተሸከርካሪዎችም ሆነ በአጋርነት የሚሰሩ ሌሎች ተሸከርካሪዎች ላይ ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ መሳሪያ ቴክኖሎጂ ለመግጠም ስንሰራ ነበር ያሉ ሲሆን የድርጅቱ ንብረት የሆኑ ሁሉም ተሸከርካሪዎች መሳሪያው ተገጥሞላቸዋል ብለዋል፡፡
ተሸከርካሪዎቹ የተገጠመላቸው ጂፒኤስ በማንኛውም ሰዓት የት እንዳሉ እና የስምሪት መስመራቸውን ለመቆጣጠር ያስቻላል ብለዋል፡፡

ነገር ግን ከአገልግሎት ድርጅቱ ጋር በኮንትራት የሚሰሩ የመልቲ ሞደልም ሆነ የብትን ጭነት የሚያጔጉዙ የግል ተሸከርካሪዎች ቴክኖሎጂው እንዳልተገጠመላቸው ገልጸዋል፡፡
አክለውም የትራንስፖርት ሚኒስቴር ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በአዲሱ የትራንስፖርት ማህበራት አደረጃጀት ተሸከርካሪዎቹ እነዚህን ቴክኖሎጂዎች ተግባራዊ ሲያደርጉ አጠቃላይ ዘርፉን አሰራር ያሻሽለዋል ብለን እንጠብቃለን ብለዋል፡፡

በዚህ ዓመት የተሽከርካሪዎች የጂቡቲ ወደብ ቆይታ በአማካይ ስምንት ቀን ለማድረስ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም እቅዱን ማሳካት እንዳልተቻለ እና ቆይታቸው ሃያ አራት ቀን እንደሆነ መገለፁ የሚታወስ ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
3.2K viewsedited  11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 17:04:21
ሳውዲ አረቢያ ለኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች እንዲከፈል የወሰነችው የክፍያ ተመን ዝቅተኛ የሆነው ከ5 አመት በፊት የተደረገውን ስምምነት ተከትሎ እንደሆነ ተገለፀ፡፡
የሳውዲ አረቢያ የሰው ሃብት ሚንስቴር በተለያዩ 8 አገራት ለሚመጡ የቤት ሰራተኞች የክፍያ ጣሪያ ተመን ይፋ ያደረገ ሲሆን ለኢትዮጵያውያን እንዲከፈል የተወሰነው ግን ከሁሉም አገራት ዝቅተኛው ሲሆን ይህም 6900 የሳውዲ ሪያል እንደሆነ አስታውቋል፡፡
ይህንንም አስመልቶ የኢትዮጵያውያኑ ክፍያ በምን ምክንያት ከሌሎቹ ዝቅተኛ ሊሆን ቻለ ሲል አሐዱ የስራ እና ክህሎት ሚንስቴርን ያነጋገረ ሲሆን ከዚህ ጋር በተያያዘ ከሳውዲ አረቢያ የሰው ሀብት ሚንስቴር እንዲሁም ከሀገሪቱ አምባሳደር ጋር ውይይት መደረጉን የስራ እና ክህሎት ሚንስቴር የሰራተኛ ዘርፍ ሚንስቴር ዲኤታ አቶ አሰግድ ጌታቸው አስታውቀዋል፡፡
ክፍያው በዚህ ልክ ዝቅተኛ የሆነበት ምክንያት ከክፍያ ጋር በተያያዘ ለመጨረሻ ጊዚ የሁለትዮሽ ስምምነት የተደረገው ከ5 አመት በፊት የነበረ ሲሆን ከዚያ በኋላ ማሻሻያ ስላልተደረገበት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
በቅርቡም 3 ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከሰራተኞች ክፍያ ጋር በተያያዘ አዲስ የሁለትዮሽ ስምምነት እንደሚደረግ ገልጸው አሱን ተከትሎም ይፋ በተደረገው የክፍያ መጠን ላይ ተገቢውን ማሻሻያ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡
አያይዘውም አሁን ላይ ሳውዲ አረቢያን ጨምሮ ወደ ተለያዩ አገራት የሚያቀኑ የቤት ሰራተኞች ከበፊቱ በተሻለ መልኩ ብቃት እና የመግባባት ክህሎት እንዲኖራቸው የሚያግዝ ስልጠና እንዲያገኙ እየተደረገ ሲሆን ይህንን ታሳቢ ያደረገ ክፍያ እንዲያገኙ ከአገሪቱ መንግስት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን ጠቁመዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
1.8K views14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 16:59:23
የህጻናት አድን ድርጅት በቦረና በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ህፃናት እና እናቶች ድጋፍ በማሰባሰብ ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡

አለማቀፉ የህጻናት አድን ድርጅት ሴቭ ዘ-ችልድረን በኢትዮጲያ ባሳለፍነው ሳምንት በሰጠው መግልጫ በትግራይ ክልል በጦርነቱ ለተጎዱ እናቶች አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል፡፡
በቦረና በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ህፃናት እና እናቶች ድርጅቱ ምን እያከናወነ ነው ሲል አሐዱ የጠየቃቸው የዓለምአቀፉ የህጻናት አድን ድርጅት በኢትዮጵያ ቃል አቀባይ ህይወት እምሻው እንደገለጹት ድርጅቱ በአፋር ክልል እና በሶማሊያ ክልል አስፈላጊውን እርዳታ ሲያደርግ እንደነበር ገልጸው በአሁኑ ወቅትም በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ህፃናት እና እናቶች አስፈላጊውን እርዳታ ለማቅረብ የኦሮሚያ መንግስት ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ገንዘብ የማሰባሰብ ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

የዓለምአቀፉ የህጻናት አድን ድርጅት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ድጋፍ እያደረገ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.7K views13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 16:58:38
የተባበሩት መንግስታት የኑክሌር ተቆጣጣሪ በሊቢያ 2.5 ቶን ዩራኒየም መጥፋቱን አስታዉቋል፡፡
በጦርነት በምትታመሰው ሊቢያ ውስጥ በአንድ ጣቢያ ውስጥ የተከማቸ 2.5 ቶን የተፈጥሮ ዩራኒየም ጠፍቷል ሲል የተባበሩት መንግስታት የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ተቋም ገልጻል።

የመንግስታቱ ድርጅት የኑክሌር ተቆጣጣሪ ተቋም ባውጣው መግለጫ አሁን ከሊቢያ የጠፋው ግዙፍ መጠን ያለው ዩራኒየም የራዲዮአክቲቭ አደጋ የሚያስከትልና የፀጥታ ስጋት እንደሆነም ነው ያስታወቀው፡፡

እንደ ዓለማቀፉ የአቶሚክ ሀይል ተቆጣጣሪ ተቋም ሪፖርት ከሊቢያ መጥፋቱ የተነገረለት የተፈጥሮ ዩራኒየም መጠን በግምት 2 ነጥብ 5 ቶን እንደሚሆን ያሳያል፡፡

ይኸው ጠፍቷል የተባለው የተፈጥሮ ዩራኒየም መጥፋቱ የተገለጸው በመንግስት ቁጥጥር ስር ካለው ስፍራ ሳይሆን ከሌላ አካባቢ መሆኑንም ነው የዓለማቀፉ የአቶሚክ ሀይል ተቆጣጣሪ ተቋም ያስታውቀው፡፡

በቪየና የሚገኘው አለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ባወጣው መግለጫ ላይ ዋና ዳይሬክተሩ ራፋኤል ማሪያኖ ስለጎደለው ዩራኒየም ለአባል ሀገራቱ ማሳወቃቸዉን ጠቅሷል።
የተቋሙ ዋና ኃላፊ በሰጡት ማብራሪያ የጠፋውን ዩራኒየም የማፈላለጉና የምርመራ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት፡፡

ሮይተርስ በመጀመሪያ ስለጠፋው የሊቢያ ዩራኒየም የማስጠንቀቂያ ዘገባ ሰርቶ እንደነበር የፎክስ ኒዉስ ዘገባዉ አስታዉሷል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.5K views13:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-17 16:55:34
አሜሪካ ከ26 ወራት በኃላ ወደ ህንድ አባሳደሯን ልትልክ ነዉ፡፡

የተከፋፈለው የአሜሪካ ሴኔት ረቡዕ መገባደጃ ላይ የሎስ አንጀለስ ከንቲባ የነበሩት ጋርሴቲ በህንድ የአሜሪካ አምባሳደር መሆናቸዉን 52 ለ42 በሆነ ድምጽ አረጋግጧል፡፡
አሜሪካ በህንድ ውስጥ የአምባሳደርነት ስራዋን ለ26 ወራት ባዶ አድርጋ ትታዉ መቆየቷን ያስታወሰዉ ዘገባዉ ይህም በህንድና በአሜሪካ ግንኙነት ዉስጥ ያለ አባሳደር ግንኙነት የቆየ ረጅሙ ጊዜ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ክፍተቱ የመጣው ዓለም አቀፋዊ ውጥረት እየጨመረ በሄደበት ወቅት ነው፡፡ ምንም እንኳን የአሜሪካ እና የህንድ መሪዎች ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የቅርብ አጋር ሆነናል ቢሉም ያለ አባሳደር ሹመት 26 ወራት ግኙነታቸዉ ቀጥሎ እንደነበር ይጠቀሳል፡፡

የአሜሪካዉ ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን ባለፈው አመት ለጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ እንደተናገሩት “በምድር ላይ ካሉን በጣም ቅርብ ከሆኑት ወዳጆቻችን መካከል ህንድ ቀዳሚዋ ናት ማለታቸዉ ይታወሳል።
ህንድ በሕዝብ ብዛቷ በዓለማችን ከሚጠሩ ሀገራት መካከል ናት፡፡ አሜሪካ ደግም ብዙን ጊዜ በእስያ በምታደርገዉ ቅኝት ህንድን ከ2 ሺ ማይል በላይ ድንበር ከምትጋራት ቻይና ጋር እንደ አንድ የምሽግ ስፍራ አድርጋ ትቆጥራታለች ነዉ የሚባለዉ፡፡
ዘገባዉ የኤን ፒ አር ነዉ፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.4K viewsedited  13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ