Get Mystery Box with random crypto!

AHADU RADIO FM 94.3

የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3 A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ahaduradio — AHADU RADIO FM 94.3
የሰርጥ አድራሻ: @ahaduradio
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.04K
የሰርጥ መግለጫ

አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2023-03-06 16:55:57
የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የ12ኛ ክፍል የአቅም ማሻሻያ ትምህርት መስጠት እንደሚችሉ ተገለጸ፡፡
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ከ95 በመቶ በላይ የሚሆኑት ተማሪዎች ከ50 በመቶ በታች ውጤት ማምጣታቸው ይታወቃል፡፡
ከሀምሳ በመቶ በታች ካመጡት ተማሪዎች መካከል በልዩ ሁኔታ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው ለአንድ አመት የአቅም ማሻሻያ ትምህርት ሪሜዲያል እንዲወስዱ የተወሰነ ሲሆን ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተጨማሪ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትም የአቅም ማሻሻያ ትምህርት መውሰድ እንደሚችሉ የትምህርት ሚንስቴር የህዝብ ግንኙት ሃላፊ ወ/ሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል ለአሀዱ ገልፀዋል፡፡
ትምህርት ሚንስቴር ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ያደረገ ሲሆን ይህን የአቅም ማሻሻያ ትምህርት መስጠት የሚፈልጉ የግል ከፍትኛ የትምህርት ተቋማትም በዚሁ መሰረት ተማሪዎች ተቀብለው ማስተማር የሚችሉ ሲሆን በቅድሚያ ግን የመዘገቧቸውን ተማሪዎች ለትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን ማሳወቅ እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የልህቀት ማእከል ተብለው በተለዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በኩል የተዘጋጀ የአቅም ማሻሻያ ሪሜዲያል ትምህርት ማስተማሪያ ተዘጋጅቶ ለሁሉም የመንግስት እና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መላኩን ጠቁመዋል፡፡
አያይዘውም የማስተማሪያ ሰነዱ ለተማሪዎቹ ከ 9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርት አጠቃሎ የያዘ ሲሆን ሁሉም የትምህርት ተቋማት ማስተማር የሚችሉት ይሄንን በመጠቀም መሆን እንዳለበት አመላክተዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutele
2.4K views13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 16:52:40
ክልሎች እርስ በእርሳቸዉ የሚያደርጉት ግንኙነት በህገ-መንግስቱ መሰረት መሆን እንደሚገባዉ ተገለፀ፡፡
ክልሎች እርስ በእርሳቸዉ የሚኖራቸዉ መስተጋብር ህገ መንግስቱን መሰረት ባደረገ እና የህግ የበላይነትን ባሰፈነ መልኩ መሆን እንደሚገባዉ አሀዱ ያነጋገራቸዉ የህግ ባለሙያዎች ገልፀዋል፡፡፡
እርስ በእርሳቸዉ የሚኖራቸዉን ችግር ወደ ህዝቡ በማውረድ ጠብን መዝራት እንደማይገባቸዉ እና እንዲህ አይነት አካሄዶች ሊቆሙ እንደሚያስፈልግ የህግ ባለሙያዉ አቶ አበባዉ አበበ ተናግረዋል፡፡
በመካከላቸው የሚኖሩ ችግሮችን መፍታት በህገ መንግስቱ በተቀመጠዉ ድንጋጌ መሰረት የፌደራል መንግስቱ ሀላፊነት መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የቃላት ጦርነቶች ወደ ከፍተኛ ችግር እንዳይስፋፉ አስቀድሞ መፍትሄ ማበጀት እንደሚገባም አመላክተዋል፡፡
በህገ መንግስቱ በተቀመጠዉ መሰረት ክልሎች እራስን በራስ የማስተዳደር መብት እንዳለቸዉ የሚታወቅ ሲሆን እርስ በእርሳቸዉ የሚኖራቸዉም ግንኙነት በህገ- መንግስቱ አማካኝነት መሆን እንደሚገባዉ የህግ ባለሙያዉ አቶ ካፒታል ክብሬ ተናግረዋል፡፡
የክልሎች ተግባር ህገ መንግስቱን የሚቃረን እየሆነ በመምጣቱ እንደነዚህ አይነት አካሄዶች እየሰፉ ሄደዉ ችግር ከማምጣታቸዉ በፊት የፌዴራል መንግስት ሊፈታዉ ይገባዋል ብለዋል፡፡
ክልሎች እርስ በእርሳቸዉ የሚያደርጉት የቃላት ጦርነትን ጨምሮ በህግ የተቀመጠላቸዉን አካሄድ በመተዉ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ፌድራል መንግስቱ ሊያስቆም እና እልባት ሊሰጠዉ እንደሚገባ የህግ ባለሙያዎቹ አመላክተዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
2.0K views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 16:43:06 በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች ከሚሰጠዉ ትኩረት በላይ ለመልሶ ግንባታ የሚሰጠዉ ትኩረት ማየሉ ተገለጸ፡፡
ላለፉት ሁለት አመታት ሲካሄድ የቆየውን የሰሜኑ የሃገሪቱ ክፍል ጦርነት ተከትሎ በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ዞን በርካታ ዜጎች የተፈናቀሉ ሲሆን አሁን ላይም በዞኑ ሁለት ጊዜያዊ የመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ያሉ ከ70 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች ከፍተኛ ችግር ውስጥ መሆናቸውን የዋግኽምራ ዞን የአደጋ መከላከልና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምላሽ ቡድን መሪ ዝናሽ ወርቁ ለአሃዱ ገልጸዋል፡፡
ካሉት ተፈናቃዮች መካከል እናቶችና ህጻናት ትልቁን ድርሻ እንደሚይዙ የገለጹት ሃላፊዋ ተፈናቃዮቹ ያሉበትን የችግር ደረጃ ከግምት ያስገባ ትኩረት እየተሰጠ አይደለም ብለዋል፡፡
ዞኑ ለአማራ ክልል አደጋ ስጋት ቢሮ ተደጋጋሚ ቅሬታ ማቅረቡንም ገልጸው ‹‹ለተፈናቃዮች ከሚደረገው ድጋፍ ይልቅ ለተቋማት መልሶ ግንባታ ይበልጥ ትኩረት ሲሰጥ አስተውለናል ፣ ይህ ደግሞ ተገቢ አይደለም›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡
‹‹አሁን ባለው ሁኔታ በየ 1 ወሩ የሚደረገው የምግብ ድጋፍ የቀጠለ ቢሆንም ለነፍሰ-ጡር እናቶችና ለጨቅላ ህጻናት ተጨማሪ የምግብ ድጋፍ ያስፈልጋል ፣ ነገር ግን እነዚህን ድጋፎች ካለፈው ህዳር ወር በኋላ ያቀረበልን አካል የለም›› ነው ያሉት፡፡
ይህንን በተመለከተ አሃዱ ያነጋገራቸው የብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ በበኩላቸው በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች ያለው የተፈናቃዮች አሃዝ ከፍተኛ መሆኑን ተከትሎ ውስንነቶች እንዳሉ አንስተዋል፡፡
ሆኖም በተቻለ መጠን እርዳታዎችን ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እያደረግን ነው ፤እርዳታን በተመለከተ ተደጋጋሚ ቅሬታዎች ቢቀርቡም ተቋሙ ከዞንና ወረዳዎች ጋር ሳይሆን ከክልል አደጋ ስጋት ቢሮዎች ጋር በመቀናጀት የተቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው ሲሉም አክለዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.2K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 16:50:15
የመድኃኒት አቅርቦትን ስራ ውጤታማ እና ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የአቅጣጫ እና የፖሊሲ መሻሻያዎች አስፈላጊ መሆናቸዉ ተገለፀ፡፡
በዓለማቀፍ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ተግዳሮቶች በመፈተን ላይ ያለውን የመድኀኒት አቅርቦት ሰንሰለትን ለማሻሻል የአቅጣጫ እና የፖሊሲ ድጋፍ አስፈላጊ በመሆኑ በጉዳዩ ላይ ከፕላንእና ልማት ሚንስቴር ጋር በመወያየት መግባባት ላይ መደረሱን የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት የኮምዩንኬሽን ዳይሬክተር አቶ አወል ሀሰን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
ለማህበረሰቡ የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሻሻል እየተሰራ ያለው ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና በቀጣይም የአገልግሎቱን ስራ ውጤታማ እና ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የፖሊሲ ማዕቀፍን በማሻሻል ረገድ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአቅርቦት ሰንሰለቱ የብዙ የባለድርሻ አካላት ሚና ያለበት በመሆኑ ለስራዉ እንቅፋት የሆኑ ነገሮች እንዲፈቱ የበርካታ አካላት ሚና የጎላ መሆኑን አስታዉቀዋል፡፡
ከአዋጅ ፤ከደንብ እና ከሰዉ ሀይል ጋር በተያያዘ ያሉትን ችግሮች በመፍታት የመድሀኒት አቅርቦት ሂደቱ እንዲሳለጥ እየተሰራ መሆኑን አቶ አወል አክለዉ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
2.0K views13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 16:46:44 የሀገር ሁለንተናዊ አንድነትን በማስጠበቅ ሂደት ውስጥ ትውልዱ ከታሪክ ሊማር እንደሚገባው ተገለጸ፡፡
አሁን የተጀመረውን የሰላም ሂደት በዘላቂነት ለማስቀጠል እና በየ አካባቢው የሚፈጠሩ የጸጥታ ችግሮችን ለመቅረፍ ትውልዱ ከታሪክ ተምሮ የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ ተገልጻል፡፡
ያለፉ ታሪኮቻችንን መለስ ብሎ መመልከቱ ለጀመርነው የሰላም ሂደት ጉልህ አበርክቶ እንዳለው ለአሃዱ የገለጹት የታሪከ ምሁሩ ፕሮፍሰር አህመድ ዘኸርያ ባለፉት ታሪኮቻችን ላይ ያሉት እውነታዎች ሰላምን በማምጣት ረገድ ይቅርታን አማራጭ አድርጎ መመልከት ለሃገር ሁለንተናዊ ሰላም እና ልማት መረጋገጥ ጉልህ አበርክቶ እንዳለው ተናግረዋል፡፡
ባለፉ ታሪኮቻችን ላይ የነበሩ እውነቶችን በምሳሌነት አንስተው ለዛሬው ትውልድ በማሳያነት ያቀረቡት ሌላኛው የታሪክ ምሁር አቶ ደረጄ ተክሌ በሃገሪቱ ውሰጥ በአሁኑ ጊዜ በአንጻራዊነት እየሰፈነ ያለውን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል በተለይ ወጣቱ ትውልድ ካለፉት መልካም ተሪኮቹ መማር እንዳለበት እና ለሀገር ስላም እና ልማት በጋራ በመቆም የበኩሉን አስተዋጽኦ ሊያበረከት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ ያለፉ ታሪኮቻችንን መልካም ተሞክሮዎች በመውሰድ ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚገባውም ምሁራኑ ተናግረዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.9K views13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 16:43:51
በተለያየ ምክንያት ሀገር አቀፍ ምርጫ ባልተደረገባቸዉ አከባቢዎች ምርጫ ለማካሄድ አስፈላጊዉን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡
ሀገር አቀፍ ምርጫ ሳይደረግባቸዉ የቀሩ ቦታዎች ምርጫዉን ለማካሄድ አስፈላጊዉን ዝግጅት እና ማጣራት እየተደረገ መሆኑን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ ተናግረዋል፡፡
በፀጥታ ምክንያት ምርጫ ያልተደረገባቸዉ አከባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታዎች የማጣራት ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
በተጨማሪ የምርጫዉ ሂደት ስህተት ያለዉ በመሆኑ ምክንያት እንዲደገሙ የተወሰነባቸዉ አከባቢዎች ምርጫዉን ለማድረግ አስፈፃሚዎችን የመመልመል ስራ እየተሰራ እንደሆም ገልፀዋል፡፡
በቀጣይም የማሟያ ምርጫ በፍጥነት የሚደረግበትን እቅድ በማዉጣት ይፋ እንደሚደረግ ገልፀዉ ምርጫ ቦርድ ብዙ ምርጫ ሂደቶችን በመፈጸም ረገድ ክህሎቱን እና አቅሙን እያሳደገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
በቅርቡ ከተደረገዉ የደቡብ ክልል ህዝበ ዉሳኔ ቁጥጥር እና ክትትል ማድረግ የሚያስችሉ ቀልጣፋ አሰራሮችን በመተግበር አቅሙንና ክህሎቱን እያዳበረ መምጣቱን አስታዉቀዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.6K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 16:43:05 አድዋ ህዝባዊ በዓል እንደመሆኑ በበዓሉ አከባበር የታዩ ችግሮች ሊደገሙ እንደማይገባ ተገልጻል፡፡
የዘንድሮ የአድዋ ድል በዓል አከባበርን ምን ይመስላል የበዓሉ አከባበር ሌሎች ዓለም ሀገራትን የሚስብና ታሪክን ከማስተዋወቅና ስለ አድዋ የአንደነትና የጽናት ተምሳሌት ለማሳየት ምን መሰራት አለበት ሲል አሀዱ የሚመለከታቸዉን አካላት ጠይቋል፡፡ የታሪክ ተመራማሪው ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ ከባለፈው ስርዓት ጀምሮ የዓድዋል በዓል እንዲደበዝዝ የማድረግ ሁኔታዎች በብዙ ይስተዋላሉ ነዉ ያሉት፡፡
የአድዋ ድል ማለት ሀገር ከመከራ እና ወረራ ነጻ የወጣችበትን ቀን በማሰብ የሚከበር ነው ያሉት ጋዜጠኛ ጥበቡ ከዘንድሮ አመት ጀምሮ በመከላኪያ ሚኒስቴር መሪናት እንዲከበር መደረጉ የሚደግፍ ነው ብለዋል፡፡ በዓሉ በመንግስት ደረጃ ታስቦ መከበሩ ብቻ ሳይሆን ማህበረሰቡ አድዋን በሚገባ እንዲያከብርና የግጭት መነሻ እንዳይሆን እና እንዳይፈጠር ሽፋን መስጠት ያስፍልጋል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
ማንኛውም ሰው በዓሉን ቅሬታ ኖሮበት ማክበር የለበትም፤ የዓድዋ ድል ሀገርን የመጠበቅ ፍልስፍና የታየበት በመሆኑ በበዓሉ አከባበር የሚታዩ ችግሮች ሊደገሙ አይገባም ሲሉም ተናግረዋል፡፡ ሌላኛዉ የታሪክ መምህሩ አቶ በላይ ስጦታዉ በሀገራችንም በዓሉን የማደብዝዝ በተለያዩ መንገዶች ይስተዋላሉ ብለዉ በዘንድሮ የአከባበር ስነስረአት ላይ የታዩ አንዳንድ ችግሮችም መደገመ የሌለባቸዉ ናቸዉ ሲሉም ገልጸዋል፡፡በገዛ ሀገራቸው ዜጎች እንደሌላ ሀገር ዜጋ መታየት የለባቸውም ያሉት መምህሩ በዚህ ረገድ ገና ቀሪ ስራዎች አሉን ነዉ ያሉት፡፡
የአድዋ ድል በአፍሪካ በአለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው እንደመሆኑ በዓሉን በማስተዋወቅ ረገድ ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ፤መገናኛ ብዙን ለበዓሉ ትልቅ ትኩረት በመስጠት መስራት አለባቸው ተብሏል፡፡ በዓሉ አንድነት የታበት እንደመሆኑ አሉታዊ አስተሳሰቦች ለጸጥታ ችግር የሚያጋልጥ በመሆኑ ሊታሰብበት ይገባል ነው ያሉት፡፡ ከ127ኛ አድዋ ድል በአዓል ጋር በተያያዘ በተለያዩ ቦታዎች ወጣቶችና የጸጥታ ሀይሎች እሰጣ ገባ ዉስጥ ገብተዉ እንደነበር አሀዱ መመልከት ችሏል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.8K views13:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 17:06:24
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት በተያዘው ሳምንት ወደ አፍሪካ አህጉር ለመጓዝ ማቀዳቸው ተነግሯል፡፡
የፈረንሳይ መንግስት የአፍሪካን አህጉር ለሩሲያ ቅርምቶሽ እንደማይተወውም ነው የሚገልጸው፡፡
ፈረንሳይ በአፍሪካ አህጉር በርካታ ሀገራት የነበራት ተፅእኖ ፈጣሪነት እየተሸረሸረና በወታደራዊም ፤በፖለቲካውም የደረሰባትን መገለል መልሶ ለማስተካከል የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ አፍሪካ አህጉር ይጓዛሉ ነው የተባለው ማክሮን በዚህ የአፍሪካ ጉዞቸውም ሶስት የአፍሪካን ሀገራት እንደሚጎበኙ ይጠበቃል፡፡
የምዕራብ አፍሪካ ቀጣና በርካታ ሀገራት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ተይዘው ዘመናትን ያለፉ መሆናቸው የሚታወቅ ነዉ፡፡
ፈረንሳይ ዛሬም ቢሆን በምዕራብ አፍሪካ ባሉ ሀገራት ወታደሮቿን አስፍራ መዝለቋ ሲነገር እንደ ቡርኪናፋሶ መሰሎቹ የቀጠናው ሀገራት የፈረንሳይ ወታደሮች ምድሯን ለቀው እንዲወጡ ማዘዟ በፈረንሳይ ዘንድ ቁጣና ቁጭትን መፍጠሩ ይታወቃል፡፡
የዘገባው፡-የኢንዲያ ቱዴይ ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.9K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 17:02:18
ናይጄሪያ በርእደ መሬት አደጋ ክፉኛ ለተጎዳችዋ ቱርክ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጓ ተገልጿል፡፡
የናይጄሪያ የፌደራል ከተሞች ሚንስትር ሙሃመድ ሙሳ ቤሎ በሰጡት ማብራሪያ የናይጄሪያ መንግስት በርእደ መሬት አደጋ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎቿን ላጣችዋ ቱርክ የአንድ ሚሊየን ዶላር እርዳታ መስጠቱን አስታውቀዋል፡፡
ቤሎ ማብራሪያውን የሰጡት የሀገሪቱን የልኡካን ቡድን እየመሩ በአደጋው የተጎዳችውን ቱርክን ሲጎበኙ ነው፡፡
በቤሎ የሚመራውን የናይጄሪያን የልዑካን ቡድን በዋና ከተማዋ አንካራ ተገኝተው አቀባበል ያደረጉት የቱርኩ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አምባሳደር ሜቭሉት ካቩሶግሉ ናቸው፡፡
በቱርክ የርእደ መሬት አደጋ ክፉኛ የተጎዳችውን ቱርክን ለመጎብኘት የተጓዘውን የናይጄሪያን የልዑካን ቡድን እየመሩ የሄዱት ቤሎ ለቱርኩ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር በሰጡት ማብራሪያ የናይጄሪያው ፕሬዝዳንት ሙሐመዱ ቡሃሪ በምርጫ ሂደት ላይ ስላሉ በአካል መጥተው ለመጎብኘት አልቻሉም ነው ያሏቸው፡፡
ዘገባው፡-የዘ ጋርዲያን ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahadutelevision
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቴሌግራም፡- https://t.me/ahadutelevision
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦ https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24
1.8K views14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-28 16:59:47
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን የተከሰተው ድርቅ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ህጻናት አድን ድርጅት አስታወቀ፡፡
በዞኑ ውሃ ፤ የጤናና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶች በአፋጣኝ እንደሚያስፈልጉ የተናገሩት የኢትዬጵያ ህጻናት አድን ድርጅት የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የሚዲያ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ አብዱራዛቅ አህመድ ናቸው፡፡
የተከተሰው ድርቅ ከፍተኛ ችግር እያስከተለ በመሆኑ በ35 ወረዳዎች ላይ ድጋፍ የማድረግ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸዉን ዳይሬክተሩ አንስተዉ ድርጅቱ ከ2 መቶ በላይ ትምህርት ቤቶች ላይ ለተማሪዎች ምገባ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በድርቁ ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ እየተደረገ እንደሆነና በድርቁ ምክንያትም ከ2 ሚሊየን በላይ እንስሳት እስካሁን መሞታቸውን አንስተዋል፡፡ ቦረና ላይ ከተከሰተው ድርቅ ባልተናነሰ በምስራቅ ሀረርጌም በዜጎች እና በእንስሳት ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ገልጸው በዚህ ምክንያት ግን እስካሁን የሞተ ሰው በእነርሱ በኩል ያገኙት መረጃ እንደሌለ ተናግረዋል፡፡
አርሶ አደሩ ላይ ከፍተኛ ጫና እንደፈጠረ የተናገሩት ዳይሬክተሩ ዝናብ ካልዘነበ አሁንም በዞኑ ያለው ችግሩ እየተባባሰ እንደሚመጣና በዞኑ ካለው ችግር፤አንፃር የሚደርሰው እርዳታ ተመጣጣኝ እንዳልሆነ በማንሳት ድርጅቱ ቦረና ላይ ለደረሰው ድርቅ እርዳታ ተደራሽ ለማድረግ ድጋፎችን እያሰባሰበ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡
በጤና ጣቢያዎችም ጭምር የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ድርጅቱ በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዉ በዞኑ ኮሌራ እና ሌሎች በሽታዎችም ተከስተዋል ነዉ ያሉት፡፡ በዞኖ የተከሰተው ድርቅ አፋጣኝ እርዳታ እና ድጋፍ እንደሚሻ አስገንዝበዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
1.6K views13:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ